TheDeepThingsOfGod
前往频道在 Telegram
1 810
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
1 810
ቅዱሳት መጽሐፍትን የማንበብ፣ የማሰላሰል እና የማድረግ(የመለማመድ) አንዱ ውጤት ኢየሱስ ክርስቶስን ተገልጦ ማየት ነው። @TheDeepThingsOfGod
1 810
ቅዱሳት መጽሐፍት እና ኢየሱስ ክርስቶስ
ከዚህ በፊት ደጋግሜ እንዳልኩት ሁለቱም መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "የእግዚአብሔር ቃል" በመባል ተጠርተዋል። ቅዱሳት መጽሐፍትም ኢየሱስ ክርስቶስም የእግዚአብሔርን ሃሳብ፣ ምክር፣ በሕሪይ...ወዘተ የምናይባቸው ናቸው። በሁለቱም መካከል ፍጹም የሆነ አንድነት አለ (the scriptures and Jesus are identical) ቅዱሳት መጽሐፍት የተጻፈውን የእግዚአብሔር ቃል የያዙ ስሆኑ ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ አካላዊ (personal) የእግዚአብሔር ቃል ነው። ቅዱሳት መጽሐፍት የተጻፈ የእግዚአብሔር ቃል ናቸው ስንል ያልተጻፋ የእግዚአብሔር ቃል አለ ማለት ነው፥ ይሄ ማለት ቅዱሳት መጽሐፍት ጠቅላላውን የእግዚአብሔር ሃሳብ፣ ስራ፣ ንግግር እና በሕሪይ በዉስጣቸው አልያዙም ማለት ነው፥ ነገር ግን የሰውን ልጆች ወደ አካላዊዉ(personal) ቃል ወደሆነው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ለመጠቆም እና ለመምራት ከበቂ በላይ የሆነ እውነት በውስጣቸው ይዘዋል።
29 ምሥጢሩ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ነው፤ የተገለጠው ግን የዚህን ሕግ ቃሎች ሁሉ እናደርግ ዘንድ ለእኛ ለዘላለምም ለልጆቻችን ነው። ዘዳግም 29፥29 እግዚአብሔር በቅዱሳት መጽሐፍት በኩል ያልገለጠው ምሥጥር አለ፥ ነገር ግን በቅዱሳት መጽሐፍት የተገለጠው ሁሉ ለጥቅማችን ነው፥ እግዚአብሔር ያለውን ሁሉ የገለጠው በኢየሱስ ክርስቶስ ነዉ። አሁን የቅዱሳት መጽሐፍትን ዋና ዓላማ መመልከት እንችላለን፥ ይህም የሰውን ልጅ ወደ ኢየሱስ መጠቆም እና መምራት እንጂ በፍጹም ለእግዚአብሔር ያለውን ሁሉ መግለጥ አይደለም።
ቅዱሳት መጽሐፊት መስካሪዎች ናቸው---39 እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤ ዮሐንስ 5፥39 --- በዚህ ክፍል ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳት መጽሐፍት ስለእርሱ የሚመሰክሩ እንደሆኑ ይናገራል፥ ምስክር ማለት ስለሌላ አካል ያለን እውነታ የሚናገር ማለት፥ የምስክር ስራው ያየውን እና የሰማውን መናገር ወደ እውነታው መጠቆም እና መምራት ነው፥ ቅዱሳት መጽሐፊትን የሚያነብ ወይም የሚሰማ ሰው የሚመራው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ስለዚህ የትኛውም ሰው ኢየሱስ ክርስቶስን በግል ከማወቁ በፊት የግዴታ የቅዱሳት መጽሐፊትን ምስክርነት፣ መሪነት እና ጥቆማ ይሻል፥ ከልሆነ ግን በራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ማድረስ አይችልም። ቅዱሳት መጽሐፍት በሰውና በኢየሱስ ክርስቶስ መካከል ያሉ መንገዶች ናቸው፣ በቅዱሳት መጽሐፊት ብርሃን የሚመላለስ ሰው በመጨረሻ የሚደርሰው ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው፤ ያኔ ፍጹም የሆነው የእግዚአብሔር እውቀት ይገኛል፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ያለው ሁሉ ነው፥ በሁሉ ነው።
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
የእግዚአብሔር ቃል መገለጥ ነዉ፥ ምጡቅ አእምሮ ያላቸዉ ሰዎች ከራሳቸዉ ሃሳብ እና ፈቃድ አመንጭተው ያቀረቡልን የሰዎች ስራ ሰይሆን ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው የተናገሩት እና የጻፉት የመንፈስ ቅዱስ መገለጥ ነዉ። @TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
እግዚአብሔር ራሱን የገለጠ እና የሚገልጥ አምላክ ነዉ!
እግዚአብሔርን ማየት ትፈልጋለህ? አዎ ከሆነ መልስህ የት ሄደህ እግዚአብሔርን ማየት እንደምትችል እነግርሃለዉ፥ እግዚአብሔርን የማየት ጥልቅ ፍላጎት ከሌለህ ግን ይሄንን ጽሑፍ ማንበብ አቁም። እግዚአብሔር ራሱን የገለጠ አምላክ ነዉ፥ አዎ እግዚአብሔር ራሱን ሰዎች ማየት ወደሚቻላቸዊ ስፍራ አቅርቦል። እግዚአብሔርን ለማየት ልቡን ያዘጋጀ የትኛዉም ሰዉ ወደዚህ አይኖቹን ማቅናት ነዉ የሚጠበቅበት ከዚያም እግዚአብሔርን ማየት እና ማወቅ ይጀምራል።
ታዲያ ምንድነው? ብላችሁ ከጠየቃችሁኝ መልሴ የእግዚአብሔር ቃል ነዉ!።
እግዚአብሔር እራሱን የገለጠበት መንገድ እና ስፍራ የእግዚአብሔር ቃል ነዉ ---"እግዚአብሔርም ደግሞ በሴሎ ተገለጠ፤ እግዚአብሔርም በእግዚአብሔር ቃል ለሳሙኤል በሴሎ ይገለጥ ነበር።" -1ኛ ሳሙኤል 3፥21
"እግዚአብሔር በእግዚአብሔር ቃል ለሳሙኤል በሴሎ ይገለጥ ነበር" ---እነዚህ ቃላት በግልጽ የሚነግሩን እግዚአብሔር ራሱን በቃሉ እንደገለጠ ነዉ። ‘የእግዚአብሔር ቃል’ የሚለው ሐረግ በመጀመሪያ የተጻፉትን ቅዱሳት መጽሓፍት (the written word of God, scriptures) ወይም መጽሐፍ ቅዱስን እናም በመቀጠል ኢየሱስ ክርስቶስን (the personal word of God) የሚገልጽ ነዉ። እግዚአብሔር በመጀመሪያ በቅዱሳት መጽሐፍት ከዛ ደግሞ በኢየሱስ ክርስቶስ ሰዎች እርሱን ማየት እንዲችሉ ራሱን ገልጦል።
ከቅዱሳት መጽሐፍት ጋር ሰፊ ጊዜ ስናሳልፍ የእግዚአብሔርን ስም፣ ስራ፣ ሃሳብ፣ ፈቃድ፣ እቅድ፣ ፍላጎት፣ የሚወደውን እና የሚጠላዉን ሁሉ ማወቅ ድምዑንም መስማት ይሆንልናል፤ በመቀጠልም ስንታዘዘው ከማወቅ እና ከመስማት አልፈን ማየት እንጀምራለን፥ የልብ አይኖቻችን ዘላለማዊ ፊቱን ማየት ይጀምራሉ።
በማንበብ እና በመስማት ማወቅ የጀመርነውን እግዚአብሔርን በማየት እና በልምምድ (experience) በማወቅ እንቀጥላለን።
ቅዱሳት መጽሐፍት የዚህ ታላቅ እና ዘላለማዊ ጉዞ መጀመሪያዎች ናቸዉ፥ በቀጣይነትም ከእግዚአብሔር ጋር እንድንሄድ የሚያስችሉን እነርሱ ናቸዉ።
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
መገለጥ እግዚአብሔር በሁሉም ስፍራ በአንድ ጊዜ የመገኘት በሕሪይ (omnipresent) አምላክ ነዉ። “ሰው በስውር ቢሸሸግ፥ እኔ አላየውምን? ሰማይንና ምድርንስ የሞላሁ እኔ አይደለሁምን? ይላል እግዚአብሔር።”
— ኤርምያስ 23፥24 እግዚአብሔር አሁን በለንበት አለ! ይሄንን ታዉቃላችሁ?
መዝሙር 139
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ? ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ?
⁸ ወደ ሰማይ ብወጣ፥ አንተ በዚያ ነህ፤ ወደ ሲኦልም ብወርድ፥ በዚያ አለህ።
⁹ እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከ ባሕር መጨረሻም ብበርር፥
¹⁰ በዚያ እጅህ ትመራኛለች፥ ቀኝህም ትይዘኛለች።
ብዙዎች እንደሚመስላቸዉ እግዚአብሔር በሰማይ የተቀመጠ አምላክ ብቻ አይደለም ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ቃል እርሱ አጽነፈ-ሰማዩን ሁሉ የሞላ እንደሆነ ይናገራል፥ በሁሉም ቦታ መገኘቱ ለአምላክነቱ ማረጋገጫ ሆኖም በዋናነት የሚጠቀስ በሕሪይ ነዉ። ታዲያ እንዴት ነዉ ይሄንን በልምምድ( experience ) ማወቅ የሚቻለዉ? መገለጥ የሚለዉ ቃል የሚመጣው እዚህ ጋር ነዉ። እግዚአብሔርም ሆነ የእግዚአብሔር ነገሮች በአእምሮ (reasoning) ወይም/እና በስምቶቻችን (feelings) ጨርሰን ማወቅም ሆነ መረዳት የምንችላቸዉ አይደሉም። የእኛ የማሰብ አቅም (reasoning) እጅግ የተወሰነ መሆኑን ለመረዳት በሕይወት ስንት ጊዜ ትክክል እንደሆንን አስበን የመረጥናቸው መልሶች ስህተት ሆነዉ እንዳገኘናቸዉ ማስተዋል በቂ ነዉ፥ ስሜቶቻችንም ተለዋዋጭነት ያላቸዉ እንደሆኑ ሁላችንም የምንረዳዉ ነዉ። በተወሰነ አእምሮ እና በተለዋዋጭ ስሜት ወሰን የሌለዉን እና የማይለወጠዉን አምላክ ለማወቅ የሚቻል አይደለም፥ ብዙዎች የሚሰሩት ስህተትም ይሄዉ ነዉ። እግዚአብሔር የሚታወቀዉ በመገለጥ ነዉ፥ ከጥንት ዘመን ጀምሮ በብሉይ ኪዳንም ሰዎች እግዚአብሔርን ማወቅ የቻሉት እግዚአብሔር እራሱ በዘጋጀዉ መገለጥ በሚባል መንገድ ነዉ። በአዲስ ኪዳንም ሐዋሪያዉ ቅዱስ ጳዉሎስ “የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።”— ኤፌሶን 1፥17 --በማለት እግዚአብሔር የሚታወቀዉ በመገለጥ እንደሆነ ያስረዳል።
የእኔም ጸሎት ይሄዉ ነዉ። እግዚአብሔር እርሱን እንድናዉቀው የመገለጥ መንፈስ እንዲሰጠን እጸልያለሁ። @TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
Repost from TheDeepThingsOfGod
አባት ሆይ😭
ከአገልግሎት በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ!
ከብዙ ተከታዮች በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ!
ተጽዕኖ ፈጣሪ ከመሆን በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ!
ከመውደድ በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ!
በዓለም ሁሉ እየዞሩ ከማገልገል በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ!
ከማስተማር እና ተዓምራት ከማድረግ በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ!
ታላቅ ሰው ከመሆን በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ!
የእግዚአብሔር ሰው ከመባል በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ!
ዘመኔን በብልጽግና መጨረስ ከምፈልገው በላይ ኢየሱስን እፈልገዋለሁ!
ከሁሉም በላይ ኢየሱስ ያስፈልገኛል እኔም እፈልገዋለሁ!😭
ልሰማው፣ ላየው፣ ልመለከተው እና ልዳስሰው እፈልጋለሁ! መንፈስ ቅዱስ እባክህ ኢየሱስን አሳየኝ😭
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
ዓላማ ከሌላቸዉ ሰዎች ይልቅ ለራሳቸዉ ዓላማ ፈጥረዉ የሚኖሩ ሰዎች የተሻሉ ናቸዉ፥ ከሁለቱም የሚልቁት እግዚአብሔር እነሱን በማህጸን ከመስራቱ በፊት ያዘጋጀላቸዉን ዓላማ አግኝተዉ የሚያደርጉት ናቸዉ። @TheDeepThingsOfGod
1 810
ዓላማ ሦስት ፊደል፥ አጭር ቃል ነገር ረጅሙ የሰዉ ልጅ ሕይወት ምን እንደሚመስል የመወሰን አቅም ያለውን ሃሳብ ያዘለ ነዉ። በዚህኛዉ ሕይወት ከአምላክ እዉቀት ቀጥሎ ትልቅ ዋጋ ያለው ለኑሮ ትርጉም፣ አቅጣጫ እና ፍጹም ዉበት የሚሰጥ እዉቀት ቢኖር የዓላማ እዉቀት ነዉ።
ዓላማህ/ ዓላማሽ ምንድነዉ? @TheDeepThingsOfGod
1 810
https://youtu.be/0tmPtN5wnfU
Three years ago, as Pastor Benny Hinn renounced the prosperity gimmicks! Watch the full interview and learn!
1 810
በለጠግነት መንፈሳዊ፣ አእምሮአዊ፣ አካላዊ፣ ቁሳዊ እና መህበራዊ ሕይወታችንን ሁሉ የሚመለከት ሁለንተናዊ ሃሳብ ነዉ። ሰዉ በጥረቱ በለሃብት መሆን ይችላል፥ በለጠጋ የሚያደርግ ግን የእግዚአብሔር በረከት ነዉ። @TheDeepThingsOfGod
1 810
ወንጌል የብልጽግና አይደለም ስል ብልጽግና የእግዝአብሔር ፈቃድ አይደለም እያልኩኝ አይደለም። እውነት ነዉ ወንጌል የብልጽግና አይደለም ብልጽግና ግን ለሕዝቡ የእግዝአብሔር ፈቃድ ነዉ፥ እንዲያዉም እግዝአብሔር የሕዝቡን ሰላም እና ብልጽግና የሚወድ በዚህም ደስ የሚሰኝ አምላክ ነዉ።
@TheDeepThingsOfGod
1 810
ወንጌል
ወንጌል ግልጽ ነዉ፥ ስለ ልጁ ነዉ። ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነዉ፥ በፍጹም ሌላ ትርጉም ሊሰጠዉ አይገባም።
ሮሜ 1፥3 ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ወንጌል በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል፣ ሞት እና በሦስተኛው ቀን ከሙታን መነሳት የሚያምን ኃጢአተኛ ከኃጢአት እና ከዘላለም ፍርድ የሚድንበት የእግዚአብሔር የማዳን ሃይል ነዉ። ወንጌል የእግዚአብሔርን ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስን ልድት፣ ሕይወት፣ መስቀል፣ ሞት እና ከሙታን መነሳት በኃጢአት ለወደቀዉ የሰዉ ልጅ እና ዓለም የሚያበስር ታላቅ መልካም ዜና ነዉ፥ ከዚህ ታላቅነቱ አሳንሶ እና ከቁሳዊ ነገር ጋር አገናኝቶ የብልጽግና ወንጌል ማለት እጅግ ታላቅ ኃጢአት ነዉ፥ እግዚአብሔር ቁሳዊዉ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት አስቦ አንዲያ ልጁን መስዋአት አድርጎ የሰራዉን ወደር የሌለዉን ስራ ማርከስ ነዉ፥ ይህንንም የሚያደርግ የተረገመ ይሁን ይላል ቃሉ።
ገላቲያ 1፥ 8 ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን።
ወንድምና እህቶች ልናስተዉል ይገባል ወንጌል አምላክ (የእግዚአብሔር ልጅ) ስጋ የሆነበት፥ በነገር ሁሉ እኛን የመሰለበት፣ ከኃጢአት በቀር እንደእኛ የተፈተነበት(ስለዚህ ይራራልናል)፥ የሰዉ ልጅ ፍጹም ከኃጢአት የጸዳ ሕይወት የኖረበት፣ በእኛ ምትክ ስለኃጢአታችን ሁሉ ታላቅ መከራን የተቀበለበት(ስለዚህ ከእግዚአብሔር ፍርድ ድነናል)፥ ኃጢአት ሰርቶ የማያውቀዉ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ኃጢአት የሆነበት(እኛ የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ)፥ እኛን ከዘላለም ሞት ለማዳን የሞተበት፥ እኛን ለማጽደቅ በሦስተኛዉ ቀን ሞትን አሸንፎ ከሙታን የተነሳበት ታላቅ የእግዚአብሔር የማዳን ስራ ነዉ፥ ቆም ብለን እናስብ ከዚህ የሚበልጥ በሰማይም ሆነ በምድር ከምድርም በታች የተደረገ ምን አለ? ምንም የለም።
በታሪኪ የሰማነዉ እና ያነበብነዉ የቀደመው ዘመን የቤተክርስቲያን ክብርና ዓለምን የሚኮንን ንጽሕና፣ ቅድስና እና ዉበት እንዲመለስ የመጀመሪያዉ ማድረግ ያለብን እውነተኛዉን የወንጌል መልእክት ወደሚገባው የክብር ስፍራ መመለስ ነዉ። በልባችን፣ በቤተሳባችን፣ በአጥቢያ አብያተክርስቲያናት ሁሉ የጥንቱ የወንጌል መልእክት ወደከፍታዉ ይመለስ ያኔ እኛም አብረነዉ እንከብራለን።
የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን፥ አሜን።
🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻🔻
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
"ቤተ ክርስቲያን ቴአትር ቤት፣ እኛም ኮሜዲያን ሆነናል!"
ብዙ አማኝ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመጣው ለመዝናናት ነው። ሌላውም ሰው ጆክ ሲያምረው፣ መሳቅ ሲፈልግ የእኛን ቪዲዮዎች ነው የሚያየው። በኢየሱስ ስም፣ በልሳን፣ በጸሎት ከት ከት ብሎ ይስቃል። እኛም አብረን እንስቃለን። ምንም ስለማይመስለን ቪዲዮውን እየተቀባበልን እንስቃለን። የእግዚአብሔር ስም መቀለጃ ስለሆነ የሚያየው አይፈራው፣ የሚሰማን አይፈራው። እኛም አላከበድነው በሚገባ አላሳየነው፣ አልገለጥነው፣ አላመጣነው...።
የአብዛኞቻችን አገልጋዮች ዓላማ ራሱ ሰውን ማዝናናት ነው፤ "ምን ብናገር አዝናናዋለሁ ነው።" የብዙ ምዕመናን የቤተ ክርስቲያን፣ የስብከትና የአገልግሎት ምርጫ "የት ብሄድ ያልተካበደ ነገር እሰማለሁ"፣ "መዝናናት አገኛለሁ" የሚል ነው። ቤተ ክርስቲያን ቴአትር ቤት፣ እኛም ኮሜዲያን ሆነናል።
ተዉ እንጂ ብዙም ሩቅ ባልሆኑ ዓመታት፣ የዛሬ ሰልሳ ዓመት ወደ ኃላ "ሪዋይንድ" ብታደርጉ አማኞች የሚፈራ ምገስ ነበራቸው። ሰዎቹ ዛሬም በሕይወት ስላሉ ሄዳችሁ ጠይቋቸው። በቤተ ክርስቲያናቸው ደጃፍ ማለፍ እንኳ ያስፈራ ነበር። ሕይወታቸው ግርማ ነበረው። መልዕክታቸው አስደንጋጭ ነበር። ለማስደንገጥ ብለው ሳይሆን እግዚአብሔር በመካከላቸው ነበር።
እዚያ ለመቀለድ አትሄድም፤ ንሰሐ እንጂ ጆክ ትዝ አይልህም። አጋንንት ይወጣል፣ ሰዎች ይፈወሳሉ። የእግዚአብሔር ቃል፣ የክርስቶስ ወንጌል ይሰበካል። ይኼ ሁሉ የሚሆነው ፐርፌክት [ፍጹማን] ክርስቲያኖች ስለሆኑ አይደለም። ግን የኢየሱስን ስም አስከባሪዎች ነበሩ።
አሁን ቢያንስ ስሙ በሆነ መንገድ ይከበር ዘንድ ብንጸልይስ? ቢያስፈልግ ኮሜዲያኖቹን በጊዜ ቢወስደን፤ ይኼም እኮ አንዱ መንገድ ነው። ወይም ደግሞ ጥግ አስይዞን የሆኑ ሌሎች ሰዎች ቢያመጣ፣ እኛ ዕድሉን አልጠቀም ስላልን ሌላን ትውልድ ቢያስነሳልን፣ ስላላየናቸው እንጂ እግዚአብሔር ስሙን የሚያስከብሩለት ልጆች አሉታ!...
በዚህ ዘመን ወንጌል የምንሰብክበት ብዙ መድረክ አግኝተን፣ ሚዲያ ተመቻችቶልን አልተጠቀምንበትም። በየሰዉ ቤት የጌታን ስም ተሸክመን ለመግባት እንደዚህ ዘመን ዕድል ተሰጥቶን ያውቃል እንዴ? እኛ ግን ጆካችንን ይዘን ገባንበት፤ እግዚአብሔርን መሳለቂያ አደረግነው። ስለዚህ ወገኖቼ በአሕዛብ መካከል የተነቀፈው ማንነቱ የቀለለው ስሙ መልሶ እንዲከብድ በየትኛውም መንገድ ምክንያት ለመሆን መጸለይ አለብን።
ዶ/ር ማሙሻ ፈንታ
@TheDeepThingsOfGod
1 810
የእግዝአብሔር እንጅ የብልጽግናም ሆነ የድህነትም የሚባል ወንጌል የለም። እግዝአብሔር አንዲያ ልጁን መስዋአት አድርጎ የሰራዉን ዘላለማዊ ታላቅነት ያለውን የሰዉን ልጅ የማዳን ስራ አሳንሶ እና ከቁስ ጋር ብቻ አገናኝቶ "የብልጽግና" ማለት የሰዉ ልጅ እግዚአብሔርን ከምበድልባቸዉ በደሎች ሁሉ በላይ እንደሆነ ይመስለኛል። @TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
1 810
ሰላም የተወደዳችሁ በዚህ ርእሰ ዙሪያ መወያየት፣ ማወቅ፣ ማሳወቅ ለሚፈልጉ ወንድምና እህቶች ሁሉ ይሄንን መልእክት አጋሩ፤ የቤተክርስቲያን ነገዎች እኛ ነን፥ ስለዚህ ይወቅ ወይም ያሳዉቅ የምትሉትን ሰዉ ሁሉ ወደዝህ ቻናል ጋብዙ እንወያይ!
