ch
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览

频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 309 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 161,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 365

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 309 名订阅者。

根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 502,过去 24 小时变化为 16,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 48.88%。内容发布后 24 小时内通常能获得 13.10% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 0 次浏览,首日通常累积 1 875 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

14 309
订阅者
+1624 小时
+1117
+50230
帖子存档
ጌታ የሚወደው መባል እንዴት መታደል ነው! ጌታ ፍቅሩን የገለፀበት ከስጦታዎች ሁሉ ስጦታ እመቤታችንን ለእናትነት የሰጠው ፤ በመከራ ጊዜ ያልተለየው ታላቁ ሐዋርያ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ ሞትን ሳይቀምስ
ጌታ የሚወደው መባል እንዴት መታደል ነው! ጌታ ፍቅሩን የገለፀበት ከስጦታዎች ሁሉ ስጦታ እመቤታችንን ለእናትነት የሰጠው ፤ በመከራ ጊዜ ያልተለየው ታላቁ ሐዋርያ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ ሞትን ሳይቀምስ የተሰወረበት ዓመታዊ ክብረ በዓል ነው! መልካም በዓል! መልካም ዕለተ ሰንበት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ቅዱስ ፓትርያርኩ የሰላም ጥሪ አስተላለፉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው አባታዊ የሰላም ጥሪ አስተላለፉ። ቅዱስነታቸው በመልዕክታቸው እንደገለጹት የሰላም ትርጉሙ ተረጋግቶ መኖር፣ ወደ ዓላማ ፍጻሜ መድረስ፣ መርቆ ማለፍ ነው። ካሉ በኋላ ወልዶ ለመሳም፣ አሳድጎ ለመዳር፣ ዐርፍተ ዘመን የገታቸውን በክብር ለመሸኘት ሰላም አስፈላጊ ነው ።ብለዋል። አያይዘውም እስካሁን ድረስ የብዙ ነገሮች ዋጋ ታውቋል፤ የሰላም ተመን ግን አልታወቀም ። ሰላም ከሌለ ልጅ መቦረቅ፣ሽምግልናው ማረፍ የሌለበት ነው ። ሰላም ጠብን መግደል፣ ከእኔ ይልቅ ወንድሜ ይድላው ብሎ የልብስፋት ማግኘት ነው ። ብለዋል።ሰላም የኑሮና የሞት ፍርሃትን የሚያስወግድ ነው ። ያሉት ቅዱስ ፓትርያርኩ ሰላም ከሌለ ምድር ትታወካለች፣አራዊት መኖሪያቸውን ለቀው ወደ ጎረቤት ሀገር ይሰደዳሉ ። በዚህም ሰላም ለሁሉም አስፈላጊ መሆኑን እንረዳለን ። ሰላም በሌለበት ሰጪ ባለጠጋ፣ ጠያቂ ተመጽዋች ማግኘት አይቻልም ።ብለዋል የቅዱስ ፓትርያርኩ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል ፦ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! ‹‹ወዝንቱ ውእቱ ዘነገርኩክሙ ከመ በኀቤየ ሰላመ ትርከቡ፡- በእኔም ሰላምን እንድታገኙ ይህን ነገርኳችሁ›› (ዮሐ. 16÷33) ዘመናትን እያፈራረቀ በድንቅ መግቦት ሕዝቡን የሚመራ ፣ በአባታዊ ምክሩ ዕረፍትን ፣ በቃሉ ትምህርት ጥበብን ፣ በመንፈሱ ምሪት መንገድን የሚሰጥ ፤ ሰውንም ከፍጥረት ሁሉ አልቆ በመልኩና በአምሳሉ የፈጠረ፣ ሞትና ድንጋጤን የሚያስወግድ ፈቃድና ሥልጣን ያለው እግዚአብሔር አምላካችንን እያመሰገንን፤ በሩቅ ሀገራችሁን በልባችሁ ተሸክማችሁ የምትኖሩ፣ በቅርብም የሀገራችሁን ደስታና ኀዘን እየተካፈላችሁ በከተማ ውስጥ በሥራ፣ በዳር ድንበር በሀገር ጥበቃ ላይ የተሰማራችሁ፣ እንዲሁም በሕመም ሆናችሁ ፈውስን፣ በእስር ቤት ነፃነትን እየጠበቃችሁ የምትገኙ መላው ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ልጆቻችን ከሁሉ በማስቀደም ለዘመኑ ህልፈት፣ ለመንግሥቱ ሽረት በሌለበት በእግዚአብሔር ስም መንፈሳዊ ሰላምታችንን እናስተላልፋለን፡፡ የሰላም ትርጉሙ ተረጋግቶ መኖር፣ ወደ ዓላማ ፍጻሜ መድረስ፣ መርቆ ማለፍ ነው። ወልዶ ለመሳም፣ አሳድጎ ለመዳር፣ ዐርፍተ ዘመን የገታቸውን በክብር ለመሸኘት ሰላም አስፈላጊ ነው ። እስካሁን ድረስ የብዙ ነገሮች ዋጋ ታውቋል፤ የሰላም ተመን ግን አልታወቀም ። ሰላም ከሌለ ልጅነቱ መቦረቅ፣ ሽምግልናው ማረፍ የሌለበት ነው ። ሰላም ጠብን መግደል፣ ከእኔ ይልቅ ወንድሜ ይድላው ብሎ የልብ ስፋት ማግኘት ነው ። ሰላም የኑሮና የሞት ፍርሃትን የሚያስወግድ ነው ። በትክክል ኖረ የሚባለው ሰላማዊ ሰው በኑሮው ድንጋጤ፣ በሞቱም ፍርሃት የሌለበት ነው ። ሰላም ከሌለ ምድር ትታወካለች፣ አራዊት መኖሪያቸውን ለቀው ወደ ጎረቤት ሀገር ይሰደዳሉ ። በዚህም ሰላም ለሁሉም አስፈላጊ መሆኑን እንረዳለን ። ሰላም በሌለበት ሰጪ ባለጠጋ፣ ጠያቂ ተመጽዋች ማግኘት አይቻልም ። ሰላም ሁለንተናዊ መገዛትን ትፈልጋለች ፣ የሰላም ልብ ፣ የሰላም ቃል ፣ የሰላም ተግባር ያስፈልጋል ። ሰላምን አስቦ ካልተናገሩትና ካልተገበሩት ሁከት እንደ ነገሠ ይቀጥላል ። ሰላምን ተናግረውት ካላሰቡበትና ካልተገበሩት በድብብቆሽ ብዙ ሰው ያልቃል። ሰላምን በሁለንተናችን መልበስ አጭሩን ዘመናችንን ለማጣፈጥ እጅግ አስፈላጊ ነው ። በዓለም ላይ ብዙ ሺህ የሰላም ስምምነቶች ሲደረጉ ኖረዋል ። የሰው ልጅ ግን ሟች መሆኑን ረስቶ ገዳይ በመሆኑ፣ ራሱንም በራሱ ለማወክ በመፍቀዱ የሰላም ስምምነቶች ተፈርመው ፊርማው ሳይደርቅ እንደገና ሁከት ይሆናል ። በዚህም “ወይፌውሱ ቅጥቃጤሆሙ ለሕዝብየ ወይቤሉ ሰላም ሰላም ወአልቦ ሰላም፡- የሕዝቤንም ስብራት በጥቂቱ ይፈውሳሉ ሰላም ሳይሆን፦ ሰላም ሰላም ይላሉ።” (ኤር. 6፡14) የሚለው ቃለ መጽሐፍ እየተፈጸመ ይመስላል፡፡ በዘመናችን ሰዎች በትዳር፣ በቤተ ዘመድ፣ በሀገር ሰላም ያጡ እንደሆነ እየተመለከትን ነው ። ሰው የራሱን ክፉ ጠባይ መግዛት ባለመቻሉ ወዶ የሸኘውን ሲፈልገው ይኖራል ። የሕጎችም ብዛት መፈራራትን እንጂ እውነተኛ ሰላምን ማምጣት አይችሉም ። ሰላም በማጣታችን በዘገየች ሀገር ዛሬም ስለምግብ የሚጨነቅ ሕዝብ አገልጋይ በመሆናችን በታላቅ ትካዜ ውስጥ ሆነን መልእክት እንድናስተላልፍ አድርጎናል። እግዚአብሔርን ለሚወዱ የተሰጠች ጸጋ ሰላም ናት ። ታዲያ ይህ ሰላም ርቆን ሳለ እርሱን መውደዳችን እውነተኛ ነው ወይ( ብለን መጠየቅ ያስፈልገናል ። አንድ ዓይነት መልክና ማንነት ያለው ሕዝብ መተላለቁ ሰውነትንም መንፈሳዊነትንም መክሰር እንደሆነ የተረዳነው አይመስልም ። በእውነቱ ካየነው ነጭ ለብሰን ሳይሆን ማቅ ለብሰን የምናለቅስበትና በንስሐ ምሕረተ ሥላሴን የምንናፍቅበት ጊዜ ነው ። የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን! ትዕግሥተኛዋ መሬት እንኳ እየተናወጠች፣ ዓለም የቅጽበት ዕድል ብቻ እንዳላት እየጠቆመች ነው ። የመሬት መንቀጥቀጡ የዘመኑን ፍጻሜ የሚያስረዳ ሲሆን የምናያቸው ምልክቶች ሁሉ በተሰበረ ልብ እግዚአብሔርን እንድንፈልግ የሚያሳስቡን ናቸው ። በመሆኑም በሀገራችን በልዩ ልዩ አካባቢዎች ያሉ ጦርነቶች ቆመው ልጆቻችን በሰላም መኖር እንዲችሉ፤ በጦርነት እየተሰቃዩ የሕመማቸውን ልክ መናገር የማይቻለን የኦሮሚያና የአማራ ክልል ነዋሪዎች ሰላምን እንዲያገኙ አባታዊ ጥሪያችንን በድጋሚ እናስተላልፋለን ። በትግራይ ክልል ያለው የአስተዳዳሪዎች አለመግባባት በሕዝቡ ላይ ተጨማሪ ችግርና ጭንቀት እያመጣ ስለሆነ በትሕትና መንፈስ እርስ በርስ መገናዘብ ተፈጥሮ ዕረፍት ያጣው ሕዝብ መረጋጋት እንዲችል ታደርጉ ዘንድ አደራችን የጠበቀ ነው ። በተጨማሪም በትግራይ ክልል የምትገኙ የሃይማኖት አባቶች መበደላችሁን እናውቃለን ፣ በኀዘናችሁ ሰዓት አብረን መቆም ባለመቻላችን ማዘናችሁም እርግጥና ተገቢ ነው ። ነገር ግን ሁሉም ነገር የሚካሰው በእርቅ ሲሆን እኛ የገፋነውን እርቅ ዓለም ሊቀበለው ስለማይችል፤ በእጃችንም የያዝነው መስቀለ ክርስቶስ የሰላም ዓርማ ነውና ልባችሁን ለሰላም፣ ለአንድነት እንድታዘጋጁ እንጠይቃለን ። በመጨረሻም የመሬት መንቀጥቀጥ ባለበት አካባቢ እየተጨነቃችሁ ያላችሁ ልጆቻችን ረድኤተ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር እንዲሆን ቤተ ክርስቲያን በጸሎት የምታስባችሁ መሆኑን እየገለጽን መላው ኢትዮጵያውያን ለጉዳቱ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ለሚኖሩት ወገኖቻቸው አቅማቸው በፈቀደው መጠን ድጋፍ ያደርጉ ዘንድ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን፡፡ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጥር ፪ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ምንጭ፦የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

መድኃኒት ተወልዶላችኋል! “እስመ ናሁ ተወልደ ለክሙ ዮም መድኅን ዘውእቱ ክርስቶስ እግዚእ ቡሩክ በሀገረ ዳዊት-እነሆ፥ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋል፡፡ (ሉቃ.2፥11) ቅዱስ ሉቃስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም ሲወለድ ስለነበረው የልቱን ነገር ሲተርክ “በዚያን ሌሊት በቤተ ልሔም ይኖሩ የነበሩ እረኞችም ከብቶቻቸውን ሲጠብቁ የእግዚአብሔር መልአክ በእረኞቹ አጠገብ ቆመ፤ የእግዚአብሔርም ብርሃን በዙሪያቸው በራ፤ በጣምም ፈሩ፡፡ መልአኩም እንዲህ አላቸው እነሆ ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ደስታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ እነሆ፥ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋል፡፡ እናንተም ባገኛችሁት ጊዜ ምልክቱ እንዲህ ነው፡፡ ሕፃን በጨርቅ ተጠቅልሎ በበረት ውስጥ ተኝቶ ታገኙታላችሁ፤ ድንገትም ከዚያ መልአክ ጋር ብዙ የሰማይ መላእክት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ መጡ፡፡” በማለት ቤተልሔምን በዓይነ ሕሊናችን እንድናይ አድጎ በሥዕላዊ አገላለጽ ይነግረናል፡፡ (ሉቃ.2፥11-13) ቅዱስ ሉቃስ በዚህ የወንጌሉ ክፍል ከድኅነታችን ጋር በቀጥታ የሚገናኙ መሠረታዊ ነገሮችን ነገሮናል፡፡ ከእነዚህም መካከል፡- 1.የእግዚአብሔርም ብርሃን በዙሪያቸው በራ፤ ይህ ብርሃን ፀሐይ ወይም ጨረቃ አይደለም፡፡ ልዩ የእግዚአብሔር ብርሃን ነው፡፡ ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሌሊት ተወልዶ በማብራት የብርሃናት ፈጣሪ እውነተኛ ብርሃን መሆኑን አሳየን፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ በዓለም ላይ ጨለማ እንደነበረ እውነተና ብርሃን በመጣ ጊዜ ጨለማ እንዳለሸነፈው ገልጾልናል፡፡ (ዮሐ.1፡9) አስቀድሞ ኢሳይያስም በጨለማ ይሄድ የነበረ ሕዝብ ብርሃን አየ በጨለማና በሞት ጥላ ለነበሩ ብርሃን ወጣላቸው፡፡ (ኢሳ 9፡2) በማለት በሥጋ ስለሚገለጠው ብርሃን ተናግሮ ነበር፡፡ ክርስቶስ እስኪወለድ ድረስ በአዳም ኃጢአት ምክንያት ዓለም ሁሉ ማለትም የአዳም ልጆች ሁሉ በጨለማ ተውጠው ነበርና ቅዱስ ሉቃስ ጨለማውን የሚያስወግድ ብርሃን እንደተወለደ ነገረን፡፡ 2. ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ደስታ የእግዚአብሔር መልአክ በለሊት ከብቶቻቸውን ሲጠብቁ ለነበሩና ከተገለጠው ብርሃን የተነሳ እጅግ ፈርተው ለነበሩ እረኞች ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ደስታ ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ አላቸው፡፡ በዚህም የክርስቶስ መወለድ ለእረኞችና ለዓለም ሁሉ ደስታ መሆኑን ይነግረናል፡፡ ለአምስት ሺ አምስት መቶ ዘመናት ከሰው ልጅ ደስታ ርቆ የአዳም ዘር ሁሉ በኀዘን ተውጦ ነበርና ለእናንተና ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ደስታ ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ በማለት የኀዘንና የፍርኃት ዘመን እንደተወገደ የምህረት ዘመን እደመጣ ደስታችንም እንደተመለሰ ደስታው ደግሞ ለሕዝብም ለአሕዛብም በአጠቃላይ ለዓለም ሁሉ መሆኑን ነገረን፡፡ 3.መድኃኒት ተወልዶላችኋል በበደል ምክንያት ቆስለን ፍጹም ፈውስ የሚያመጣ መድኃኒት የሚያስፈልገን ታማሚዎች ነበርንና የምሥራቹን የነገረን የእግዚአብሔር መልአክ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት ተወልዶላችኋል አለን፡፡ በዚህም በቤተልሔም ከድንግል ማርያም ተወልዶ በግርግም ተኝቶ ያያነው ክርስቶስ አዳምንና ልጆቹን ከኃጢአታቸው የሚያድናቸው ከቁስላቸውም የሚፈውሳቸው መድኃኒት መሆኑን ተረዳን፡፡ 4.የሰማይ መላእክት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ መጡ ወንጌላዊው ሉቃስ የጌታን ልደት ሲተርክ የነገረን ሌላው ቁም ነገር “የሰማይ መላእክት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ መጡ” የሚል ነው፡፡ ይህም በሰውልጅ መዳን መላእክት እንደሚደሰቱ እና በኃጢአታችን ምክንያት አጥተነው የነበረውን የመላእክትና የሰው ልጆች አንድነት በጌታችን ልደት እንደተመለሰ የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህም የጋራ ዝማሬ በምድር ላይ ሰላም እንደሆነ ተገልጧል፡፡ በልደተ ክርስቶስ ሰውና እግዚአብሔር መላእክትና ሰው፣ ነፍስና ሥጋ፣ ሰማይና ምድር፣ ሕዝብና አሕዛብ ታርቀዋልና በምድር ሰላም ኾነ ሰውና መላእክትም በአንድነት ዘመሩ፡፡ በአጠቃላይ የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት፡- የእግዚአብሔር ብርሃን በጨለማ ለነበርነው ሁሉ የበራበት፣ ፍርኃት የተወገደበት፣ ለእረኞቹና ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ደስታ ደስታ ታላቅ የምሥራች የተነገረበት፣ ሰውና መላእክትም በአንድነት የዘመሩበት ታላቅ የደስታ በዓል ነው፡፡ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እግዚአብሔር አምላክ የሰውን ዘር በሙሉ ያዳነበትን ድንቅ ሥራ ሲገልጽ “ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? ከዘመን አስቀድሞ የነበረው እርሱ ሕፃን ሆኗልና፡፡ እኔ ፈጽሜ አደንቃለሁ፡፡ ከሰማየ ሰማያት በላይ የሚሆን፣ በዘለዓለማዊ ዙፋን የሚኖር እርሱ በበረት ተጣለ፡፡ ከሥጋዌ አስቀድሞ አይዳሰስ የነበረ አንዱ እርሱ በምድራውያን እጅ ተዳሰሰ፡፡ ኀጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱን በጨርቅ ጠቀለሉት፤ ይህን ወዷልና፤›› (ሃይማኖተ አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ፣ ፷፮፥፲፯) በማለት የመወለዱንና የትሕትናውን ነገር እያደነቀ ይናገራል፡፡ ይህ በዓል የአምላክ ትሕትና የታየበት የተዋረደው የሰው ልጅ ደግሞ መክበሩ የተገለጠበት በዓል ነው፡፡ ስለሆነም ልደተ ክርስቶስ ከትዕቢት ይልቅ ትሕትናን እንድንይዝ፣ ከጥላቻ ይልቅ ሰላምን እንድንሰብክ፣ ጌታችን ወደ ተዋረድነው የሰው ልጆች መጥቷልና በኑሮ ከእኛ ዝቅ ወዳሉት በትሕትና እንድንሄድ ደግፈንም እንድናነሳቸው፣ የእውነተኛው ብርሃን ልጆች ነንና በሕይወታችን የብርሃን እንጂ የጨለማ ሥራ እንዳይታይ፣ ለሰው ሁሉ የደስታ እንጂ የኀዘን ምክንያት እንዳንሆን የክርስቶስ ልደት ያስተምራናል፡፡ ስለዚህ ክርስቶስ ተወልዶ ውሉደ እግዚአብሔር ያደረገን ክርስቲኖች የፍቅርና የሰላም ሰዎች በመሆን፣ ከጨለማ ሥራ በመራቅ ትሕትናንም ገንዘብ በማድረግ የክርስቶስ ልጆች መሆናችንን ልናሳይ ይገባል፡፡ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰለም አደረሳችሁ! መልካም በዓል ይሁንልን! መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪ ሓላፊ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።" ሉቃ 2:11 እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል! የሰንበ
"ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።" ሉቃ 2:11 እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

#መልእክተ_ቅዱስ_ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፤ በምሉእ ፍቅሩ ሰውን ከባርነት ወደ ነጻነት ለመመለስ በሥጋ ሰብእ የተወለደው ጌታችን  ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ፡፡ “ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዘሠምሮ ለሰብእ፤ ክብር በሰማያት ለእግዚአብሔር ይሁን›› በምድርም እጅግ ለወደደው የሰው ልጅ ሰላም ይሁን” (ሉቃ ፪÷፲፬) ይህ ቃለ ሰላም በጌታችን ዕለተ ልደት የተነገረ ነው፣ ቃሉ የተነገረው እንዲሁ እንደ ተራ ነገር ሳይሆን በቃለ መዝሙር እየተደጋገመ ነው፡፡ የተዘመረውም በምድራውያን ደራሲዎች ሳይሆን በሰማያውያን መላእክተ እግዚአብሔር ነው፣ የያዘው መልእክትም ሰማያውያንና ምድራውያንን ሁሉ ያካለለ ነው፡፡ የመልእክቱ ገዢ ሓሳብም አምላክ ከሰውነታችን ጋር ባለመለያየት፣ ባለመጠፋፋት፣ ባለመቀላቀል፣ ባለመዋዋጥ፣ ባለመለዋወጥና ያለባዕድና አንድ አካል፣ አንድ ክዋኔ፣ አንድ ጠባይ ሆኖ በተዋሕዶ ተገልጾኣልና እግዚአብሔር ይክብር ይመስገን፡፡ የተዋሕዶውም ምስጢር ሰላምን ያሰፍናልና እግዚአብሔር ሰውን በእጅጉ መውደዱ ከዚህ ተዋሕዶ ዓውቀናል የሚል ነው፡፡ በእርግጥም እግዚአብሔር ሰውን ለመውደዱ ከዚህ የበለጠ ማሳያ ወይም ማስረጃ የለም፤ እንከን የለሽ ንጹህ አምላክ የእኛን ኃጢአተኛ ሰውነት አካሉ አድርጎ ተወለደ ሲባል ላስተዋለው ሰው ምንኛ ቢወደን ነው የሚለው ጥልቅ አድናቆትን ያጭራልና ነው፡፡ይህ ብቻም አይደለም በዚህ ነገረ ተዋሕዶ ምክንያት ሰውነታችን አምላክ ሆኖ በመንበረ ጸባኦት እንዲቀመጥ መብቃቱ የድኅነታችንና የክብራችን ከፍታ ምን ያህል አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንደደረሰ መንፈሳችን በአንክሮ ይረዳዋል፡፡ድምር ውጤቱም በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ፍጹምና አስተማማኝ ሰላም መፈጠሩን ያስረዳናል፤ ሰማያውያኑ መላእክተ እግዚአብሔር በመዝሙራቸው ያበሰሩን ይህንን የምስራች ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! እኛ ክርስቲያኖች እግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ እግዚአብሔር በእጅጉ ይወደናል ስንል እንዲሁ ከሜዳ ተነሥተን ኣይደለም፡፡ በበደላችንና በኃጢአታችን ሳይጸየፈን ሰውነታችንን በረድኤት ወይም በኅድረት ያይደለ በኩነት ተዋሕዶ ወደ አምላክነት ደረጃ ከፍ ስላደረገው  ነው እንጂ፡፡ እግዚአብሔር በዚህ ፍጹምና ምሉእ ፍቅሩ ሰውነታችንን በመበረ ጸባኦት ኣስቀምጦ መላእክት ሳይቀሩ ፍጥረታትን በሙሉ እንድንገዛ አድርጎናል፤ ምክንያቱም መላእክት በዕለተ ልደት የዘመሩለት በተዋሕዶ አምላክም ሰውም ለሆነ ለቤተ ልሔሙ ሕፃን እንጂ ለመለኮት ብቻ ኣይደለምና ነው፡፡ የዕለተ ልደት መዝሙር ዛሬም በሰማያትም ሆነ በምድር በተዋሕዶ ሰውም ኣምላክም የሆነ አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመለክበታል፣ ይመሰገንበታል፡፡የሰማዩና የምድሩ ዕርቅ ወደ ኋላ ላይመለስ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በዚህ ተከናውኖኣል፣ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሰውም አዋጭ ምርጫ ይህ ዕርቅ ተጠብቆ እንዲኖር ነው፣ ያለ ዕርቅ ሰላም ሕይወት የለውምና፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! የእግዚአብሔር ክብርና ሰላም በእጅጉ የተሳሰሩና የተቆራኙ ናቸው፤ እኛ እግዚአብሔርን ካከበርነው፣ ካዳመጥነው፣ ከታዘዝነውና ከተከተልነው ሰላም አለ ማለት ነው፡፡ ለሱ ካልታዘዝንና እሱን ካላከበርን ግን ዘላቂ ሰላምን ማግኘት ፈጽሞ የማይታሰብ ነው፤ ምክንያቱም ሰላምን ጨምሮ መልካም ነገር ሁሉ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ነውና፡፡ ዛሬ በሁሉም የዓለማችን ማዕዘን የሚታየው የሰላም መደፍረስ እግዚአብሔርን ካለማክበራችንና ለሱ ካለመታዘዛችን የተነሣ እንደሆነ መዘንጋት የለብንም፡፡ ዓለም ከእግዚአብሔር ቃል ርቃ ለመሄድ በእጅጉ እየኳተነች ነው፤ በዚህ እኩይ ተግባርዋ ደግሞ እግዚአብሔር ለስጋትና ለጉስቁልና አሳልፎ እየሰጣት ነው፡፡ እግዚአብሔር በምስጢረ ሥጋዌው ቢታረቃትም ዕርቁን ማክበር አቅቶአታል፤ ይህንን የእግዚአብሔር ጸጋ ቸል ብላ የምታደርገው ሩጫ የትም ሊያደርሳት እንደማይችል ብታውቅና በንስሓ ብትመለስ እግጅ ተጠቃሚ ትሆናለች፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! የእግዚአብሔር ቃል “እናንተስ ከማይጠፋ ዘር ተወለዳችሁ” ብሎ ተስፋውን እንደነገረን ምድባችን ከማይጠፋ ዘር እንዲሆን ክርስቲያኖች የሆን ሁላችን በአእምሮ ጐልብተን፣ በሥነ-ምግባር ኣምረን፣ ጤናማ ሕይወትን ልንመራ ይገባናል፡፡ የአምላካችንን በዓለ ልደት ስናከብር ነገረ እግዚአብሔርን፣ ነገረ ፍቅርን፣ ነገረ ዕርቅንና ነገረ ሰላምን በማኅበረሰባችን የማሥረጽ አጀንዳ ይዘን ልናከብር ይገባል፡፡ ጠቡ ፣ ጥላቻው፣ መለያየቱ፣ መጠፋፋቱ፣ ለወንድሜ  ከማለት ይልቅ ለኔ ለኔ ማለቱ ሲጎዳን እንጂ ሲጠቅመን ኣላየንም፡፡ አሁንም ወደ ልባችን እንመለስና በፍቅር፣ በዕርቅና በእኩልነት፣ በስምምነትና በወንድምነት ወደሚገኝ አንድነት እንምጣ፤ የልደቱ መዝሙር ያስተማረን ይህና ይህ ብቻ ነውና፡፡ በሌሎቹ ክፍለ ዓለማት እንደሆነው ሁሉ በሀገራችን የተከሠተው አላስፈላጊ ግጭት ብዙዎችን አሳጥቶናል፤ ብዙዎችንም ከቤት ንብረታቸው አፈናቅሎ ሜዳ ላይ ፈሰው የሰቆቃ ኑሮ እንዲገፉ አድርጎብናል፡፡ የሀገር ሀብት እንዲወድም ሆኖአል፤ ልጆቻችን ምናለ ከእንግዲህ ወዲህ ቢበቃንና ምድሪቱን የሰላም አየር እንድትተነፍስ ብንፈቅድላት፤ ይህ የወቅቱ የቤተክርስቲያናችን ዋነኛ መልእክትና ጥሪ ነው፡፡     በመጨረሻም፡- በዓለ ልደት የእግዚአብሔር በዓል ነውና፣ እግዚአብሔር በምድራችን ሰላምን ያወርድ ዘንድ ካለን ከፍለን ለተፈናቃዮች፣ ለነዳያን እና ለአካል ጉዳተኞች በመለገስ በዓሉን በመንፈሳዊ ደስታና በሰላም እንድናከብር አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤ መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር  አሜን!       አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

"እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል።" መዝ 23፡1-2 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን
"እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል።" መዝ 23፡1-2 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

እንኳን #ለብስራት_ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! በዚህ ዕለት ታላቁ መልዐክ መጋቢ ሐዲስ የተባለ ቅዱስ ገብርኤል ለዓለም ታላቁን ዜና አበሰራት ! የሰው ዘር በሙሉ ለ 5ሺ 500 ዘመን አንድ ዜናን በጉጉት ይጠብቅ ነበር ። መጠበቅ ከባድ ነው ! ግን ደግሞ መጠበቅ ተስፋ ነውና አለመጠበቅ አይቻልም። ኅጥሁ ከ ጻድቁ በአንድነት "ፈኑ ዕዴከ እም አርያም" እጅህን  ከሰማይ ከመንበርህ ላክልን እያሉ ይማጸኑ ነበር የለመኑትን የማይነሳ የተናገረውን የማይረሳ እግዚአብሔር አብዝተው ቢለምኑት አንድም ስራውን የሚሰራበት ጊዜ በመድረሱ መልዓኩን ወደ አንዲት የ15 ዓመት ብላቴና ላከው። ቅዱስ እና ሊቅ የሚሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ለጽኑ ሸክም ጽኑ ተሸካሚ ያስፈልጋል እንዳለ መለኮት ለመቀበል በንጽህና ለተገኘች ቅድስት መልዓኩ ታላቁን ዜና አበሰራት ። በዓለም ላይ ትልቁን ዜና ማብሰር ምን ይሆን ስሜቱ ?! ወናሁ ትጸንሲ ወትወልዲ :- እነሆ ትጸንሻለሽ ትወልጃለሽ ብሎ የተናገረ መልአኩ ገብርኤል ድንቅ ነገር አበሰረን ። ብስራትሽ ብስራታችን ነው ። በብስራትሽ ነገረ ድኅነታችን ታወጀልን። ድንግል ሆይ #ይኩነኒ :-ይሁንልኝ በማለትሽ የአዳም ተስፋው ፣ የአበው ልመና ፣ የነቢያት ትንቢት የአዳም ልጆች ድኅነት ተፈጽሟል። አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመውለድ በተገባ ተገኝተሻል እና አማልጂቱ ሆይ ክብር ይገባሻል። ቅዱስ ህርያቆስ እንዲህ እያለ እንዳመሰገነሽ እኔም አመሰግንሻለው ። እግዚአብሔር አብ በሰማይ ሁኖ ምስራቅን እና ምዕራብን ሰሜንን እና ደቡብን ዳርቻዎችንም ሁሉ #በአማን_ነጸረ በእውነት ተመለከተ ተነፈሰም አሻተተም እንደ አንቺ ያለ አላገኘም ። የአንቺን መዓዛ ወደደ ። ደም ግባትሽንም ወደደ ። የሚወደውን ልጁንም ወደ አንቺ ሰደደ። አንቺን የወደደ እግዚአብሔር አብ ቅዱስ ነው #በእውነት ቅዱስ ነው ! በማኅጸንሽ ያደረ ወልድ ዋሕድም ቅዱስ ነው #በእውነት ቅዱስ ነው ! ያጸናሽ የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስም ቅዱስ ነው #በእውነት ቅዱስ ነው ! መልካሙን ዜና ያበሰርክ አብሳሪው ሆይ ስለ ዛሬም መልካሙን ዜና አሰማን ! #በነገር_ሁሉ_ስለ_ሀገር_መጸለይን_አታስታጉሉ! በዲ.ን እስጢፋኖስ ደሳለኝ ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም የግማሽ ዓመት ጠቅላላ ጉባኤውን ብጹዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት አከናወነ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ታኅሣሥ 20/
+5
የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም የግማሽ  ዓመት ጠቅላላ ጉባኤውን ብጹዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት አከናወነ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ታኅሣሥ 20/04/2017 ዓ.ም የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት 11ኛ  1ኛ የ2017 ዓ.ም የግማሽ ዓመት ጠቅላላ ጉባኤውን ብጹዕ አቡነ ዮሐንስ የማዕ/ጎ/ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ :ሊቀ ሥልጣናት አባ ዮሴፍ ደስታ የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ :የሀገረ ስብከት የመምሪያ ኃላፊ: በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ አንድነት የተቋቋመባቸው ወረዳዎች የመጡ የአንድነት ተወካዮች የጎንደር ርዕሰ ከተማ አድባራት ተወካዮች በተገኙበት ዛሬ ታህሳስ 20/2017 ዓ.ም ተከናውኗል። በመርሐ ግብሩም የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤት ክፍል ኃላፊ ሊቀ አእላፍ ብርሃኑ የተበሰረ ሲሆን :የወረዳ ሰ/ት/ቤት አንድነት ሪፖርት እና እቅድ የቀረበ ሲሆን :የሀገረ ስብከቱ ሰ/ት/ቤት አንድነት ሪፖርት እና እቅድ ደግሞ በሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ሰብሳቢ ዲ/ን አንዳርጋቸው  ቀርቦ የተገመገመ ሲሆን እንዲሁም የሥርዓተ ትምህርት ሥልጠና:የሰ/ት/ቤቶች ተሞክሮ እና ውይይቶች ተከናውነዋል። በመጨረሻም በክቡር ስራ አስኪያጁ በጉባዔው ለተነሱ ጥያቄዎች በሀገረ ስብከት በኩል የሚፈጸሙትን መልስ በመስጠት እና በብጹዕ አቡነ ዮሐንስ አባታዊ መልዕክት በአጽንኦት የተላለፈ ሲሆን  ማሳረጊያ ጸሎት ተደርጎ ፍጻሜውን አግኝቷል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የአዲስአበባ ሰንበት ት ቤቶች አንድነት አስራ አንደኛ ዓመት የስድስት ወር የሥራ አፈፃፀም ጉባኤውን አከናወነ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ታኅሣሥ 20/04/2017 ዓ.ም "አንድነታችን ለቤ
+7
የአዲስአበባ ሰንበት ት ቤቶች አንድነት አስራ አንደኛ ዓመት የስድስት ወር የሥራ አፈፃፀም ጉባኤውን አከናወነ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ታኅሣሥ 20/04/2017 ዓ.ም "አንድነታችን ለቤተ ክርስቲያናችን" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደው ጉባኤ ከአ/አ ሁሉም ክፍለ ከተሞች አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የተውጣጡ የሰንበት ት/ ቤቶቾ የሥራ ኃላፊዎች እና ወጣቶች የታደሙ ሲሆን የሥራ አፈፃፀም ሪፖርቶች ቀርበው ውይይት እና ምክክር ተደርጓል። የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የሰንበት ትቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ እንዲሁም ሊ/ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና መጋቤ ሐዲስ ፀጋ ወልደ ትንሳኤ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ሐላፊ በጉባኤው  ተገኝተዋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ።" ሉቃ 1:19 እንኳን ለገናናው መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅ
"እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ።" ሉቃ 1:19 እንኳን ለገናናው መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤ እነርሱ ይምሩኝ፥ ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ።" መዝ 42(43)፡3 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይ
"ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤ እነርሱ ይምሩኝ፥ ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ።" መዝ 42(43)፡3 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

"ወንድሞች ሆይ፥ የመከራና የትዕግሥት ምሳሌ የሆኑትን በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያትን ተመልከቱ።" ያዕ 5፡10 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
"ወንድሞች ሆይ፥ የመከራና የትዕግሥት ምሳሌ የሆኑትን በጌታ ስም የተናገሩትን ነቢያትን ተመልከቱ።" ያዕ 5፡10 ሰናይ ሌሊት! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok