የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览
频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 309 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 167,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 365 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 309 名订阅者。
根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 502,过去 24 小时变化为 16,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 48.88%。内容发布后 24 小时内通常能获得 13.10% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 0 次浏览,首日通常累积 1 875 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
14 309
订阅者
+1624 小时
+1117 天
+50230 天
帖子存档
+7
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሁለተኛውን መንፈቅ ዓመት የሙከራ (Model) ምዘና ሰኔ 15/2017 ዓ.ም አከናወነ።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ወጥ ሥርዓተ ትምህርት ቀርጾ ማስተግበር ከጀመረ ዓመታት አስቆጥሯል ። በዚህም መሠረት አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት አራት እርከኖች ያሉት ሲሆን ተማሪዎች ከአንዱ እርከን ወደሌላው እርከን ሲዘዋወሩ በሀገረ ስብከት ደረጃ ምዘና ተደርጎላቸው ማለፍ ይጠበቅባቸዋል።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነትም ይሄንን ምዘና ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ እየሰጠ ይገኛል። በዚህ ዓመትም ሥርዓተ ትምህርቱን በመተግበር ላይ ላሉ እንዲሁም #የ4ኛ ፣ #የ8ኛ እና #10ኛ ክፍል እያስተማሩ ለሚገኙ ከ130 በላይ በሚሆኑ ሰንበት ት/ቤቶች ሰኔ 15 / 2017 ዓ.ም ላይ የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት የሙከራ (Model) ምዘና ሰጥቷል ።
በቀጣይም በዚህ ዓመት የማጠቃለያ ምዘናውን የሚወስዱና ወደ ቀጣዩ እርከን (ክፍል ) መዛወር የሚችሉት እነዚህ ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን የአንድነቱ ትምህርት ክፍል አሳውቋል።
ዘገባውን ያደረሰን የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል!
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሰኔ 9/2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለሚገኙ ገዳማት እና አድባራት አብነት መምህራን የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርትን መሠረት ያደረገ የአብነት እና የግዕዝ ትምህርት አሰጣጥ እና የማስተማር ሥነ ዘዴ ስልጠና ሰጠ፡፡
በዕለቱም ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ እና ሐድያ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ በስልጠናው ላይ የተገኙ ሲሆን ከሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ጋራ በአንድነት በመሆን የቤተክርስቲያንን አገልግሎት የተሳካ እንዲሆን ሊቃውንቱ በማስተማር እንዲበረቱ አጽኖት ሰተው አባታዊ መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡
በተጨማሪም በሦስቱም የስልጠና ማዕከላት በመገኘት ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት የተሻለ ለማድረግ ከወጣቶች ጋር መልካም ግንኙነት በመፍጠር እና በማጠናከር የበለጠ ሥራ መስራት እንደሚገባ በዚህም ሊቃውንቱ እንዲተጉ እና የበለጠ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ የሀገረ ስብከቱ ትምህርት እና ስልጠና ዋና ክፍል ኃላፊ መላከ ገነት አባ ተክለማሪያም አምኜ ስልጠናው አንዴት ከወጣቶች ጋራ ተባብሮ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት ማሻሻል እንደሚገባ የሚያስችል የምክክር እና የውይይት መድረክ መሆኑን ገልጸው አክለውም ሊቃውንቱ ይህንን ተረድተው በስልጠናው የበለጠ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ሰጥተውበታል፡፡
በተጨማሪም በሳሪስ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወአቡነ አረጋዊ ገዳም በነበረው ስልጠና ላይ የአቃቂ እና ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተክህንት ሥራ አስኪያጅ ሊቃውንቱን የቀደመውን አስተምህሮ እና የአበው ትምህርትን መሠረት በማድረግ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ወጣት ትውልድ ያለውን ዕውቀት እና መንፈሳዊ ህይወት የሚያጠነክርበትን መሠረታዊ ነገር መስራት እንደሚገባ አሳስበው በቀጣይነት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስር ለሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች ከአብነት መምህራን ጋር ጥብቅ የመማር ማስተማር ግንኙነት በማድረግ እና እንዲያስተምሯቸው በመጠየቅ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ስራውን የተሻለ በማድረግ ህጻናትን እና ወጣቶችን እንዲያስተምሩ አሳስበዋል፡፡
ስልጠናው ከዚህ ቀደም የሰንበት ት/ቤት ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ላይ በተለየም የግእዝ እና የአብነት ትምህርት ላይ የገጠመውን የመምህራን እጥረት ከእውቀቱ ምንጭ ከሆኑት ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በየአጥቢው ያላቸውን እውቀት ለሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የአብነት ትምህርቱን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ተማሪዎቹ ካላቸው የትምህርት ሰዓት ጋር መጥነው እና አዋህደው እንዴት ማስተማር እንዳለባቸው ግንዛቤ የሚያስጨብጥ እና በየትምህርት ክፍሉ ሊሸፈኑ ስለሚገባቸው ትምህርቶች የግንዛቤ መፍጠር የሚያስችል ስልጠና እንደነበር ለመገንዘብ ተችሏል፡፡
ስልጠናው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ካሉ ገዳማት እና አድባራት የተውጣቱ 402 ሊቃውንት አባቶች በሦስት የስልጠና ቦታ ላይ የተሰጠ ሲሆን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የስብሰባ አዳራሽ ፣ በሳሪስ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ወአቡነ አረጋዊ ገዳም እና በደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ድንግል ማርያም እና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ካቴድራል አዳራሽ ተከናውኗል፡፡
በስልጠናውም ላይ የክፍለ ከተማ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጆች ፣ የክፍለ ከተማ ቤተክህነት የክፍል ኃላፊዎች ፣ የሳሪስ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ወአቡነ አረጋዊ ገዳም አስተዳዳሪ እና የደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ድንግል ማርያም እና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ካቴድራል አስተዳዳሪ በስልጠናው ላይ ተሳትፈዋል፡፡
ይህ ስልጠናም ቀጣይነት ያለው እና ሁሉም ገዳማት እና አድባራት ላይ በመምህርነት መደብ ያሉ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት በሰንበት ት/ቤት እንዲያስተምሩ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መመሪያ ያስተላለፈ መሆኑን እና መምህራኑም ለገዳማቱ እና አድባራቱ በደረሰው መመሪያ መሠረት በየአጥቢያው ያለባቸው የሥራ ጫና ተቀንሶላቸው ወደ ማስተማሩ እንዲያተኩሩ እንዲሁም ወንበር ዘርግተው እንዲያስተምሩ ሰንበት ት/ቤቶች ከመምህራኑ ጋር አፈጻጸሙን በተመለከተ በየአጥቢያቸው ከሰበካ ጉባኤ አስተዳደር አካላት እና ከመምህራኑ ጋር በመወያየት ወደ ማስፈጸሙ እንደሚገቡ እንደሚጠበቅ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ትምህርት ክፍል ከተገኘው መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡
#የአዲስ_አበባ_ሀገረ_ስብከት_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
“ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ።” ዳን 10፡13
👉🏻 #ሚካኤል ማለት መኑ ከመ አምላክ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው የሚል ትርጉም አለው። ይህም እንደ እግዚአብሔር ያለ በባሕርይው ቅዱስ የሆነ ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ንጹሐ ባሕርይ ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ፍጹም ማነው የሚል ነው። ቅድስና ፣ ንጽሕና እና ፍጹምነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነ ከእግዚአብሔር በቀር የለምና። ዘዳ 33፡26
👉🏻 ሰኔ 12 በዚህች ቀን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሲመቱ ይታሰባል። እንዲሁም የባህራንን የሞቱን ደብዳቤ ወደ ሕይወት የቀየረበት እንዲሁም ቅድስት አፎምያን ከሰይጣን ያዳነበት መታሰቢያ ነው። "በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ።" ዘጸ 23፡20 ይህ መልአክ በብሉይ እስራኤል ዘሥጋን ከግብጽ ባርነት መርቶ ነጻ እንዳወጣቸውና ምድረ ርስት ከንዐንን እንዲወርሱ በመንገዳቸው ሁሉ እንደረዳቸው፤ እንደጠበቃቸው ሁሉ ባሕራንም ይሄድ ከነበረበት የሞት መንገድ ሕይወትን ሰጥቶ ፤ አፎምያን ደግሞ ከጥንተ ጠላታችን ከዲያብሎስ እጅ በተራዳኢነቱ አድኖ ለክብር አብቅቷቸዋል።
👉🏻 በባሕራን እና በቅድስት አፎሚያ ታሪክ ውስጥ የምናገኘው የመልአኩ ተራዳኢነት ዛሬ ላይ ላለነው ለክርስቲያኖች በሕይወታችን ውስጥ የመልአኩን ተራዳኢነት አምነን እንድንጠቀም ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ነው። ቅዱስ ሚካኤል ወይም ቅዱሳን መላእክት በሰዎች የዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ መዳን መንግሥተ ሰማይን ለመውረስ በሚደረጉ ሒደቶች ሁሉ የሚራዱና የሚያግዙ ናቸው። ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን መልእክቱ ላይ “ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስ አይደሉምን?” ብሏል። ዕብ 1፡14 ዛሬም እኛ ከቅዱሳን መናፍስት ወገን አንዱና አለቃቸው የሆነ ቅዱስ ሚካኤል መዳን መንግሥተ ሰማይን እንወርስ ዘንድ የሚላክ የሚያገለግል አይደለምን እንላለን። ማመን መጠመቅ በጎ ሥራ መሥራት ሕጉን ትዕዛዙን መጠበቅ ንስሐ መግባት እነዚህ በሙሉ ወደ መዳን / መንግሥተ ሰማያት / የሚያደርሱን መንገዶች ናቸው ፡፡
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል
👉🏻 ለሰዎች የሚራራ ፣ በተጨነቁም ጊዜ የሚያረጋጋ ፣ በደከሙ ጊዜ የሚያበረታ ፣ ባዘኑ ጊዜ የሚያጽናና ነው። ሉቃ 22፡43 ፣ ዳን 10፡20
👉🏻 የሰው ልጆችን ከመከራ ሥጋ እና ከመከራ ነፍስ የሚያድን የሚታደግ ነው። መዝ 33፡7 ፣ ዘፍ 48፡16 ፣ ዕብ 1፡14
👉🏻 ሰውን ከሚገጥመው ክፉ ነገር ሁሉ ይራዳል። ዳን 10፡13 ፣ ዳን 12፡1
👉🏻 ስለ ሰዎች ይማልዳል ከአምላካቸው ያስታርቃል። ዘካ 1፡12-13
👉🏻 ለሰው ሁሉ በጎን የሚያደርግ መልአክ ነው። ሔኖክ 6፡1-2
👉🏻 የከበረ መልአክ ነው። ከክብሩ የተነሳም ምድር ሁሉ ትበራለች። ራእ 10፡1 ፣ ራእ 18፡1
👉🏻 ትሕትናን የሚያስተምር ትሑት መምህረ ትሕትና ነው። ይሁ 1፡9
👉🏻 በሰዎች ድኅነት ሀሴት ደስታን የሚያደርግ ነው። ሉቃ 15፡7
የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነቱ አማላጅነቱ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይጠብቀን።
ይቆየን!
መልካም በዓል!
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
👉 Website
የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የሞዴልና ማጠቃለያ ፈተና ለመፈተን ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የሀገር አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አሳወቀ።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ሰኔ 8 2017ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በትግበራ ላይ በሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ተምረው ለምዘናው የተዘጋጁ ሰንበት ተማሪዎችን የመመዘኛ ፈተና ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታወቀ።
ለምዘናው የሚቀርቡ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በ2015ዓ.ም በሀገረ ስብከት ደረጃ የተዘጋጀውን የ10ኛ ክፍል መመዘኛ ፈተና ወስደው 12ኛ ክፍል የደረሱ ሰንበት ተማሪዎችን ሲሆን ለዚህም አስፈላጊውን መረጃ የመሰብሰብ አጥቢያዎችን የመለየት ሥራ መሥራቱን አንድነቱ አስታውቋል።
አንድነቱ በዘገባው የሞዴል ፈተናው የፊታችን ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን ዋናውና ማጠቃለያ ፈተናው ደግሞ በአምስት የፈተና ማዕከላት ሐምሌ 27 የሚሰጥ መሆኑን ተናግሯል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
14ኛው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ በከሚሴ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ሰንበት ትምህርት ቤት ተከበረ !
በዓለ ጰራቅሊጦስን መሠረት በማድረግ በጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና ዓለም አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በመተባበር ለ14ኛ ጊዜ የሚከብረው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን በከሚሴ ብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ ሰንበት ትምህርት ቤተ አዘጋጅነት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ገነት ደጀን ተስፋዬ የአጥቢያዎች ወረዳ ቤተ ክህነት ልዑካን የከሚሴ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤልና ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርሰቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ምህረት ልዑለ ቃል አሰፋ በተገኙበት በታላቅ ዠግጅት ተከብሮ ውሏል።
በዓሉ በጸሎተ ወንጌል በአባቶች ካህናትና ዲያቆናት የተጀመረ ሲሆን በሰንበት ትምህርት ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ ዲ ን ኤርምያስ ተፈራ የመግቢያ (የመክፈቻ) ንግግር ተደርጎ ለእለቱ የተዘጋጀው የዝማሬ አገልግሎት ከተሰጠ በኋላ "በዓለ ጰራቅሊጦስን በተመለከተና የወንጌል አገልግሎት በሰንበት ትምህርት ቤት ምን መምሰል አለበት" በሚል የምክረ አበው ጠያቄ ሰፊ ማብራሪያ በተጋባዥ መምህራን ተሰጥቷል።
በጉባኤው ከሀርቡ ቅዱስ ሚካኤል ከወለዲ ኪዳነ ምህረት ከጨፋ ሮቢት አቡነ ተክለሃይማኖት አብያተ ክርስቲያናት የሰንበት ትምህርት ሥራ አመራሮች ተገኝተዋል። በመቀጠልም በሰንበት ትምህርት ቤቱ ዋና ሰብሳቢ ብርሃኑ ወረደ ቃል የሁለት ዓመት ሪፖርት ቀርቧል በቀረበው ሪፖርትም በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አሰኪጅና በደብሩ አስተዳዳሪ አወያይነት ከሰበካ ጉባኤ፣ ከማህበረ ቅዱሳን፣ ከጨፋ ሮቢት፣ ከወለዲ፣ ከሀርቡ፣ የመጡ ታዳሚዎች ሐሳብ አስተያየት ሰጥተዋል። በአስታያየታቸውም ሰንበት ትምህርት ቤቱ ከትምህርት ባሻገር በልማት የተሻለ እንቅስቃሴ ላይ መሆኑና ከ1ኛ እሰከ 5ኛ ክፍል ከ6መቶ በላይ ተማሪዎችን ተቀበሎ በማስተማር ላይ መሆኑ ካለው የመማሪያ ቤት እጥረት የተነሳ ትምህርቱ እየተሰጠ ያለው በዛፍ ሥር ጭምር መሆኑ በሰው ኃይልም የተሟላ ባለመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ያሉትን ቤቶች በሥራ ላይ ለማዋል በጋራ በመሥራት ሁለቱም አብነቱም ሆነ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ባለመጠፋፋት መቀጠል እንዳለባቸው የተጀመረውን 1% የአሁኑ የሰበካ ጉባኤ ይሄን ሐሳብ ተቀብሎ በተሻለ መንገድ ማስቀጠል እንዲችል ተመላክቷል።
በመጨረሻም የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ገነት ደጀን ተስፋዬ ሁሉም የጽዋዕ ማህበራት ሌሎችም በመማር ማስተማሩ ላይ በገንዘብ በሐሳብ በጉልበት በእውቀት ሙሉ አቅማቸውን መጠቀም እንዳለባቸውና ሰንበት ትምህርት ቤቱ እንደ ጅምር የቻለውን ይሄን ያህል ካሳየ ማስቀጠል ደግሞ የሁሉም ባለድርሻና አጋር አካላት መሆን እንዳለበትና ከሀገረ ስብከቱ የአንድነት ጉባኤ ጋር አብሮ መሥራት እንደሚገባ አንደነቱ ከሁሉም የሰንበት ትምህርት ሥራ አመራር የተውጣጣ ስለሆነ ለአንድነቱ ሁሉም ቦታና ትኩረት በመስጠት ማጽናት ያስፈልጋል ብለዋል።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን በደማቅ ሁኔታ አካሂዷል።
የማዕ/ጎ/ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን እና የበዓለ ጰራቅሊጦስ የሰ/ት/ቤቶች ቀንን በማስመልከት ግንቦት 30 እና ሰኔ 1 ቀን ለተከታታይ ሁለት ቀናት የቆየ ጉባኤ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ሥልጣናት አባ ዮሴፍ ደስታ ፣ የሀገረ ስብከቱ ጸሐፊ ፣ የሀገረ ስብከቱ የመመሪያ ኃላፊዎች ፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ከወረዳ ሰ/ት/ቤት አንድነት የመጡ ተወካዮች ፣ በጎንደር ከተማ የሚገኙ የሰ/ት/ቤት አመራሮች እና አባላት በተገኙበት ጉባኤውን አከናውኗል።
በዚህ ጠቅላላ ጉባኤ እና የሰ/ት/ቤት ቀን ክብረ በዓል በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙት ወረዳዎች 10ሩ ተገኝተው የወረዳቸውን ዓመታዊ የአገልግሎት ሪፖርት እና የ2018 ዓመታዊ እቅድ አሰምተው ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል። በአዳሩ መርሐ ግብርም ነገረ ቤተ ክርስትያን በሚል ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ሥልጠና ከተሰጠ በኋላ ውይይቶች ተካሂደዋል።
በሰ/ት/ቤቶች ቀንም ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት የማ/ጎ/ሀ/ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ዓመታዊ የአገልግሎት ሪፖርትና የወደፊት ዕቅድ ቀርቦ ለውይይት የቀረበ ሲሆን የሰ/ት/ቤቶች አሁናዊ ሁኔታ ዳሰሳ እና መፍትሔዎች ሥልጠና ተሰጥቶች የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አሁናዊ ገጽታ እና አካሄድ ላይ ያተኮሩ ልዩ ልዩ መርሐ ግብራትና ዳሰሳ ተከናውኗል።
በመጨረሻም በክቡር ሥራ አስኪያጁ አባታዊ መልዕክት እና ሰ/ት/ቤትን እንዴት መጠበቅ እንዳለብን የአደራ መልዕክት ጋር በጸሎት ተጠናቋል።
ዘገባውን ያደረሰን የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቶች አንድነት ነው።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+7
14ኛው ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች ቀን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ዋለ።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ14ተኛ ጊዜ በሀገረ ስብከታችን ለ2ኛ ጊዜ የሚከበረው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀንን በማስመልከት በልዩ ልዩ መርሐ ግብሮች ተከብሮ የዋለ ሲሆን ሚያዚያ 18 መክፈቻውን አድርጐ ፤ ግንቦት 24 በአውደ ርዕይ እና በፓናል ውይይት ቀጥሎ ግንቦት 30 ታላቅ ኪነ ጥበብ ምሽት እንዲሁም ሰኔ 1 በሕፃናት መርሐ ግብር እና ልዩ በሆነ የጋራ አንድነት ጉባኤ ተጠናቋል።
በመዝጊያ መርሐ ግብሩ ላይም በአባቶች ጸሎት ተከፍቶ ትምህርተ ወንጌል በመምህር ዲ/ን ዘላለም ታዬ የተሰጠ ሲሆን ዝማሬዎች እና የሥነ ጥበብ ሥራዎች ከቀረቡ በኋላ ለመርሐ ግብሩ መሳካት አስተዋጽዖ ላደረጉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የምስጋና እና የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋው በመላእከ መንክራት ቀሲስ ድርሻዬ ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ የመርሐ ግብሩ መጠናቀቅ ሆኗል።
ዘገባው የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሚዲያ ነው።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+8
በዓለ ጰራቅሊጦስን የሰ/ት/ቤቶች ቀን በሚል ለመጀመሪያ ጊዜ በደ/ማርቆስ ከተማ በሚገኙት አድባራትና ገዳማት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ ተከበረ።
ጉባኤውም ለሁለት ቀናት በአድባራቱና ገዳማቱ የሰ/ት/ቤት አንድነት ጉባኤ ቤቶች በጽ/ጽዮን አብማ ማርያም ካቴድራል ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ ተከብሯል። በደብረ ማርቆስ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት ሥር የሚገኙት አድባራትና ገዳማት የሰ/ት/ቤት አንድነት ጉባኤ በዓለ ጰራቅሊጦስ የሰ/ት/ቤቶች ቀን ተብሎ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገረ ስብከቱ ሰ/ት/ቤት ክፍልና በደ/ማርቆስ ከተማ ሰ/ት/ቤት ክፍል ተዘጋጅቶ እንደተከበረ የሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤት ክፍል ገልፀዋል።
መረጃው የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ነው።
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ቤተክርስቲያን እየገጠማት ላለው ፈተና የመፍትሔ አካል ለመኾን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ኅብረታቸውን ማጠናከር አለባቸው ተባለ።
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ቀን "ሰንበት ትምህርት ቤቶች የትምህርትና የልኽቀት ማእከላት ናቸው" በሚል መሪ መልእክት በተለያዩ መርሐ ግብራት በወልድያ ከተማ ግንቦት 29 እና ሰኔ 01 2017 ዓ.ም በድምቀት ተከበረ።
በሰሜን ወሎ መንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጋር በመተባበር የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ቀን ከግንቦት 29 እስከ ሰኔ 1 በተለያዩ መርሐ ግብራት አክብሯል።
በከተማ አስተዳደር ቤተክህነቱ ስር የሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤት ሥራ አመራሮች የተሳተፉበት የውይይት መርሐ ግብር ፣ በተለያዩ ርዕሶቸ የቀረቡ ጥናታዊ ጽሑፎች ላይ ምክክርና ውይይት ተደርገዋል።
የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተክህነት የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ ክፍልና የሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ኀላፊ መ/ር ቡሩክ ተስፋየ በመርሐ ግብሩ ባስተላለፉት የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክት በአንድ መንፈስ፣ በአንድ እውነት፣ ራእይና ተልእኮ ከተሰበሰብን እግዚአብሔር በመካከላችን ይገኛልና ለበጎ ሥራ መሰባሰባችንን አንተው ብለዋል።
የአንድነቱ ሥልጠና ክፍል ተጠሪ ዲ/ን በፈቃዱ መኰንን "የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሚና ለቤተክርስቲያን ኹለንተናዊ እድገት፤ ቅዱስ ሊቀዲያቆናት ሀቢብ ጊዮርጊስን እንደማሳያ" በሚል ርእስ የዳሰሳ ጥናት አቅርበው ውይይት የተደረገበት ሲኾን ቤተክርስቲያን እየገጠማት ላለው ፈተና የመፍትሔ አካል ለመኾን ሰንበት ትምህርት ቤቶች ኅብረታቸውን ማጠናከር አለባቸው ተብሏል።
የቀረበው የዳሰሳ ጥናት ቅዱስ ሀቢብ ጊዮርጊስ ታሪኩና ለቤተክርስቲያን ያበረከተው አስተዋጽኦ፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አጀማመር በኢትዮጵያ፣ የመንፈሳዊ ሕይወት እድገት ማነቆዎች፣ የቤተክርስቲያን ፈተናዎችና መፍትሔዎቻቸው ላይ ያተኮረ ነበር።
የዳሰሳ ጥናቱ በገለጻ የቀረበ ሲኾን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ወቅታዊ ፈተናዎች፣ በሰንበት ትምህርት ቤቶች የሚከሰቱ ውጫዊና ውስጣዊ ፈተናዎችና መፍትሔው ላይ ተሳታፊዎቹ
በቡድን ተወያይተው ገለጻ አድርገዋል።
የከተማው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በስሩ ለሚንቀሳቀሱ ኹሉም ሰንበት ትምህርት ቤቶች ለሕጻናት ማስተማሪያ አጋዥ የሚኾን የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ለልጆች የተሰኘ መጻሕፍት በስጦታ አበርክቷል።
ለሰንበት ትምህርት ቤቶቹ የተበረከቱትን መጻሕፍት መግዣ ገንዘብ የለገሱ በጎ አድራጊዎችዎችን አንድነቱ የእውቅና ሽልማት አበርክቶላቸዋል።
ሕዝባዊ ጉባኤውም በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል ተከናውኗል።
ዘገባውን ያደረሰን የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቶች አንድነት ነው።
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሣኤ በ14ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ላይ ያስተላለፉት መልእክት
“ወይረድአነ ለነ ድካመነ በመንፈስ ቅዱስ - ድካማችንን በመንፈስ ቅዱስ ያግዛል፡፡ ሮሜ 8፡26
ከሁሉ በማስቀደም አምላካች ቅዱስ እግዚአብሔር እንደ ሐዋርያት በተስፋ ለምንጠብቀውና ኃይል መንፈሳዊም አግኝተን ለበለጠ ሥራ ለምንነሳበት ለበዓለ ጰራቅሊጦስ፣ ለሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን እና ለ14ኛው ዓለም ዐቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ፡፡ እንኳን ደህና መጣችሁ።
መንፈስ ቅዱስ የደከሙትን የሚያበረታ ያዘኑትን የሚያጽናና የታወኩትን የሚያረጋጋ ኃጢአተኞችን የሚያነጻ መንፈስ ነውና በደከምን ጊዜ ብርታትን፣ በመከራ ጊዜ ጽናትን፣ በፍርሐት ጊዜ ጥብአትን፣ በሁከት ጊዜ መረጋጋትን ይሰጠናል፡፡
በዘመነ ሐዋርያት የነበረው አገልግሎት በሰይፍና በስለት ውስጥ አልፎ የጠፉትን መፈለግ፣ በሞት ተወራርዶ በጎችን፣ ጠቦቶችንና ግልገሎችን መጠበቅን የሚጠይቅ ነበርና የሚያደክሙና የሚያፍገመግሙ ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች በርካቶች ቢሆኑም ሲፍገመገሙ ያጸናቸው በድካማቸውም ሁሉ ያገዛቸው የብርታታቸውና የጽናታቸው ምክንያት መንፈስ ቅዱስ ነውና “ወይረድአነ ለነ ድካመነ በመንፈስ ቅዱስ-ድካማችንን በመንፈስ ቅዱስ ያግዛል” በማለት ሐዋርያው ተናገረ፡፡
ይህ ታላቅ የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን የሆነው በዓለ ጰራቅሊጦስ በ፭ኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዘመነ ፕትርክና በቅዱስ ሲኖዶስ መልካም ፈቃድ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን ተብሎ ከተሰየመ እነሆ ዛሬ ፲፬ኛ ዓመት ላይ እንገኛለን፡፡ ባለፉት 14 ዓመታት መንፈስ ቅዱስ ድካማችንን እያገዘ ብዙ መልካም ሥራዎችን ለማከናወን በመቻላችን የጅማሬም የፍጻሜም ባለቤት የሆነውን ልዑል እግዚአብሔርን እናመሰግናለን፡፡
ዕለተ ጰራቅሊጦስ ሐዋርያት በአንድ ሐሳብ በአንዲትም ልብ ሆነው በተሰበሰቡባት ጽርሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ሁሉም የራሱን ቋንቋ በሚሰማበት ልሳን እንዲያስተምሩ የተለያዩ ልሳኖች ለሐዋርያት የተገለጡባት፣ ፍርሐት ጠፍቶላቸው ጥብአትን ገንዘብ ያደረጉባት ዕለት ናት።
ይህችን ዕለት መነሻ በማድረግ በየዓመቱ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ዕለት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን የሚያከብረው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያም እንደ ሐዋርያት አንድ ልብ በመሆን ከመምሪያው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጋር የሊቃውንት ጉባኤ አባላትን፣ የመንፈሳዊ ዩንቨርስቲና የኮሌጆች መምህራንን እንዲሁም የሥርዓተ ትምህርት ባለሙያዎችን በማሳተፍ በተዘጋጀው ወጥ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ሁሉም እንደ እድሜው ደረጃ ሊረዳው በሚችለው ልክና አቅም በተለያዩ ልሳናት መጻሕፍትን በማዘጋጀት ስያሜውን በተግባር በማሳየት ላይ ይገኛል።
ይህም ውጤት ከዚህ ቀደምም በተግባር የታየና ዛሬም በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ ታትመው ለምረቃ በተዘጋጁት መጻሕፍት የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡ ወደ ፊትም በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ በተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ቋንቋዎች መጻሕፍቱን ለማሳተም በዝግጅት ላይ ነን፡፡
ይህ ሁሉ ዘመን ተሸጋሪ የሆነና በዘላቂነት ትውልድን የሚታደግ ሥራ የተሠራውና እየተሠራም ያለው "ወሀሎ ምስሌሆሙ ኅቡረ መንፈስ ቅዱስ" መንፈስ ቅዱስ በጉባኤያቸው ሁሉ አብሯቸው ነበር እንዲል መጽሐፈ ምስጢር በሥራችን ሁሉ መንፈስ ቅዱስ ስላልተለየን በድካማችንም ስላገዘን ነው።
ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ከወረደላቸው በኋላ በሁሉም ቋንቋ ባስተማሩት ትምህርት ብዙ ነፍሳትን ማርከው “ምንተ ንግበር አኃዊነ” እንዳሰኙ ሁሉ በእነዚህ ፲፬ ዓመታት በተለይም ባለፉት ሁለት እና ሦስት ዓመታት በትኩረት በተሠራው ሥራ እና በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ ለሰንበት ት/ቤት አገልግሎት በሰጠው ትኩረትና በፈቀደው በጀት በ2016 ዓ.ም ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል በአማርኛ፣ በዚህ ዓመት በ2017 ዓ.ም ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በአማርኛ እና ከ1ኛ እስከ 4ኛ በአፋን ኦሮሞ የሰንበት ት/ቤት መማሪያ መጻሕፍት በመታተማቸው ያለቋንቋ ገደብ ወጣቶችንና ሕጻናትን በማስተማር ግልገሎችንና ጠቦቶችን የመጠበቅ የመምሪያውን ተልእኮ ለማስፈጸም ትልቅ በር ተከፍቷል፡፡ በሥርዓተ ትምህርቱም ቤተ ክርስቲያናቸውን በሚገባ ያወቁና የተረዱ፣ በሥነ ምግባርም አርዓያ፣ “ምንተ ንግበር” በማለትም የቤተ ክርስቲያን ተስፋ የሚሆኑ ወጣቶችን ለማፍራት የተሻለ ዕድል ተገኝቷል፡፡
ወደፊትም በቤተ ክርስቲያናችን በ10 ዓመቱ መሪ ዕቅድና በዚህ ጠቅላላ ጉባኤ በጸደቀው የ5ዓመት ሥልታዊ ዕቅድ እየተመራን የበለጠ ለመሥራት የምንጥር መሆናችንን እየገለጽኩ እና የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ልዩ ክትትልና የቅዱስነትዎ አባታዊ መመሪያ፣ ጸሎትና ቡራኬ እንዳይለየን በታላቅ ትሕትና እየጠየቅሁ በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት የማደራጃ መምሪያው ሠራተኞችና የመምሪያውን ተልዕኮ ለማስፈጸም በቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ ከተዋቀረው የመምሪያው የሀገር አቀፍ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሥራ አመራርና ሥራ አስፈጻሚ እንዲሁም ልዩ ልዩ አገልጋዮች ጋር በመሆን፣ በመምሪያው ሊቀ ጳጳስ መመሪያ ሰጪነት ታግዘን ከምንጊዜው በተሻለ ውጤታማ ሥራ በመሥራት ላይ እንገኛለን፡፡
በአጠቃላይ በዘንድሮው የጉባኤያችን መሪ ቃል “የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡” ብሎ ሐዋርያው እንደተናገረው የሰንበት ት/ቤት ወጣቶችና ሕጻናት መንፈሳዊ ሰይፍ የሆነውን ቃለ እግዚአብሔርን በአግባቡ ታጥቀው ክህደት ጥርጥርና ኑፋቄን ቆርጠው ይጥሉበት ዘንድ በ2017 ዓ.ም ዕቅዳችን ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተነው የነበረው የሰንበት ት/ቤት መማሪያ መጻሕፍትን ቀጣይ ኅትመት የማከናወን ተግባር ተሳክቶ በዕቅዳችን መሠረት ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በአማርኛ ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል በአፋን ኦሮሞ ማሳተም በመቻላችን እግዚአብሔርን እናመሰግናለን፡፡
በሚቀጥለው በ2018 በጀት ዓመት እግዚአብሔር ቢፈቅድ ቀሪዎቹ ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ መጻሕፍት የአርትዖት ሥራን በልዩ ትኩረት በማጠናቀቅ ለማሳተምና በተመሳሳይ በአፋን ኦሮሞም ቀጣይ የትርጉም፣ አርትዖትና የኅትመት ሥራን ለመሥራት ከወዲሁ ዝግጅት ጀምረናል፡፡
በመጨረሻም በ10 ዓመቱ የቤተ ክርስቲያናችን መሪ ዕቅድ መሠረት የተዘጋጀውን የ5 ዓመቱ ስልታዊ ዕቅድ አግባቡ በለመተግበር እንችል ዘንድ በእነዚህ ሁለት ቀናት በሚኖረን የምክክር መድረክ በዓለ ጰራቅሊጦስንና ዓመታዊ የሰንበት ት/ቤቶችን ቀን እያከበርን በቀጣይ ሥራዎቻችን ዙሪያ በትኩረት ተመካክረን የሚጠብቀንን ሰፊ አገልግሎት ባገናዘበ መልኩ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሚጠቅም፣ የወጣቱንም ሕይወት የሚታደግ ምክክር እንድናደርግ በትሕትና አሳስባለሁ፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ
የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሐላፊ
ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም
(የሰ/ት/ቤቶች አንድነት)
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
