የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览
频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 477 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 026,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 324 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 477 名订阅者。
根据 29 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 526,过去 24 小时变化为 12,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.31%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.22% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 538 次浏览,首日通常累积 1 477 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 30 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
14 477
订阅者
+1224 小时
+1357 天
+52630 天
帖子存档
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
ሞቱን ቀድማ የተረዳች ሴት
ዮሐ. 12:1
የሴት ተፈጥሮ ግልጽ ባልሆነ መንገድ ስለ ጌታ ሕማማትና ሞት አሰበ። ሴቲቱ ኃጢአተኛ የነበረች ማርያም ነበረች። ከስቅለተ አርብ ስድስት ቀን ቀድሞ በስምኦን ቤት ነበር። ከፋሲካ በዓል በፊት የነበሩ ቀናት ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ነበር። ማርያም ሽቱ ይዛ ወደ ኢየሱስ ቀረበች። ማርያም የአልአዛርና የማርታ እህት ነበረ። "ማርያምም ጌታን ሽቱ የቀባችው እግሩንም በጠጕርዋ ያበሰችው ነበረች፤ ወንድምዋም አልዓዛር ታሞ ነበር" ዮሐ.12:2 ሽቱው በጣም ውድ ነበር። በይሁዳ ግምት ሶስት መቶ ብር ነበር። ማርያም ሽቱው ውድ ቢሆንም ለእግዚአብሔር ውድ አልነበረም።
ጌታ በተወለደ ጊዜ ሰብአ ሰገል ለሞቱና ለሥርዓተ ቀብር እንዲሆን ከርቤ አምጥተው ነበር። ከምድራዊ ሕይወቱ የመጨረሻ ማርያም ለሞቱ እንደገና ከርቤ አመጣች በሽቱ እግሩንና ራሱን ቀባች። እግሩን በጸጉሯ አበሰች። ያዕቆብ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ለማቅረብ እንዲያገለግል በአንድ ድንጋይ ላይ ሽቱ በመቀባት አሰናዳ። ይህች ሴት በአዲሱ እስራኤል ላይ ሽቱ በመቀባት ለመስዋዕትነት አሰናዳች።
ሐዋርያት ሁሉም በነገሩ ያልተደሰቱ ቢሆንም ምንም አልተናገሩም የሚናገረው ይሁዳ ብቻ ነበር። ዮሐ.12:5
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይሁዳ ሲናገር የመጀመሪያ ቃሎቹ ናቸው። ምንም ትምህርት ጠይቆ የማያውቀው ይሁዳ የገንዘብ ብክነት መስሎ ታየው። አሳቡን በሙሉ ከክርስቶስ ወደ ድሆች አዛወረ። ከጌታ ይልቅ ለድሆች የሚያስብ የሚያስመስል ጥያቄ አቀረበ።
ማርያም ብልቃጥዋን ባዶ አድርጋለች ይሁዳ ግን ከረጢቱን በገንዘብ ይሞላ ዘንድ ነበር። ለእግዚአብሔር ክብር የሆነውን ነገር እንደ ማባከን ቆጠረው። ጌታችን ለሴቲቱ ተከላከለላት። በሴቲቱ ልብ ውስጥ የተደናገረውንም ነገር በግልጽ አስታወቀ። ማር14:8
ከሞቱ ስድስት ቀን ቀድማ ለቀብሩ ቀባችው። ሐዋርያት ብዙ ጊዜ ነግሯቸው ያልተረዱትን የሞቱንና የትንሣኤውን ነገር እሷ ተረድታለች። ድሆችን ሁሌ መርዳት ይቻላል ለነርሱ የተደረገውን አገልግሎት ለራሱ እንደተደረገ አድርጎ ይቆጥረዋል። ማቴ.25:40
ማርያም ላደረገችው ሥራ ዘለዓለማዊ መታሰቢያ ተደረገላት። ሥራዋ ሁሌ እንደሚነገር መድኅኒታችን ተናገረ። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "ብዙ ታላላቅ የምድር ነገሥታት ያደረጉት ነገር በምድር ተደብቆ ሲቀር ኃጢአተኛ ሴት ያደረገችው በበመላው ዓለም ሰዎች ዘንድ የሚከበር ሆነ" ብሎታል። የፈለገችው ብዙ ኃጢአቷም ተሰረየላት።
ከመምህር ነዋይ ካሳሁን
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
በአዲስ አበባ ከ30 በላይ ሰ/ት/ቤቶች ፣ ከ1500 የሚበልጡ ሕፃናት የተሳተፉበት በዓለ ሆሣዕና በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም በመርሶ ሕይወት ሰ/ት/ቤት አዘጋጅነት በትላንትናው ዕለት ተከበረ።
ሙሉ መርሐ ግብሩን ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ይመልከቱ!
https://youtube.com/live/VidG8daCrQY?feature=share
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
ሆሳዕና
“ንጉሥሽ ይመጣል”
ሆሳዕና ማለት መድኃኒት ማለት ነው፡፡ ሆሳዕና በአርያም ማለት ከሰማይ የመጣ መድኃኒት ማለት ነው፡፡ ይህ ታሪክ ከጌታ ሞት አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ የሆነ ክስተት ነው፡፡ የሞቱ ዋዜማ ነው፡፡ ክስተቱ የሆነውም በሳምንቱ መጀምሪያ ቀን ነበር፡፡ ታሪኩ በአራቱም ወንጌላት ተጽፏል፡፡ በተለያየ አቀራረብ በመመዘገቡ ሁሉንም ወንጌላት በማንበብ ሙሉ ታሪኩን ለመረዳት ይቻላል፡፡
“ወደ ኢየሩሳሌምም ቀርበው ወደ ደብረ ዘይት ወደ ቤተ ፋጌ ሲደርሱ፥ ያንጊዜ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለት ላከ፥” ማቴ. 21፣1። ደብረ ዘይት የጌታ መኖሪያ ሲሆን፡ በዋሻ ውስጥ ነበር፡፡ ቤተ ፋጌ ከደብረ ዘይት 2ኪ.ሜ ከኢየሩሳሌም ውጭ ደብረዘይት አጠገብ ነበር። ቤተ ፋጌ ማለት ደግሞ የበለስ ቤት (ከተማ) ማለት ነው፡፡ በለስ በብዛት ይበቅልባት ነበር፡፡ እንዲሁም አይሁድ ካህናት ከተማ፣ የአይሁድ መጽሐፍ (ታልሙድ) ያለባት ናት፡፡ በመሆኑም ቅዱስ ቅዱስ ጄሮም የእውቀት ቦታ በመሆንዋ “የእውቀት ብርሃን ቦታ” ያለባት ቦታ ናት ይላታል፡፡ ደብረ ዘይትን ቦታው የወይራ ዘይት ያለበት በመሆኑ “የእውቀት ብርሃን ጌታ መምጣቱን ያሳያል” ብሎታል፡፡
“እንዲህም አላቸው፦ በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ፥ በዚያን ጊዜም የታሰረችን አህያ ውርንጫም ከእርስዋ ጋር ታገኛላችሁ፤ ፈትታችሁ አምጡልኝ” እንደ ቅዱስ ጄሮም ትርጉም አህዮቹ የተሰረቁ ነበሩ፡፡ ሲገኙ ታስረው ነበር፡፡ እንዲፈቱ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት ተላኩ፡፡ ሁለቱ ደቀመዛሙርት የእውቀትና ሥራን ይወክላሉ ይላል፡፡ (የሚያውቁትን መስራትን) ሰውን መንፈሳዊ የሚያደርጉ እኒህ ሲተባበሩ ነው፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም የሁለቱ አህዮችን “ የተገዘሩትን አይሁድና ያልተገዘሩትን አህዛብ ” ይወክላሉ ይላል። አህዮቹ ታስረው ነበር፡፡ ጄሮም የታሰረችው አንዷ ነበረች ውርንጭላዋ በእናትየዋ ዙርያ ትፈነጭ ነበር ይላል፡የታሰረችው ደግሞ “በጣም ተተብትባ ነበር በአንድ ገመድ አይደለም” ይላል፡፡ ይህውም የአዳም ልጅ በታላቅ ሐጢአት መያዙን ያሳያል፡፡ በአጠቃላይ የታሰሩት አህያ አዳምና ልጆቹን ትወክላለች ።
ቅዱስ ጄሮም የታሰረች አህያ አይሁድ ሲሆኑ የሙሴ ሕግ አላቸው፡፡ አህዛብ የተሰጠ ሕግ የላቸውም፡፡ እንዲሁም የታሰረች አህያ የምኩራብ ምሳሌ ናት፡፡ ምኩራብ ወደ ቤተክርስቲያን የምታደርስ ሆና ሳለ አይሁድ የነቢያትን ትንቢት በመተርጎም ፈንታ በራሳቸው ሕግ ዋናውን የነቢያት ትምህርት ተብትበዋት ነበርና ሲል የተረጉመዋል፡፡የአዳምና የሔዋን መፈታት መቅረቡን ለማመልከት “ፈታችሁ አምጡልኝ ” አለ፡፡ የሰውን ልጅ ከሐጢአት ባርነት ሊያወጣን መምጣቱን ያሳያል፡፡ ዛሬም ብዙ ሰው ወደ እግዚአብሔር እንዳይመጣ ታስሯል መፈታት ይፈልጋል፡፡
“ፈትታችሁ አምጡልኝ ማንም አንዳች ቢላችሁ፦ ለጌታ ያስፈልጉታል በሉ፤ ወዲያውም ይሰዳቸዋል” ለጌታ የማያስፈልግ የለም ነገር ግን መፈታት ያስፈልገዋል፡፡ ለመፈታታቸው ምክያት የሆነው ጌታ ይፈልጋቸዋል የሚለው ቃል ነው፡፡ “ወደ ኢየሱስም አመጡት፥ በውርንጫውም ላይ ልብሳቸውን ጭነው ኢየሱስን አስቀመጡት” ሉቃ 19፡34 በቤተ ልሔም በተወለደ ጊዜ መድኅኒታችንን ያስተናገዱ እነርሱ ነበሩ፡፡
እስከ ዛሬ ድረስ ወደ ኢየሩሳሌም የሚጓዘው በእግር ብቻ ነበር፡፡ ሐዋርያትን አስገርሟል፡፡ ጌታ የተቀመጠው በውርንጭላው ብቻ ነበር፡፡ ለምን በግልገሉ ተቀመጠ ቢሉ፤ አዲስ ሕግ ሠራሁላችሁ ሲል ነው፡፡ የተቀመጠባት አህያ ባዶ ነበረች ሕዝቡ በልብስ አስጌጣት ፡፡አህያዋ ከፊት ይልቅ አማረች፡፡ ልብስ እንደማይቆረቁር የሐዲስ ኪዳን ሕግ ሰራሁላችሁ ሲል ነው፡፡ የሐዲስ ኪዳን ሕግ ደግሞ የፍቅር ሕግ ናት ፡፡ ባልንጀራን እንደራህስ ውደድ የምትል ናት፡፡ ልብስ ምግባር ሃይማኖት ናት፡፡
ጌታ ወደ ኢየሩሳሌም የመጣው በአይሁድ ልማድ ነበር፡፡ የጦርነት ዘመን ሲሆን በፈረስ የሰላም ዘመን ሲሆን በአህያ ነገስታቱ በከተማ ይታዩ ነበር፡፡ እነርሱ የጠበቁት በፈረስ የሚመጣ ነበር ነገር ግን በአህያ በትህትና መጣ፡፡ ሐዋርያቱ ጌታ ለምን በአህያ እንደተቀመጠ አላስተዋሉም ነበር፡፡ “ደቀ መዛሙርቱም ይህን ነገር በመጀመሪያ አላስተዋሉም፤ ነገር ግን ኢየሱስ ከከበረ በኋላ በዚያን ጊዜ ይህ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈ ይህንም እንዳደረጉለት ትዝ አላቸው” ዮሐ.12፤16
ሌላው ምክንያት ትንቢቱን ሊፈጽም “ለጽዮን ልጅ፦ እነሆ፥ ንጉሥሽ የዋህ ሆኖ በአህያ ላይና በአህያይቱ ግልገል በውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል በሉአት ተብሎ በነቢይ የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆነ” የሚል ትንቢት ስላለ። ዘካ 9.4
“ብዙ ሰዎችም ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉ፥ ሌሎችም ከዛፍ ቅጠሎችን እየቈረጡ ያነጥፉ ነበር” ማቴ.21፤8 ልብስ “የሐዋርያት የሥነ ምግባር ትምህርት፣ የቅዱሳት መጽሕፍት ምስጢር ነው" ቅዱስ ጄሮም፡፡ የቅዱሳት መጻሕፍት ምስጢር የሚመች ነው፡፡ ልብስ መጀመሪያ ያነጠፉት ሐዋርያት ሲሆኑ ከዚያ ሕዝቡ ተከተለ፡፡ መሪ ማለት ራሱ ሰርቶ ሌላው እንዲሰራ አብነት መሆን ስላለበት፡፡ ልብስ ከማንጠፍ ባሻገር ከመንገድ ላይ እንቅፋት የሚሆነውን ድንጋይ አነሱ፡፡
ወቅቱ ለምለም ነበር፡፡ እነዚያ ዛፎች ፍሬ የሚያፈሩ ነበሩ “አንተ የሕይወት ፍሬ ሆነህ መጥሀል” ሲሉ ነው፡፡ “በአጋንንት ላይ ድልን ተቀዳጅቶ በአህዛብ ላይ ስለሚነግሥ” ይህንን አደረጉ፡፡ “የዘንባባ ዛፍ ዝንጣፊ ይዘው ሊቀበሉት ወጡና፦ ሆሣዕና፤ በጌታ ስም የሚመጣ የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው እያሉ ጮኹ” ዮሐ.12፤13፡፡ ሐዋርያት ዝማሬውን ጀመሩ ሕዝቡ ተቀበለ፡፡ዝማሬው አይሁድ ከሚዘምሩት የዳዊት መዝሙር የተወሰደ ነበር፡፡ መዝ.118፡25
በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፡፡ ስለ እግዚአብሔር እየተናገረ የሚመጣ የተባረከ ነው፡፡ አሁን የመጣው የእግዚአብሔር አንድያ ልጁ እግዚአብሔር ሆኖ መጣ፡፡ዮሐንስ አፈወርቅ “ ራሱ ሰው ሆኖ መጣ” ይላል
ዘንባባ በዮሐንስ አፈወር ትርጉም፦የድል ምልክት (ምሳሌ) ሲሆን ከግብጽ ሲወጡ ይዘውት ነበር፤ በክረምትም በበጋም አይደርቅም ዘላለማዊ ንጉሥ ነህ ሲሉት ነው፡፡ ጫፉ ላይ እሾህ አለው ፡፡ ኃይለ መዊዕ አለህ ሲሉት፡፡ በዚህ እለት ዝማሬ “መለኮታዊ ሥልጣን ታወጀ ፣ መሲህ መሆኑ ተገለጠ”
እነርሱ በሚጠብቁት በመሲህነት መንገድ መጣ፡፡ መዝሙሩ ተራ አልነበረም፡፡ለመሲህ ብቻ የሚዘመር ነው፡፡መሲሁን የሚጠብቁት ግን ጦር አሰልፎ ከሮማውያን አገዛዝ ነጻ እንደሚያወጣቸው አስበው ነው፡፡ የሮማውያን ወታድሮች ከከተማ ወጥተው እስራኤል ነጻ ሐገር ስትሆን በዓይነ ኅሊናቸው ተመለከቱ፡፡ ሕዝቡ ነጻነት የሚያገኙበት ጊዜ እንደደረሰ አመኑ፡፡ “አንቺ የጽዮን ልጅ አትፍሪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ በአህያ ውርንጫ ላይ ተቀምጦ ይመጣል ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ኢየሱስ የአህያ ውርንጫ አግኝቶ በእርሱ ተቀመጠ” ዮሐ.12፡14
«አንች የጽዮን ልጅ አትፍሪ፤ እነሆ ንጉሥሽ በእህያ ውርንጫ ላይ ተቀምጦ ይመጣል» ተብሎ እንደተጻፈ ኢየሱስ የአህያ ውርንጫ አግኝቶ በእርሱ ተቀመጠ ዮሐ.12፥15፡፡
በቤተ ክርስቲያናችን ከሚከበሩ ፱ኙ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆነውን የሆሳዕና በዓል ሰ/ት/ቤቶች በጋራ ሆነው ለማክበር ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል።
በመሆኑም ነገ ሚያዚያ ፩ ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ ከ22 አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች የተውጣጡ የሰ/ት/ቤት ሕጻናት ክፍል አባላት በሆሳዕና አንድነት አስተባባሪ ኮሚቴ ወደ ሐመረ ኖኅ እንጦጦ ኪዳነ ምህረት በመጓዝ በዓሉን ከትውልድ ወደ ትውልድ በተጠናከረ አከባበር በዓደባባይ ለማክበር የሚደረገውን ሥራ በሚያስፋፋ መልኩ የሚከናወን ይሆናል።
መርሐ ግብሩን በመገኛት እና በቀጥታ ስርጭት እንድትከታተሉ (https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg) ተጋብዛችኋል።
"ኒቆዲሞስ"
የዐቢይ ጾም ሰባተኛው ሳምንት ኒቆዲሞስ ይባላል። ስያሜውን ያገኘው እውነተኛ እውቀትንና ሕይወትን ፈልጎ ነገር ግን ምድራዊ ሥልጣኑን በአይሁድ ሸንጎ እንዳይነጠቅ ፈርቶ በሌሊት ወደ ጌታ እየሄደ ይማር ከነበረው ከአይሁድ አለቃ ከኒቆዲሞስ ነው።
ዳግም ልደትን በተመለከተ ኒቆዲሞስ የጠየቀው ጥያቄና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመለሰው መልስ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 3 ላይ በሰፊው ተብራርቶ ተጽፏል።
ኒቆዲሞስ በፍርሃት ተውጦ እየተደበቀ በሌሊት ብቻ ኢየሱስ ክርስቶስን ሲከተለው የነበረ ሲሆን በኋላ በቃሉ ተመስጦና በፍጹም ፍቅሩ ተስቦ በድፍረት ተከትሎታል። የኢየሩሳሌም ሸንጎ ኢየሱስን ሊከሰው ሲፈልግ ኒቆዲሞስ ግን መከሰስ እንደሌለበት በድፍረት ሲመሰክር እናየዋለን (ዮሐ 7፥45-52)።
በተጨማሪም ኢየሱስ ክርስቶስ ከተሰቀለ በኋላም ሌሎች ደቀ መዛሙርት በፍርሃት ተውጠው ሲሸሹ እርሱ ለመግነዝ የሚሆን መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ በድፍረት በቦታው ሲገኝም እንመለከተዋለን (ዮሐ 19፥39)።
የዘለዓለም ሕይወትን መውረስ የሚፈልግ ሁሉ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ከውኃና ከመንፈስ ዳግመኛ መወለድ እንዳለበት የዮሐንስ ወንጌል ምዕ 3 ያስተምረናል።
ክርስቶስ " ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው " ብሏል።
የመጀመሪያው ልደት ከእናትና አባት ከሥጋ መወለድ ሲሆን ዳግም ልደት ደግሞ ከመንፈስ ቅዱስ የመወለድ ምሥጢር ነው። ይህ ደግሞ በሰው ኃይል ሳይሆን በእግዚአብሔር ኃይል ነው የሚሆነው።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ ያስተማረው ዘለዓለማዊ ሕይወት የሚገኝበት ዳግም ልደት ለእኛም ጭምር የተነገረ መሆኑን ከልብ ልናስተውል ይገባል። ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ሕያውና ዘለዓለማዊ ነው።
ጠቅለል ባለ መልኩ" ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው" (1ኛ ጢሞ 1፥15) ብሎ ሐዋርያው እንደተናገረው ክርስቶስ የከፈለልንን የደም ዋጋ ከልብ በማመንና ዘወትር ያለማቋረጥ ፍቅሩንና ቤዛነቱን በማሰብ በፍርሃትና በሌሊት ሳይሆን በፍጹም እምነትና በብርሃን ልንከተለው ይገባል።
የዳግም ልደት ዋናው ጽንሰ ሐሳብም ለምድራዊው ሥልጣንና ሀብት ቅድሚያ በመስጠት በሥጋ ልደት ጸንቶ መኖር ሳይሆን ለዘለዓለማዊ ሕይወት ቅድሚያ በመስጠት ዳግም ከመንፈስ ቅዱስ በመወለድ ሰማያዊ ዜግነትን ማግኘት ነው።
ከአ/አበባ ሃገረ ስብከት ቴሌግራም ገጽ የተወሰደ።
⚜💫🌺⚜💫🌺⚜💫🌺💫⚜🌺⚜🌺⚜💫🌺💫⚜🌺💫⚜🌺⚜🌺
"ለፍቅር እና ለመልካም ሥራ እንድንነቃ እርስ በእርሳችን እንተያይ" (ዕብ 10÷24)
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የየሰንበት ት/ቤቶች ሥራ አመራር አባላቶች በተገኙበት ከመጋቢት 16-17/2015 ዓ.ም ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ጠቅላላ ጉባዔ ተጠናቀቀ !!!
መጋቢት 17/2015 ዓ.ም
ጉባዔው ከመጋቢት 16-17/2015 ዓ.ም ለሁለት ቀናት የተካሄደ ሲሆን በመጀመሪያ ቀን ውሎው የ2015 ዓ.ም ግማሽ በጀት ዓመት ዕቅድ እና የትኩረት አቅጣጫዎች ቀርበው ከጉባዔው ተሳታፊዎች አስተያየቶች ቀርበው ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። በመዋቅራዊ አሠራሮች ፤ ሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት እና ትግበራ ፤ የሚዲያና ቴክኖሎጂ አገልግሎት ፤ ዕቅድ መረጃ እና ግንኙነት ዙሪያም ትኩረቱን ያደረገ ገለጻ ተደርጎ ከጉባዔው ታዳሚዎች አስተያየት ተሰጥቶበታል።
ጉባዔው በሁለተኛው ቀን የስብሰባ ውሉውም ብጹዕ አቡነ ፊሊጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት እንዲሁም የየሰንበት ት/ቤቱ የሥራ አመራር አባላቶች የተገኙ ሲሆን የኦርቶዶክሳውያን የኢኮኖሚ ትብብር በሚል ርዕስ የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሰብሳቢ በሆኑት በላዕከ ኄራን መንክር ግርማ ጥናታዊ ጽሑፍ የቀረበ ሲሆን በጥናቱ ዙሪያ በግሩፕ ውይይት ተደርጓል።
በመቀጠልም በከሰዓት በኃላ በነበረው መርሐ ግብሩ ላይ ብጹዕ አቡነ ፊሊጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ወቅታዊ ጉዳይን በተመለከተ ሰፊ ዳሰሳዊ ጥናት አቅርበዋል። በተጨማሪም በዚሁ ወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ በመምህር በላይ ተጨማሪ ጥናቶች እና የመፍትሔ አቅጣጫዎች ተጠቁመዋል።
በጉባዔው ማጠናቀቂያ ላይም ጠቅላላ ጉባዔው በሁለት ቀናት ውሎው በተወያየበት መሠረት 10 ነጥቦች የያዘ የአቋም መግለጫ በማውጣት ጉባዔው በጸሎት ተጠናቋል።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
የ2015 ዓ.ም 1ኛ ጠቅላላ ጉባኤ የአቋም መግለጫ!!!
1.ከመጋቢት 16 እስከ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ለጠቅላላ ጉባኤው የቀረበውን ሪፖርት ጉባኤው ተቀብሎ አጽድቆታል፡፡በቀጣይ በትኩረት አቅጣጫነት የተቀመጡ ነጥቦች እንዲሳኩ በጋራ እንሰራለን፡፡
2.እኛ ሰንበት ት/ቤቶች የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መዋቅራችን ውጤታማ እንዲሆን በሰው ኃይልና በፋይናንስ እንዲጠናከር የበኩላችንን አስተዋጽዖ በአንድነቱ ተወስኖ በሚሰጠን መመሪያ መሰረት ለመፈጸም ቃል እንገባለን፡፡
3.ከአጥቢያ እስከ ሃገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ያለውን መዋቅራችንን ለማጠናከር በሁሉም የአገልግሎት እርከን መደበኛ አገልጋዮችን በመቅጠር አንድነቱ እንዲጠናከር እንሰራለን፡፡ለሰንበት ት/ቤቶች መጠናከር እና መናበብ እንዲረዳ ሰ/ት/ቤቶች በተመሳሳይ ጊዜ ምርጫ የሚያደርጉበት አሰራር ተጠንቶ እንዲተገበር ተስማምተናል፡፡
4.የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ሙሉ ለሙሉ እንዲሳካ ሥርዓተ ትምህርቱን በአጥቢያችን በአጥቢያችን እንዲተገበር እናደርጋለን፡፡የአተገባበር ሂደቱንም አንድነቱ በጥብቅ እንዲከታተል እንጠይቃለን፡፡
5.የሰንበት ት/ቤቶች እንዲሁም የአንድነቱ አገልግሎት በላቀ ሚዲያና ቴክኖሎጂ እንዲመራ እንሰራለን፡፡ለተግባራዊነቱም በሙሉ ተገቢውን ድጋፍ እናደርጋለን፡፡
6.የኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች በኢኮኖሚ መተሳሰርና ማደግ ለቤተክርስቲያን የሚሰጠውን ሁሉን አቀፍ አቅም እንገነዘባለን፡፡በመሆኑም አንድነቱ በዚህ ዘርፍ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት እያደረገ ያለውን ጥረትና ትጋት እንዲቀጥልበት ወስነናል፡፡
7.ኦርቶዶክሳውያን፣የሰንበት ት/ቤት አባላት፣የአባላት ወላጆች የኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚሆኑባቸውን የሥራ ዘርፎችና የፋይናንስ እድሎች በማጥናት የቀረቡ ምክረ ሃሳቦችን በማድነቅ ያለምንም መሸራረፍ የተቀበልነው ሲሆን ተሳክተው ውጤት እስኪገኝባቸው በጽናትና በትጋት እንሰራለን፡፡
8.ወቅታዊ የቤተክርስቲያን ፈተናዎችን በአግባቡ ተገንዝበናል፡፡ቤተክርስቲያናችን ከገጠሟት ፈተናዎች መውጣት እንድትችል አንድነቱ ከቅዱስ ሲኖዶስና ከብጹዓን አባቶቻን ጎን በመሆን እያደረገ ያለው አስተዋጽዖን እጅጉን አድንቀን ተቀብለናል እንዲቀጥልበትም በአጽንዖት እንጠይቃለን፡፡
9.ከወቅታዊው የቤተክርስቲያን ፈተና ለመውጣት የቤተክርስቲያን መዋቅር እንዲከበር፣ በቃለ አዋዲ ለካህናት፣ለምዕመናንና ለሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የአስተዳደር የተሰጡ ተሳትፎዎች በአግባቡ ከአጥቢያ እስከ ጠቅላይ ቤተክህነት እንዲተገበሩ እንጠይቃለን፡፡ለዘላቂ መፍትሔ መሳካት የተቋቋሙ ዐቢይና ንዑሳን ኮሚቴዎች እያደረጉት ያለው ጥናትና የትግበራ አማራጭ መፍትሔ የማምጣት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እየጠየቅን፡፡ በቤተክርስቲያናችን እየታዩ ያሉ ብልሹ የአስተዳደር አሰራሮችና በየአካባቢው የሚደረጉ የቤተክርስቲያንን ቀኖናዊ አንድነት የሚጥሱ እንቅስቃሴዎችን ለማስቆም ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ጠቅላይ ቤተክህነት ባለው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መዋቅር በቁርጠኝነት እንሰራለን፡፡
10.ዛሬ በዚህ ጠቅላላ ጉባኤ የተወያየንባቸውንና የተወሰኑ ውሳኔዎችን በሰንበት ት/ቤቶቻችን ጠቅላላ ጉባኤ በ1ወር ጊዜ ውስጥ በማስገንዘብ ሁሉም አባል ለተግባራዊነቱ እንዲሰራ እናደርጋለን፡፡
#የአዲስ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት
⚜💫🌺⚜💫🌺⚜💫🌺💫⚜🌺⚜🌺⚜💫🌺💫⚜🌺💫⚜🌺⚜🌺
#የሁለቱ_ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት #ሥርዓተ_ቀብር_ተፈጸመ
የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ እና የብፁዕ ዶ/ር አቡነ አረጋዊ ሥርዓተ ቀብር ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የሌሎች እምነት ተቋማት መሪዎች እንዲሁም
ወዳጅ ዘመዶቻቸውና ቤተሰቦቻቸው በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ተፈጽሟል
“መኑ ውእቱ ገብር ኄር” ? ማቴ.24፥45
የዐቢይ ጾም ስድስተኛው እሑድ ወይም ሳምንት ገብር ኄር ይባላል፡፡ ሰያሜውን የሰጠውም ኢትዮጵያዊ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ ከአምስቱ መጻሕፍቶቹ አንዱ በሆነው ጾመ ድጓ መጽሐፍ የዐቢይ ጾም ሳምንታት ስያሜዎች ከነሥርዓተ ማኅሌቱ አዘጋጅቷል፡፡ ስለዚህ በስድስተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት ከዋዜማው ቅዳሜ ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን፡- የሚዘመረው ዝማሬ፣ የሚሰበከው ስብከት፣ የሚሰጠው ትምህርት ገብር ኄርን የሚያወሳ ወይም ስለ ታማኝ አገልጋይ ነው፡፡ በማቴ.25፥14-25 የተገለጸውና በዕለቱ የሚነበበው ወንጌልም የሚነግረን ይህን ነው፡፡
“አንድ ባዕለ ጸጋ ሰው ባሪያዎችን ጠርቶ ለአንዱ አምስት መክሊት ሰጠው፣ ሁለት መክሊት የሰጠውም አለ፣ አንድ መክሊትም የሰጠው አለ፡፡ ከዚህ በኋላ ወደሩቅ አገር ሄደ፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለውም ወጥቶ ወርዶ ሌላ አምስት አትርፎ አስር አደረገ፡፡ ሁለት የተቀበለውም አትርፎ አራት አደረገ፡፡ አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ መሬቱን ቆፍሮ በሻሽ ጠቅልሎ የጌታውን መክሊት ቀበራት፡፡
ከብዙ ጊዜ በኋላ ጌታቸው መጥቶ ተቆጣጠራቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለው ቀርቦ ጌታዬ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር እነሆ አምስት አተረፍኩ አለው፡፡ “ገብር ኄር ወምዕመን ዘበሁድ ምዕምነ ኮንከ ዲበ ብዙህ እሰይመከ ባዕ ውስተ ፍስሐሁ ለእግዚእከ” “አንተ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው፡፡ ሁለት የተቀበለውም ቀርቦ ጌታዬ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር እነሆ ወጥቼ ወርጄ ሌላ ሁለት አትርፌ አራት አድርጌአለሁ፡፡ “አንተ ታማኝ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው፡፡
አንድ መክሊት የተቀበለው ግን ቀርቦ “ጌታዬ አንተ ክፉና ጨካኝ ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህበት የምትሰበስብ እንደሆንክ ስለአወቅሁ መሬቱን ቆፍሬ ቀበርኋት እነኋት መክሊትህ” አለው፡፡ “አንተ ሰነፍ ባሪያ መክሊቴን በጊዜ ልትሰጠኝ በተገባህ ነበር እኔም ወጥቶ ወርዶ ለሚያተርፍ በሰጠሁት ነበር”፡፡
ኑ የዚህን ሀኬተኛ መክሊት ውሰዱና አስር መክሊት ላለው ስጡት፡፡ ላለው ይሰጡታል ይጨመርለታል ለሌለው ግን ያለውን ይቀሙታል፡፡ ንዑ ይህን ሰነፍና ሃኬተኛ ባሪያ እጅ እግሩን አሥራችሁ ጽኑዕ ጨለማ ወደአለበት ውሰዱት ጩኸትና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ጨምሩት” አለ ማቴ.25፥14-25፡፡
ባዕለ ጸጋ የተባለው ጌታ ነው፡፡ መክሊት የተባለው ልዩ ልዩ የአገልግሎት ጸጋ ነው፡፡ ያተረፉት በሚገባ በታማኝነት ያገለገሉ ቅዱሳን ሰዎች ናቸው መክሊቱን የቀበረው ደግሞ በታማኝነት በተሰጠው ጸጋ ማገልገል ሲገባው ያላገለገለ ነው፡፡ ጌታቸው ሊቆጣጠራቸው መጣ ማለት በዕለተ ምጽአት ለሁሉም በአገለገለው አገልግሎት ዋጋ ለመስጠት እንደሚመጣ ያሳየናል፡፡
ያገለገሉትን ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አላቸው ማለት ታማኝ አገልጋዮች መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉና፡፡ ሰነፎች ደግሞ ጥርስ ማፋጨት ስቃይ ጽኑዕ ጨለማ ባለበት ሲዖል መግባታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
ከላይ ያነሳነው የቅዱስ ወንጌል ቃል፡- “ታማኝ አገልጋይ ማነው”? ይህ እያንዳንዱ በአርዓያ እግዚአብሔር የተፈጠረ የሰው ልጅ ጥያቄ ነው የዚህን አምላካዊ ጥያቄ መልስ መስጠት ከሰው ልጆች ይጠበቃል፡፡
ሁላችንም በተሰጠን ጸጋ ታማኝ ሆነን እንድናተርፍና ወድ መንግስቱ እንድንገባ እግዚአብሔር ያበርታን።
ዛሬ ምሽት 2፡00 ላይ በEOTC TV ፈለገ ጥበብ የቴሌቭዥን መርሐ ግብር ላይ ይጠብቁን!
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
"የሕገ ወጥ ቡድኑን የሹመት ይጽደቅልን" ጥያቄን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መቼውንም የማትቀበለው ጥያቄ ነው"።
የመንበረ ፓትርያርክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በዛሬ ዕለት የተካሔደውን በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና በሕገ ወጥ መንገድ በተሾሙ የቀድሞ አባቶች መካከል የነበረውን ውይይት አስመልክተው መግለጫው የሰጡት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሓላፊ ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገብረ ክርስቶስ ሲሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ከመጋቢት ፮/፳፻፲፭ ዓ/ም ጀምሮ በሕገ ወጥ የተሾሙ ግለሰቦችን አስመልክቶ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ለመቀበል ያከናወነውን ተግባራት አብራርተዋል።
በዚህም ቅዱስ ሲኖደስ በቀኖና ቤተ ክርስቲያንና ከሕገ ወጥ የተሾሙ ግለሰቦች በአምስት የሥራ ቀናት ውስጥ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ጽ/ቤት የይቅርታ መመልከቻ እንዲያስገቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ ያስተላላፈ ቢሆንም በይቅርታ ደብዳቤ አስገብተው ከተመለሱት ከአንዱ " አባ " ኃይለ ኢየሱስ ከተባሉት ውጭ ሌሎች ግን በይቅርታ ከመመለሰ ይልቅ ለውይይትና ሕገ ወጥ ድርጊቱም እንዲጸድቅላቸው መጠየቃቸውን ተገልጿል።
የመምሪያው ኃላፊ ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገብረ ክርስቶስ ቀጥለው ቤተ ክርስቲያን የይቅርታ ቤት የሰላም ዓደባባይ የንስሓ ሰገነት በመሆኗ ለፍቅር ረጅም ርቀት በመጓዝ ግለሰቦቹ ጋር በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ እንዲሁም በሌሎች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አማካኝነት መወያያቷን አስታውሰዋል። ከዚህም አልፎ ቤተ ክርስቲያን የሀገር ሰላም የኢትዮጵያውያን የደኅንነት ኑሮ በእጅጉ ስለሚያሳስባት በብዙ ርቀት ለይቅርታ በሯን ከፍታ ስትጠባበቅ እንደነበረችም አክለው ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ በዛሬው ዕለት ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ የመጡት ሁሉንም እንወክላለን ያሉት 6 ግለሰቦች ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና ከብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ ጋር የተወያዩ ሲሆን በውይይቱ ግን የተዘረጋው የቤተ ክርስቲያን የፍቅርና ይቅርታ እጅ በግለሰቦቹ ግን እንደመልካም አልታየም። ከዚህ ይልቅ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት ከተደረሱ 10 የስምምነት ነጥቦች መካከል በተራ ቁጥር 6 የሚገኘው ውሳኔ "በሕገ ወጥ መንገድ የተሾሙት "አባቶች" ወደ ቀደመ አገልግሎታቸው ይመለሳሉ" የሚል ቢሆንም ግለሰቦቹ ግን በመርሕ ደረጃ ስምምነቱን እንቀበለዋለን በአፈጻጸም ደረጃ ግን ቅዱስ ሲኖዶስ ሹመታችንን ያጽድቅልን" የሚል ጥያቄ ማቅረባቸውን የመምሪያው የሓላፊ ገልጸዋል።
ስለሆነም ይላሉ የመምሪያው ሓላፊ ቤተ ክርስቲያን እስካሁን የሄደችበት የይቅርታ መንገድ እጅግ የሚያስመሰግን ሲሆን ከዚህ በኋላ ሕገ ወጦቹን በተመለከተ ቤተ ክርስቲያን የሚከተለውን ውሳኔ መወሰኗን አስታውቀዋል።
፩.በየትኛውም መንገድ የጋራ ውይይት አይኖርም
፪.ለይቅርታ የሚመጡ ከሆነ በቡድን ተሰባስቦ ሳይሆን በግለሰብ ደረጃ እንዲሆን
፫.የይቅርታ ማመልከቻውን እያንዳንዳቸው ለመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዚህና በሌሎች መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ለማሳለፍ መጋቢት ፳፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም (21/07/2015 ) ምልዓተ ጉባኤ መጠራቱ የሚታወስ ነው።©Eotc tv
የዲና መንገድ
"ያዕቆብም ከአጎቱ ከላባ ዘንድ ወጥቶ በከነዓን ምድር ወዳለችው ወደሴኬም ከተማ በደኅንነት መጣ፤በከተማዪቱም ፊት ሰፈረ።ድንኳኑንም ተክሎበት የነበረውንም የዕርሻውን ክፍል ከሴኬም አባት ከኤሞር ልጆች በመቶ በጎች ገዛው። ለያዕቆብ የወለደችለት የልያ ልጅ ዲናም የዚያን አገር ሴቶች ልጆችን ለማየት ወጣች።የኤሞር ልጅ ሴኬም አያት ወሰዳትም ከእርሷም ጋር ተኛ አስነወራትም" (ዘፍ 30÷1)
በዚህ ታሪክ ውስጥ የዲናን መንገድ ስንመለከት ከሁለት ስሕተት አንድ መጥፎ ውጤት እናገኛለን፦
አንደኛ ማየት የሌለባትን ተመለከተች፦ የዲና የመጀመሪያ ጥፋት ማየት የሌለባት የዚያን አገር ሰዎች መመልከቷ ነው። እግዚአብሔርን የማያውቁ ፈሪሃ እግዚአብሔር የሌላቸውን ሰዎች። ዛሬም የብዙዎቻችን ችግር መመልከት ያለብን ትተን መመልከት የሌለብንን መመልከታችን ነው። ዲና ከዚያ አገር ሰዎች ይልቅ መመልከት የምችላቸው የተሻሉ አራያ የሚሆኑ ሰዎች ነበሩ። እግዚአብሔርን የሚያመልክ ቤተሰብ ነበራት ከዚያ አገር ሰዎች ይልቅ መመልከት የምችላቸው ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸው ወገኖች ነበሯት።
እኛም አርአያ ምሳሌ የሚሆኑን ቅዱሳን አንስት በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሱ እና መማር የምንችልባቸው እያሉን ማየት የሌለብን ግብረገብ የጎደላቸውና ፈሪሃ እግዚአብሔር የሌላቸውን እየተመለከትን የዲናን መንገድ የምንጓዝበት ጊዜ ጥቂት አይደለም።
ሁለተኛ መከተል የሌለባትን ተከተለች፦ ሁለተኛ የዲና ስሕተት ደሞ መከተል የሌለባትን ሴኬምን ተከትላ መሄዷ ነው። እግዚአብሔርን ከሚፈራ እና ከሚያመልክ ቤተሰብ ወጥታ ሳለ ዲና ግን ያልተገረዘውን እግዚአብሔርን የማያውቀውን ሴኬምን ተከትላ ሄደች።
ሁልጊዜ ጥፋት የሚጀምረው እንዲህ ነው መከተል የሌለብን መከተል ስንጀምር ማመን የሌለብን አምነን ስንከተል ያኔ ጥፋት ሁሉ ይጀምራል። በሕይወታችን ሁሉ የሚመጣ ሰው ስለወደደን መከተል አለብን ማለት አይደልም። ነገሮችን ልንመረምርና ልናስተውል ይገባል። ሕይወታችን ውስጥ ያለው ማነው? ዓላማው ምንድነው? እምነቱስ? ብለን ልናጤን ይገባል ያለዚያ ግን መንገዳችን የዲና አይነት መንገድ መሆኑ የማይቅር ነው።
ከዚህ ሁሉ የስህተት ጉዞ በኋላ የዲና ስሕተቶች መጨረሻ ከክብር ማነስ ነበር፡፡ ማየት የሌለባትን የዚያን አገር ሰዎች ተመለከተች መከተል የሌለባትን ሴኬምን ተከተለች በመጨረሻ ክብሯን አጣች።
በሕይወታችን ውስጥ የምንመለከተው ነገር ለነገ መልካምም ይሁን ጠማማ የሕይወታችን ጉዞ ትልቅ ተጽዕኖ አለው። ታዲያ ማንን ነው እየተመለከትን ያለነው? ማንንስ ነው እየተከተልን ያለነው?
በመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንመለከተው "ንጉሡም ከሴቶች ኹሉ ይልቅ አስቴርን ወደደ ፥በዐይኑም ከደናግል ኹሉ ሞገስንና መውደድን አገኘች፤ የመንግሥቱንም ዘውድ በራሷ ላይ አደረገ" (መጽሐፍ አስቴር ፪፥፲፯) ይላል። አስቴር ክብሯን የጠበቀች ናትና ማንን መስማት ማንን መከተል እንዳለባት ጠንቅቃ ታውቅ ነበርና በንጉሥ ፊት ሞገስን አገኘች።
ክብርን መጠበቅ ያስመርጣል። አስቴር በንጉስ ዘንድ ሞገስን ማግኘቷ ክብሯን በመጠበቋ ነው። ክብርን መጠበቅ ያሸልማል። አስቴር ዘውድን ያስሸለማት በንጽህና ክብሯን ጠብቃ በመኖሯ ነው።
ክብር መጠብቅ እንደሚገባ በሰፊው የምታስተምረን ቅድስት ቤተክርስቲያን የአስቴርን መንገድ ተከትለው ክብራቸውን ለጠበቁ ሴቶች የድንግልናቸውን ዋጋና ሽልማት ይሆናቸው ዘንድ በሰማዕትነት ቆጥራ በጋብቻቸው ወቅት አክሊልን ትሸልማቸዋለች።
ስለዚህ ሁልጊዜም በሕይወታችን የምንሄድበትን መንገድ መመልከት ይኖርብናል ድንገት አካሄዳችን የዲና መንገድ ከሆነ ቆም ብለን ልናስተውል ይገባል። ማየት ያለብን እንድንመለከት መከተል ያለብንን እንድንከተል መጠበቅ ያለብን እንድንጠብቅ እግዚአብሔር ይርዳን።
“ሴቶች ሆይ አስቴርን እንምሰላት “
✍️ቤተልሔም ታምራት
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
