ch
Feedback
Ethiopian Coffee Sport Club - Team Page

Ethiopian Coffee Sport Club - Team Page

前往频道在 Telegram

Professional Sport club

显示更多
4 781
订阅者
+124 小时
-47 天
-4130 天
帖子存档
#የካፍ_ኮንፌዴሬሽን_ዋንጫ_የማጣሪያ_ጨዋታ 12' ኬንያ ፖሊስ 0~0 የኢትዮጵያ ቡና 🗓 እሁድ ነሐሴ 12/2016 ዓ.ም 🕛 ቀን 9:00 ሰዓት 🏟 በንያዮ ብሔራዊ ስታዲየም 🎯 ድል ለታላቁ የኢትዮጵያ ቡና‼

#የካፍ_ኮንፌዴሬሽን_ዋንጫ_የማጣሪያ_ጨዋታ ⚽ ኬንያ ፖሊስ ከ የኢትዮጵያ ቡና 🗓 እሁድ ነሐሴ 12/2016 ዓ.ም 🕛 ቀን 9:00 ሰዓት 🏟 በንያዮ ብሔራዊ ስታዲየም 🎯 ድል ለታላቁ የኢትዮጵያ ቡ
#የካፍ_ኮንፌዴሬሽን_ዋንጫ_የማጣሪያ_ጨዋታ ⚽ ኬንያ ፖሊስ ከ የኢትዮጵያ ቡና 🗓 እሁድ ነሐሴ 12/2016 ዓ.ም 🕛 ቀን 9:00 ሰዓት 🏟 በንያዮ ብሔራዊ ስታዲየም 🎯 ድል ለታላቁ የኢትዮጵያ ቡና‼

የኬኒያ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቡና ጨዋታ በዋነኝነት የክለቡ ኦፊሻል የ Facebook ገፅ እንደሚያስተላልፈው ማረጋገጥ ችለናል። https://www.facebook.com/share/eNtcrSTCkoRhv3ra/?mibextid=qi2Omg

⚽ ኬንያ ፖሊስ ከ የኢትዮጵያ ቡና 🗓 እሁድ ነሐሴ 12/2016 ዓ.ም 🕛 ቀን 9:00 ሰዓት 🏟 በንያዮ ብሔራዊ ስታዲየም 🎯 ድል ለታላቁ የኢትዮጵያ ቡና‼
⚽ ኬንያ ፖሊስ ከ የኢትዮጵያ ቡና 🗓 እሁድ ነሐሴ 12/2016 ዓ.ም 🕛 ቀን 9:00 ሰዓት 🏟 በንያዮ ብሔራዊ ስታዲየም 🎯 ድል ለታላቁ የኢትዮጵያ ቡና‼

የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ በአሁኑ ሰዓት በንያዮ ስታዲየም ቀለል ያለ ልምምድ በመስራት ላይ ይገኛል። 📸 አብነት ብዙነህ
+6
የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ በአሁኑ ሰዓት በንያዮ ስታዲየም ቀለል ያለ ልምምድ በመስራት ላይ ይገኛል። 📸 አብነት ብዙነህ

የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ በካፍ ኮን ፌዴሬሽን ጨዋታ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታውን ለማድረግ ዛሬ ወደ ናይሮቢ ኬኒያ አቅንቷል። 18 ተጫዋቾች እና 6 የአሰልጣኝ ቡድን አባላትን ያካተተው የኢትዮጵያ ቡ
+2
የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ በካፍ ኮን ፌዴሬሽን ጨዋታ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታውን ለማድረግ ዛሬ ወደ ናይሮቢ ኬኒያ አቅንቷል። 18 ተጫዋቾች እና 6 የአሰልጣኝ ቡድን አባላትን ያካተተው የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ከቀኑ 6:00 ናይሮቢ የደረሰ ሲሆን በተያዘለት weston Hotel ማረፊያውን አድርጓል።

#ዜና_የኢትዮጵያ_ቡና 👉 የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ላለበት የኢንተርናሽናል ጨዋታ እና የ2017 ዓ.ም የውድድር ዘመን ይረዳው ዘንድ መቀመጫውን በአዳማ ከተማ በማድረግ ያለፉት ሦሥት ሳምንታት የ
+1
#ዜና_የኢትዮጵያ_ቡና 👉 የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ላለበት የኢንተርናሽናል ጨዋታ እና የ2017 ዓ.ም የውድድር ዘመን ይረዳው ዘንድ መቀመጫውን በአዳማ ከተማ በማድረግ ያለፉት ሦሥት ሳምንታት የቅድመ-ውድድር ዝግጅቱን እያደረገ እንደሚገኝ ይታወሳል። 👉 የፊታችን እሁድ ነሐሴ 12/2016 ዓ.ም በኬንያ ናይሮቢ ንያዮ ስታዲየም ከኬኒያ ፖሊስ ጋር ላለበት ጨዋታ 18 ተጫዋቾችን እና 6 የአሰልጣኝ ቡድን አባላት በመያዝ የፊታችን ቅዳሜ ከረፋዱ 4:00 ወደ ናይሮቢ ያቀናል። 👉 በኬኒያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ለክለባችን አቀባበል ለማድረግ ዝግጅት እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን በንያዮ ስታዲየም በመገኘትም ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ ከስፍራው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። 👉 ጨዋታው እሁድ ነሐሴ 12/2017 ዓ.ም ቀን 9:00 ሰዓት ላይ የሚደረግ ሲሆን ጨዋታውን በቀጥታ ለመከታተል የሚረዱ አማራጭ ገፆችን መረጃውን እንዳገኘን የምንገልፅ ይሆናል። 👉 ሁለቱ የስፖርት ክለቦች በ #Betika የስፖርት ውርርድ ስፖንሰር ይደረጋሉ። 👉 የመልሱ ጨዋታ ዕሁድ ነሐሴ 19/2016 ዓ.ም ቀን 9:00 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የሚደረግ ይሆናል።

እሁድ ነሐሴ 5/2016 በአዲስ አበባ ስታዲየም ሊከናወን መርሐ ግብር ተይዞለት የነበረው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮጵያ ቡና ጨዋታ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ማም
እሁድ ነሐሴ 5/2016 በአዲስ አበባ ስታዲየም ሊከናወን መርሐ ግብር ተይዞለት የነበረው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮጵያ ቡና ጨዋታ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ማምሻውን በድሀረ-ገፁ አስታውቋል።

#ላለፉት_ሁለት_ዓመታት_ለኢትዮጵያ_ቡና_የተጫወተው_ወልደአማኑኤል_ጌቱ_ውሉን_አድሷል። ያለፈውን የውድድር ዓመት 1215 ደቂቃዎች በሜዳ ላይ ቆይታ ያደረገው ወልደአማኑኤል ጌቱ፤ የተለያዩ ክለቦች እሱን
+3
#ላለፉት_ሁለት_ዓመታት_ለኢትዮጵያ_ቡና_የተጫወተው_ወልደአማኑኤል_ጌቱ_ውሉን_አድሷል። ያለፈውን የውድድር ዓመት 1215 ደቂቃዎች በሜዳ ላይ ቆይታ ያደረገው ወልደአማኑኤል ጌቱ፤ የተለያዩ ክለቦች እሱን ለማስፈረም ፍላጎታቸውን ቢያሳዩም ለተጨማሪ ሁለት ዓመታት ለኢትዮጵያ ቡና ቅድሚያ በመስጠት ለመጫወት ውሉን አራዝሟል።

#ዜና_የኢትዮጵያ_ቡና 👉 የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ዋናው ቡድን ለ2017ዓ.ም የውድድር ዘመን እና ከፊቱ ለሚጠብቁት የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ እና የካፍ ኮንፌዴሬሽን የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ይረዳው ዘንድ መቀመጫውን አዳማ ከተማ በማድረግ ዝግጅቱን በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ስታዲየም ያደርጋል። 👉"የኔ ደም ለውድ ወገኖቼ ህይወት ነው" በሚል መሪ ቃል የኳስ ሜዳ እና አካባቢው የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች መረዳጃ ዕድር ዛሬ በኳስ ሜዳ አካባቢ የዕድሩ አባላት እና የአካባቢው ማህበረሰብ የደም ልገሳ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። 👉 የኢትዮጵያ ቡና በካፍ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ከኬኒያ ፖሊስ ጋር መደልደሉ ይታወሳል። የመጀመሪያ ጨዋታውን በናይሮቢ ከተማ 15,000 ሰው በሚይዘው ንያዮ (Nyayo) ስታዲየም ነሐሴ 12/2016ዓ.ም ቀን 9:00 ሰዓት የሚደረግ ሲሆን፤ የመልሱ ጨዋታ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ነሐሴ 19/2017 ዓ.ም ይደረጋል። 👉 ለዚሁ ውድድር ይረዳ ዘንድ የአበበ ቢቂላ ስታዲየምን ብቁ ለማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት እንዲሁም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እያደረጉት ያለውን ጥረት በክለባችን እና በደጋፊዎቻችን ስም ከልብ እናመሰግናለን። የ YouTube እና የ Telegram ገፃችንን ይቀላቀሉ 🌐 https://youtube.com/@ethiopiancoffeesportclub?si=obZvhA6q-E_he_fp 🌐 https://t.me/Etcospcl

የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ በ2017 ዓ.ም ላለበት የኢንተርናሽናል፣ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እና የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ጨዋታዎች ጥሩ ተፎካካሪ ለመሆን ከ2016ዓ.ም የውድድር ዓመት አጋማሽ ጀምሮ ውላቸው ከሚጠናቀቅ ተጫዋቾች ጋር ድርድር አስቀድሞ ድርድር መጀመሩ ይታወቃል። ክለባችን የቤት ስራዎቹን ቀድሞ ለመጨረስ ዝግጁ ቢሆንም በተጫዋቾቹ "የዝውውር መስኮቱ ሲከፈት እንንነጋገራለን!!!" የሚል ሀሳቦችን በማቅረባቸው ድርድሮቹን ለመዘግየት ተገደናል። ከዚህም ባሻገር ክለባችን ላለበት ኢንተርናሽናል ጨዋታ ከእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ ጋር በመነጋገር የውድድር መስኮቱ አንድ ሳምንት ቀደም ብሎ እንዲከፈት እና ውላቸው የተጠናቀቁ ተጨዋቾችንና አዲስ ክለባችንን የሚቀላቀሉ ተጨዋቾችን ለማስፈረም ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል። እየተደረገም ይገኛል። በዚህ መነሻነት በክለባችን የአሰልጣኞች ቡድን የታመነባቸው እና ለድርድር ፍቃደኛ ከሆኑ ተጨዋቾች ጋር ድርድር እያደረግን እንደሆነ ይታወቃል።ለዚህም እንዲያግዝ በተቋቋመው ኮሚቴ አማካኝነት በከፍተኛ ምስጢር ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ። በዚህም መነሻነት ውላቸው የተጠናቀቁ እና ለድርድር ፈቃደኛ የሆኑ ተጨዋቾች በተለይም በኢትዮጵያ ቡና ውስጥ የቆዩ ተጫዋቾች ከፍተኛ የደሞዝ እና የጥቅማጥቅም ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ለዚህ ድርድር የተመረጡ ኮሚቴዎችም ከቦርዱ እና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለሙያዎች ጋር በመነጋገር በተለይም ይበልጥ የምንፈልጋቸውን ተጫዋቾችን ለማቆየት ጠንካራ ሥራዎችን እየሰሩ ይገኛሉ። በዚህም መሰረት በልዩነት የምንፈልጋቸው ተጨዋቾች ያቀረቡት የደሞዝ እና የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች የኢትዮጵያ ቡና ካለው በጀት እና አዲስ ተግባራዊ የሆነው ህግ መሰረት ክለባችንን የሚፈትን ሆኗል። ያም ሆኖ ክለባችን ብዙ ርቀቶችን በመጓዝ ተጨዋቾቹ ያቀረቡትን ጥያቄዎች እና አቅማችንን ለማመጣጠን ለመጓዝ ጥረቶችን እያደረገ እና ድርድሩ ባልተቋጨበት ሁኔታ ከእኛ ጋር ገና በድርድር ላይ የነበሩ ተጨዋቾች በሌሎች ክለባት ለመጫወት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ከተለያዩ ድህረ-ገፆች ላይ መመልከት ችለናል። ለማሳያነትም ድርድር እያደረግን ከነበሩት ቀደምት ተጨዋቾች መሐከል አማኑኤል ዮሐንስ እና አብዱልከሪም ወርቁ በማሳያነት እናነሳለን። ኮሚቴው ከተጨዋቾቹ ጋር ባደረገው ተደጋጋሚ ንግግር መነሻነት ለእያንዳንዳቸው ጥቅማጥቅምን ሳይጨምር ያልተጣራ ክፍያ 687,069(ስድስት መቶ ሰማንያ ሰባት ሺ ስልሳ ዘጠኝ) ብር ለመፈፀም ሀሳብ አቅርቦላቸዋል። በዚህም መነሻነት አብዱልከሪም ወርቁ 773,276 መነሻ ብር የተጣራ ክፍያ ጥያቄ አቅርቧልም አማኑኤል ዮሐንስ በተደጋጋሚ ኮሚቴው ያቀረበለትን የደሞዝ መጠን መነሻ አድርጎ የእርሱን ጥያቄ እንዲያቀርብ ቢጠየቅም ትክክለኛ ፍላጎቱን ወይም የደሞዝ መጠን ለማስቀመጥ ፈቃደኛ አልሆነም። ያም ሆኖ አብዱልከሪም ያቀረበውን የገንዘብ መጠን እንዲያስተካክል ክለባችንም ወደ እርሱ ፍላጎት ለመቅረብ የማሰቢያ ጊዜ ለመውሰድ ተስማምተው ተለያይተዋል። አማኑኤል ዮሐንስም የቀረበለትን የደሞዝ መጠን መነሻ በማድረግ የእርሱን ሀሳብ እንዲያቀርብ ከስምምነት ላይ ተደርሶ የነበረ ቢሆንም ከኮሚቴው ሀሳባቸውን ለማወቅ የሚደረጉላቸውን ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪዎች ለመመለስ ፈቃደኛ ሆነው አልተገኙም። ይህ ጥረት እስከ ትናንት ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ቀጥሏል። ሆኖም ተጨዋቾቹ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር የጀመሩትን ድርድር በውል ሳይቋጩ ወደ ሌሎች ክለቦች ማምራታቸውን ማወቅ ችለናል። ሁለቱ ተጨዋቾች ከኢትዮጵያ ቡና ጋር እንዲቀጥሉ ከፍተኛ ፍላጎት ያለን ቢሆንም ወደ ሌላ ክለብ አምርተዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ሁለቱ ተጨዋቾች ለክለባችን የሰጡትን አገልግሎት በክብር የሚያየው መሆኑን እየገለፅን በተጓዙበት ክለብ መልካሙን ሁሉ እንዲገጥማቸው እንመኛለን። በዚህ አጋጣሚ አሁንም ክለባችንን የማጠናከር ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ለማስታወስ እንወዳለን።

#የኢትዮጵያ_ቡና_እና_አሰልጣኝ_ነፃነት_ክብሬ_ውላቸውን_አደሱ በ2014ዓ.ም የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ቡና የተቀላቀሉት አሰልጣኝ ነፃነት ክብሬ ዛሬ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ለአንድ ዓመት የሚያቆያቸውን
+1
#የኢትዮጵያ_ቡና_እና_አሰልጣኝ_ነፃነት_ክብሬ_ውላቸውን_አደሱ በ2014ዓ.ም የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ቡና የተቀላቀሉት አሰልጣኝ ነፃነት ክብሬ ዛሬ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ለአንድ ዓመት የሚያቆያቸውን የውል ስምምነት አድርገዋል። ባለው የውድድር ዘመን ከአሰልጣኝ ኮቫዞቪች ኒኮላ ቡድኑን ተረክበው በፕሪሚየር ሊጉ 3ኛ ሆነው የጨረሱ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቡናን ሻምፒዮን ማድረግ ችለዋል። የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ ነፃነት ክብሬ በ2017 ዓ.ም ክለባችን ላለበት ኢንተርናሽናል እና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጠንካራ ቡድን ገንብተው እንደሚመጡ እያመነ ፤ ከወዲሁ ከስራ ባልደረቦቻቸው እና ተጫዋቾቻቸው ጋር የኢትዮጵያ ቡና ወደ ስኬት እንደሚወስዱት በመተማመን ነው። መልካም የስራ ጊዜ!!

#ስም ፦ ዳዊት ሽፈራው #ቀድሞ_የተጫወተበት_ክለብ፦ 👉 ወሊሶ ከተማ (2013-2014) 👉 ጉለሌ ክ/ከተማ (2015) 👉 ቢሾፍቱ ከተማ (2016) #የሚጫወትበት_ቦታ፦ የመስመር አጥቂ #ቁመት፦ 1
+3
#ስም ፦ ዳዊት ሽፈራው #ቀድሞ_የተጫወተበት_ክለብ፦ 👉 ወሊሶ ከተማ (2013-2014) 👉 ጉለሌ ክ/ከተማ (2015) 👉 ቢሾፍቱ ከተማ (2016) #የሚጫወትበት_ቦታ፦ የመስመር አጥቂ #ቁመት፦ 1.77m #ኪሎ፦ 65kg በኢትዮጵያ ቡና የሚቆየው፦ 3 ዓመት እንኳን ወደ ታላቁ የኢትዮጵያ ቡና መጣህ‼

#ስም ፦ ኦካይ ጁል #ቀድሞ_የተጫወተበት_ክለብ፦ 👉 ጉለሌ (2013-2014) 👉 ለገጣፎ ለገዳዲ (2015) 👉 አላባ ከነማ (2016) #የሚጫወትበት_ቦታ፦ የአማካኝ ተከላካይ #ቁመት፦ 1.79m
+3
#ስም ፦ ኦካይ ጁል #ቀድሞ_የተጫወተበት_ክለብ፦ 👉 ጉለሌ (2013-2014) 👉 ለገጣፎ ለገዳዲ (2015) 👉 አላባ ከነማ (2016) #የሚጫወትበት_ቦታ፦ የአማካኝ ተከላካይ #ቁመት፦ 1.79m #ኪሎ፦ 70kg በኢትዮጵያ ቡና የሚቆየው፦ 3 ዓመት እንኳን ወደ ታላቁ የኢትዮጵያ ቡና መጣህ‼

#ስም ፦ እስራኤል ሻጎሌ #ቀድሞ_የተጫወተበት_ክለብ፦ 👉 አርባምንጭ ከተማ (2011-2012) 👉 ነገሌ አርሲ (2014-2015) 👉 ባቱ ከነማ (2016) #የሚጫወትበት_ቦታ፦ አጥቂ #ቁመት፦ 1.
+3
#ስም ፦ እስራኤል ሻጎሌ #ቀድሞ_የተጫወተበት_ክለብ፦ 👉 አርባምንጭ ከተማ (2011-2012) 👉 ነገሌ አርሲ (2014-2015) 👉 ባቱ ከነማ (2016) #የሚጫወትበት_ቦታ፦ አጥቂ #ቁመት፦ 1.77m #ኪሎ፦ 63kg በኢትዮጵያ ቡና የሚቆየው፦ 3 ዓመት እንኳን ወደ ታላቁ የኢትዮጵያ ቡና መጣህ‼

በ2016 ዓ.ም በተወዳደሩበት ውድድሮች ሁሉ ከአንድ አቻ ውጪ ሁሉንም በአሸናፊነት ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ ቡና ሴቶች ቡድን ዛሬ በተጠናቀቀው የክልል ከተሞች ሻምፒዮን በመሆን አጠናቋል። ነተደረገው የኮ
+5
በ2016 ዓ.ም በተወዳደሩበት ውድድሮች ሁሉ ከአንድ አቻ ውጪ ሁሉንም በአሸናፊነት ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ ቡና ሴቶች ቡድን ዛሬ በተጠናቀቀው የክልል ከተሞች ሻምፒዮን በመሆን አጠናቋል። ነተደረገው የኮከቦች ምርጫም አሰልጣኝ ቶሎሳ ቢርቢርሳ ➡ ኮከብ አሰልጣኝ ስኳሬ ሁሌ ➡ ኮከብ ግብ ጠባቂ ስሚያ ሬድዋን ➡ ኮከብ ተጫዋች ሆነው ተመርጠዋል።

የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ በ2016ዓ.ም የውድድር ዓመት በተሳተፈባቸው ውድድሮች አራት ዋንጫዎችን ማሳካቱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ቡና ዋናው ቡድን ➡ የኢትዮጵያ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቡና U-20 ቡድን
የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ በ2016ዓ.ም የውድድር ዓመት በተሳተፈባቸው ውድድሮች አራት ዋንጫዎችን ማሳካቱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ቡና ዋናው ቡድን ➡ የኢትዮጵያ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቡና U-20 ቡድን ➡ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ ቡና ሴቶች ቡድን ➡ የአዲስ አበባ ከፍተኛ ዲቪዝዮን ሻምፒዮን እና የክልል ከተሞች ውድድር ሻምፒዮና ሆነው ማጠናቀቃቸው ይታወቃል። በአሰልጣኝ ቶሎሳ ቢርቢርሳ የሚመራው የኢትዮጵያ ሴቶች ቡድን ባለው ዕሮብ የክልል ሻምፒዮና የምድብ ጨዋታቸውን ሁሉንም በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆናቸውን ያረጋገጡት ሲሆን፤ ዛሬ ድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በሚደረገው የመዝጊያ ፕሮግራም ላይ የሻምፒዮናነታቸውን ዋንጫቸውን በክብር ያነሳሉ።