不要被骗子欺骗!Telemetrio 会找到并标记这些频道 👉 如果想查看标记,请订阅 👈
3 584
订阅者
无数据24 小时
-87 天
-4930 天
无数据
帖子浏览量
无数据24 小时
无数据48 小时
无数据
参与率
无数据
每日帖子数
帖子存档
3 584
በነጻ አንብቡ 💚
ክላሽ የታጠቀን ወታደር ‘የመሸበት የእግዜር እንግዳ’ ብሎ ቤቱ ወስዶ እንደማሳደር ካለ ደግነት አንስቶ፣ ድንገት ‘ግልፍ’ ያደረገውን ፖሊስ በጥፊ እስከ መምታት የደረሰ ቁርጥ ኃይለኝነት... በእነዚህ ጠርዝ እና ጠርዞች መሀል ያሉ ትውስታዎች የተቋጠሩበት የአባት ማስታወሻ ነው።
3 584
ለቅዳሜያችን 💚 "ከወደቀው ዋርካ አሥራ አራት ቅጠሎች" ለንባብ በቅቷል። አፍሮ ሪድ ላይ ገብታችሁ #በነጻ እያነበባችሁ "ነፍስ ይማር" ማለት ነው። ለሌሎችም SHARE አድርጉት። አንብባችሁ review አድርጉት።
3 584
ቅዳሜ አይደለሞይ? ደስታ አንፈልግሞይ? 🤨😍
እነሆ የብቻ ሦስተኛ መጽሐፌን በቅርብ ቀን ብያለሁ። "በከንፈርሽ በራ'ፍ"ን እንደ ታናናሾቿ እንደ የ"ብርሃን ልክፍት" እና "የብርሃን ሰበዞች" ፊት ሰጥታችሁ፣ ስማችሁ፣ ተቆጥታችሁ፣ ተንከባክባችሁ እንደምታሳድጉልኝ አምናለሁ። እንግዲህ ከ"እኔ" ወጥታ "የእኛ" መሆኗ ነውና፣ ወሬውን ለወዳጅ ዘመድም አጋሩት።
Spread the word!
❤
3 584
አጽንኦት እንዲያገኝ ስለፈለግኹኝ ነው። በነገራችን ላይ ቤተሰቦቼ እንኳን ወዳጅነታችንን አሁን ከእናንተ ጋር ነው የሚያነቡት። ይኽንን አደረግኹኝ ብዬ ልታበይ ወይ ልደነቅበት አይደለም። ወዳጅ ነኝ የሚል ቀርቶ፣ ማንም ሰው ለክብሯ እና ለprivacyዋ ሲል ማድረግ የሚጠበቅበት የኅሊና ግዴታ መሆኑን ግልጽ ለማድረግ ነው።
3 584
እኔና ጥቂት ወዳጆቼ ከጎኗ ሳንርቅ፣ በሰው እና በገንዘብ አቅም በሚታለፍ ነገር ሁሉ ለማገዝ ያልሞከርነው ነገር፣ ያልፈነቀልነው ድንጋይ የለም። እኛ እንዲህ የሞከርን የቤተሰቦቿን መገመት ነው። ቢያንስ መኖሪያ አካባቢዋን ለመቀየር ብዙ ጊዜ ታስቦ እና ተሞክሮ በእሷ እምቢታ ነው የተፋረሰው። እንግዲህ ትልቅ ሰው ናት የአገሩም ህግ አይፈቅድምና፣ ካለእሷ ፍቃድ እና ፍላጎት ጣልቃ መግባት አይቻልም።
ሀኪሞችም ጥቂት እንኳን የጤናዋን ሁኔታ trigger የሚያደርግና የሚያባብስ ነገር እንዳይደረግ፣ ሁሉም ነገር በእሷ ፍቃድ እና ፍላጎት ላይ እንዲሆን አበክረው አሳስበዋል። ያንን ማክበር ነው። የሚባለውንም ሁሉ ብታይ እንዳዲስ የመቀስቀስ እና የመረበሽ አቅም አለውና፣ እስከ ጊዜው ድረስ ከዚህ በላይ ማለት አልችልም። ቢያንስ የሰለጠነ አገር እንደሚኖር ሰው ይኽን መረዳትና ራስን ከተጠያቂነት ማራቅ ይገባ ነበር። ግን አስገራሚ ፍጡሮች ነን።
እንግዲህ እንዲህ የቀረጸውን ቪዲዮ ይዞ ነው እለቀዋለሁ ብሎ ማስፈራሪያ አድርጎት ዛሬ የለቀቀው። ትክክለኛ ቀረጻ እንዳልሆነ ያውቀዋል። ያለችበትን ሁኔታ እና የምትፈልገውንም ከለላ ይረዳል። ለዚያም አይደል ማስፈራሪያ አድርጎት የነበረው? ባይሆንና በሰላም የተቀረጸ ቢሆን በወቅቱ ባሰቡት ቻናል ይለቁት ነበር። እኛም ተደስተን በናፍቆት እናየው ነበር። የቀረጿትም አሁን የታየው ያህል ብቻም አይደለም።
በወቅቱ እሷ ህክምናዋን በተሻለ ሁኔታ ላይ ለመከታተል በጣም ጥሩ ሂደቶች ስለነበሩ ላለማበላሸት ላይ ታች ተብሎ ለእርሷ ሰላም እና ደህንነት ሲባል፣ በመሀል በነበሩ በጎ ሰዎች እገዛና ትብብርም እንዳይለቁት ተሞክሮ ቀርቶ ነበር። ይኸው ነገሩን መልሰው ይዘውት መጥተዋል።
ነፍሱን ይማረውና የአድማስ ሬድዮው ቴዎድሮስ ከማርክስ ባለቤት ከማያ ኃይሌ ጋር ሄዶ ቀርጾ የነበረው ድምጽ ይታወቃል። ቴዲ ራሱ በወቅቱ ሚዲያ እንደማትፈልግና በድብቅ መቅረጹን እዚያው ሬድዮ ላይ ተናግሮ ነበር። ለምን የማትፈልገውን አደረገ? ለምን በድብቅ? ልክ እንዳልሆነ ለማወቅ ህሊናውን ምን ጋረደበት? ለእሱ የአንድ ቀን ቀረጻ ነበር። እሷ ግን ብዙ ተጎዳችበት። ቀርጾ ከተመለሰ በኋላ አንድም ቀን መልሶ ለመደወል አልሞከረም ነበር። እሷም በድብቅ ቀርጾ ማስተላለፉን ስትሰማ እና ስታውቅ በጣም ተረብሻ አዝናበት ነበር ያለፈው።
ሁኔታዋን እንዳየ ወዳጅ እኔም በጣም አዝኜበት ነበር። በወቅቱ እኔ ጋ ደውላ የተናገረችውን እና የተሰበረችውን እስክሞት አልረሳውም። "ጆንዬ እኔ እኮ እንደ አንተ ሰው ወንድም እየመሰሉኝ ነበር በሬን ሲመቱ ተደስቼ የምከፍተው። ምን አደረግኳቸው ይኽን ያህል? ለምን አይተዉኝም?" ብላ ነበር። ያንን መረበሿን ሳይ ቴዲ ጋ ደውዬ ላወራው ሞክሬ ነበር። እሱ እንኳን ሊጸጸት "እንደውም ብዙ ነገር ቆራርጬ ያወጣሁት። ብዙ የተውኩት ድምጽ አለ።" ብሎ ጭራሽ ምስጋና ፈልጎ ነበር። በሰላም ይረፍ።
ግን ለምን ይኽን ያህል አስፈለገ? ጂጂ ሙዚየም ወይ መደበሪያ አይደለችም። የትልቅ ልጅ እናት ትልቅ ሰው ናት። ያንን መገንዘብ ለምን አቃተን? ሚዲያው አስፈላጊ እና ጠቃሚ ቢሆንላትስ ከልጅነት እስከ እውቀት የማደንቃት እኔ አላደርገውም ነበር? ከዚህ ቀደም ክንፉ አሰፋ ያወራበትን ድፍረት ልክ በደፈናው አንስቼው ነበር። ለአንድ ቀን ለሃያ ደቂቃ አግኝቷት ስንት ስዓት ስንት ነገር አወራ? ብቻ በጣም አሳፋሪ ነው።
የሀኪም ትዕዛዝ ስናከብር፣ ለእሷ የሚያስፈልጋትን ብቻ ለማድረግ ስንሞክር እንጂ፣ እንዲህ አይነት ነገር ከእለት ርካሽ የሶሻል ሚዲያ ጩኸት በቀር፣ ለእሷ ጥቅም ቢኖረው፣ ይኽን ድሮ አናደርገውም ነበር? ጭራሽ እንዲህ ዓይነት ነገር ብዙ ወደ ኃላ ይመልሳታል። ሀኪሞችም በሕይወት ላይ ሁሉ ስለሚመጣ ጉዳትና ህመም ማባባስ ሊደርስ ይችላል ልዩ ጥንቃቄ ትፈልጋለች ብለዋል።
አሜሪካ ውስጥ የስነ ልቡና እና አእምሮ ህመም በጥንቃቄ ነው የሚያዘው። ሰው ካልፈቀደ መታከምም ከቦታ ቦታ መዘዋወርም አይችልም። ወዳጅ ነኝ ያለ ያንን ማክበር፣ ሊያደርግ ከሚችለው በጣም ትንሹ ነገር ነው። ትክክለኛ ምርመራዋንም እንኳን እኔ ወይ ሌላ ሰው፣ ሀኪሞች እንኳን እርስ በርስ እንዳያወሩ የHIPPA ህግ ያስገድዳቸዋል።
እንደ ተወዳጅ መዚቀኛ ይቅር፣ ብዙ እንደሰራ ሰው ይቅር፣ እንደ አንድ ሰው፣ እንደ የአገር ልጅ፣ እሷን ያያት እና ያለችበትን ሁኔታ ያየ ሰው ሊያደርግ የሚችለው አንድ ነገር እሷን መጠበቅ እና ከለላ መስጠት ነው። የሚፈልገውን ሳይሆን የሚያስፈልጋትን የሞራል ግዴታ መፈጸም ነው። እንጂ መረሳቱ ትዝ ባለው ቁጥር እንዲህ ዓይነት ግብታዊና ፍጹም ሊጎዳት የሚችል መረጃ ማሰራጫት ተገቢ አይደለም።
አሜሪካ ውስጥ በህግም ቢሆን ራሱን መከላከል የማይችልን ሰው፣ ለራሱ የህግ ከለላ ፍላጎት ወይ በቤተሰብ ፍቃድ (ወላጆች እና ልጅ) እሱንም ታካሚው ቀድሞ ይሁንታ ከሰጣቸው ለህክምና ሂደት ካልሆነ በቀር መቅረጽ ፎቶ ማንሳት በህግ ያስጠይቃል።
ቤተሰቦቿ ለምን ወጥተው አይነግሩንም? የconspiracው ቋሚ ማጀቢያ ነው። ለምን ይነግሩናል? እኛ እንደ አድናቂ ይኽንን ያህል የተጨነቅን እንደ ቤተሰብ እንቅልፍ አግኝተው ይኖራሉ? ሌላው ነገር ቢቀር ቢያንስ ከእኛ አፍ ሰላም ለማግኘትና እፎይ ለማለት ይኽንን ማድረግ ቢችሉ ለምን አይመርጡትም?
ወጥተው ሚዲያው ላይ እንዲህ ነው እንዲያ ብለው መስማት የምንፈልገውን ቢነግሩን፣ እሷ ስትሰማውስ ምን ይሰማታል? ጭራሽ ወደባሰ ሁኔታ እና ድብርት ውስጥ ለመክተት trigger ያደርጋል ተብሎ አይታሰብም?
እናንተ እህታችሁ ወይ ወንድማችሁ ላይ ተመሳሳይ ነገር ቢከሰት እንዲሁ ለወሬ ፍጆታ ታውሉታላችሁ? ብዙ ደስታ ለሰጠችን ሰው ለምን ሰላም እና ከለለ መስጠት ከበደን? የወሬ ፍቅራችን ይህን ያህል ለምን ህሊናችንን አሸነፈው?
አሁንም የተሻለ ህክምናዋን የመከታተል ሁኔታ እና ጥረት ላይ ናት። (ነበረች ባልል ደስ ይለኛል። ግን ይህን ቪዲዮ ካየችው በጣም ትረበሽና የከፋ ሁኔታ ውስጥ መግባቷ አይቀርም። :( ) ብዙ ጊዜ ነገሮች ሊቃኑ ሲሉ ፈተና የሆነው እንደ ቅቤ ሚዲያው ላይ ጠብ የሚደረገው እንዲህ ሆነች፣ በዚህ ገባች ነው። ዋና የምትፈልገው ሰላም እና ከለላ (protection) ነው። Privacyዋን እናክብርላት።
የምትወዷት ከሆነ የምትፈልገውን space እና ነጻነት ስጧት። ፍቅራችንን እና አክብሮታችንን በዚያ እናሳያት። እንርዳት እናሳክማት የሚለው ሀሳብ ከጥሩ ልብ የሚነሳ ቢሆንም፣ ስትፈልግ እና ስትፈቅድ ነው። እስከዚያ የእኛን እርዳታ በግልጽ የጠየቁ ብዙ አርቲስቶች አሉ። እነሱን እናግዝ። በየእምነታችን እንጸልይላት።
ይኽ በእንዲህ እንዳለ በተለቀቀው ቪዲዮ የተነሳ በጤናዋም ሆነ በህይወቷ ላይ ሊደርስ ስለሚችለው ነገር የENT TV ሰዎች እና ጋዜጠኛ ወድንወሰን ከበደ ሙሉ ኃላፊነቱን ይወስዳሉ። ሌሎቻችን ፍቅራችንን እና አድናቆታችንን በመተው፣ ሰላሟን ባለመንሳት እናሳያት። አገር አለኝ ወገን አለኝ ትበል።
P.S. ይኽን ፎቶ የተነሳነው ከአንድ ዓመት በፊት ከእንጅባራ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬት በተሰጣት ጊዜ፣ የሰማችሁትን የምስጋና ድምጽ በቀረጽኳት እና በወቅቱ ያያችሁትን ፎቶ ባነሳዃት ጊዜ፣ ለማስታወሻ እንነሳ አብረህ ላክላቸውና ይውጣ ብላኝ ያስቀረነው ነበር። በወቅቱም ከዚያም በኋላ በጭራሽ ፎቶውን የማጋራት ፍሎጎት አድሮብኝ አያውቅም ነበር። እንደ ቅርብ ወዳጇም ላደርግ ከምችላቸው ነገሮች መካከል በጣም ተራው ነው። አሁንም የማጋራው በእሷ ፍቃድ፣ በሀኪም ምክረ ሀሳብ መልእክቱ
3 584
ጂጂን የሚወዳት የሚቆረቆርላት ሁሉ ማወቅ ያለበት!
«ሰው እየመሰሉኝ ነው በሬን ሲመቱ ተደስቼ የምከፍተው።»
ይኸው ደግሞ የእጅጋየሁ ሽባባውን ነጻነት እና ሰላም ማወክ ዞሮ መጥቷል። ያው መነሻው አብሮ የመታየት፣ ስሜ ከስሟ ጋር ይነሳ የማለት ፍላጎት ነው። እኔ እንኳን የማውቀውን ሁሉ ብናገር፣ ብዙ ነውረኞችን ማጋለጥ ይቻል ነበር። በእሷ ገንዘብ እንሠራለን፣ ዝና እናገኛለን በሚል ፍላጎት እና ተስፋ፣ እንደ investment ገንዘብ መድቦ ለማውጣት፣ ከቦታ ቦታ ይዞ ለመሄድ እስከ መሞከር ድረስ (kidnapping በሉት)፣ ግጥምና ዜማ አስጠንቶ ለዩቲዩብ ንግድ እስከማሰብ ብዙ አሳፋሪ እና ህገወጥ ሙከራ ያደረጉ አሉ። ነገር ግን ዝርዝሩ እሷን ላለመረበሽ እና ደህንነቷን ለመጠበቅ ሲባል ተከድኖ ይብሰል።
አሁን የሚንሸራሸረው ፎቶ እና ዛሬ የተለቀቀው ቪዲዮ፣ ከሁለት ዓመት በፊት ኦክቶበር 23/30, 2022 የተቀረጸ ነው። ጋዜጠኛው አሁን ይኽንን ማድረግ ለምን እንደፈለገ ራሱ ያውቃል። (የሙያ ethics አላየሁበትምና ስቅቅ እያለኝ ነው ጋዜጠኛው የምለው) በወቅቱ ጋዜጠኛም ነውና ከENT (Ethiopian Network TV) ነው የመጣነው ብለው ካሜራ ወድረው ቃለ መጠይቅ አድርጎ ቀርጿትም ነበር። ከቀረጿት ጥቂቱን ነው የለቀቀው።
እጅጋየሁ በጣም ልዩ የሆነ ትኩረት፣ የራስ ምርጫ ነጻነት እና ህክምና የሚፈልግ ሁኔታ ውስጥ እንዳለች ብዙ ሰው ይረዳል ብዬ አስባለሁ። በእሷ የጤንነት ሁኔታ ላይ ያለን ሰው ለቃለ መጠይቅ ማሰብ ትንሽ ህሊና ቢስነት ይጠይቃል። የሚለውም ሁሉም ነገር በቁም ነገር ያለመወሰድ እድሉ ስፋት ለመረዳትም ብዙ ምርምር አይጠይቅም። በተለይ ሀኪሞች አስጠንቅቀው እንዳሉት የሚዲያ ሰው ናትና፣ ከሚዲያ ጋር የተያያዘ ትኩረት ሙሉ ለሙሉ፣ በጭራሽ አያስፈልጋትም።
此内容仅面向 18 岁及以上用户
登录服务即表示您确认已年满 18 周岁。
