ኢትዩ ኢስላማዊ ጥያቄና መልስ
前往频道在 Telegram
ኢስላማዊ እውቀታችንን የምንገመግምበትና የምናጎለብትበት ቻናል ነው። ጥያቄ የሚቀርብበት ሰዓት በኢትዩ አቆጣጠር ቀን 6:00 ( ሰዓት ) ምሽት 1:00 (ሰዓት ) ይቀርባል ጁምዓ ሁሌም ጥያቄ አይኖርም
显示更多未指定国家未指定类别
2 915
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
2 915
የረመዳን ፆም ትሩፋቶችና የተደነገገበት ጥበብ
1.ትሩፋቱ፦
አቡ ሑረይራ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል
“የረመዳንን ወር በእምነትና ምንዳን በማሰብ የፆመ ያሳለፋቸው ኃጢቶች ይማራሉ፡፡”
ቡኻሪ (19ዐ1) ሙስሊም (76ዐ)
በሌላም ሀዲስ እንዲህ ብለዋል “አምስቱ ሰላቶች፣ ከጁምዓ እስከ ጁምዓ፣ ከረመዳን እስከ ረመዳን በመካከላቸው ያሉትን ኃጢአቶች ያብሳሉ ታላላቅ ወንጀሎችን ሲቀር፡፡”
ሙስሊም (233)
2.የፆም መደንገግ ጥበቦች፦
1.ፆም የሸይጧንን መተላለፊያ ደም ስር ስለሚያጠብ ነፍስን በማፅዳት ከመጥፎ ባህሪና ከክፉ ተግባር ያርቃል፡፡
2.የምድራዊ ህይወትን ቸል ተብሎ የነገው ህይወት እንዲወሳና እንዲከጀል ያደርጋል::
3.ፆመኛ ርሃብን ስለሚያስተናግድ ለረሃብተኛ እንዲያዝን ትምህርት ይሰጣል፡፡ ሌሎችንም ጥበቦች ጠቃሚ ውጤቶች አሉት::
2 915
የረመዳን ፆም ሸሪዓዊ ድንጋጌውና መረጃው
አላህ የረመዳንን ወር መፆም ግዴታ ከማድረጉም በላይ ከአምስቱ የኢስላም ማዕዘናትም አንዱ ነው:: አላህ እንዲህ ብሏል፦
يَـٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ كُتِبَ عَلَيْكُمُ ٱلصِّيَامُ كَمَا كُتِبَ عَلَى ٱلَّذِينَ مِن قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
البقرة ١٨٣
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ ጾም በነዚያ ከናንተ በፊት በነበሩት (ሕዝቦች) ላይ እንደ ተጻፈ በናንተም ላይ ተጻፈ (ተደነባ) ልትጠነቀቁ ይከጀላልና”፡፡
አል-በቀራህ 183
አብደላህ ኢብን ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል
“ኢስላም በአምስት ነገሮች ተገነባ:: ከአላህ በቀር መመለክ የሚገባው እንደሌለና ሙሐመድም የአላህ መልዕክተኛ መሆናቸውን መመስከር ሰላትን በተሟላ መልኩ መስገድ ዘካን መስጠት ረመዳንን መፆና ከተቻለ ሐጅን ማድረግ፡፡”
ቡኻሪ (8) ሙስሊም (16)
ጠልሃ ኢብን ኡበይዲላህ እንዳስተላለፉት
“አንድ ሰው ወደ ነቢዩ (ﷺ) መጥቶ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! አላህ ግዴታ ያደረብኝን ፆም ይንገሩኝ? ሲል “የረመዳን ወር ፆም” አሉት፡፡ እሱም “ከዚህ ሌላ አለብኝ? በማለት ሲጠይቅ “አይ በፈቃድህ የምትጨምረው ብቻ ነው” በማለት መለሱ፡፡”
ቡኻሪ (46) ሙስሊም (11)
የረመዳንን ወር መፆም ግዴታና ከኢስላም ማዕዘናት አንዱ በመሆኑ ዑለማዎች ሁሉ ይስማማሉ፡፡ ይህንን የሚያስተባብል ከእስልምና ይወጣል፡፡
2 915
✔ የመልቲፕል ስክለሮሲስ ህሙማን በጎ አድራጎት ማህበርን
ይህ ተቋም በ MS የተጠቁ እህት ወንድሞች እርዳታ የሚያገኙበት ተቋም ነው።
MS ምንድን ነው?
የበሽታ ተከላካይ ሀይላችን የራሱን፣ንፁሁን የሰውነታችንን አካል ሲያጠቁ የሚከሰት በሸታ ነው።በዚህ መልኩ ከአንጎላችን ወደ አካላችን የሚተላለፉ መልእክቶች በአግባቡ አለመድረስ ወይም ሙሉ ለ ሙሉ አለመድረስን ያስከትላል።
MS
👉የነርቭ ህመም ነው
👉አንጎልንና የጀርባ አጥንትን የሚያጠቃ በሽታ ነው
👉 እእነዚህን አካሎች በማጥቃት የተለያዩ የአካል ክፍሎች ላይ ለውጥ ይፈጥራል። ከነዛም ውስጥ ንግግርን ያኮላትፋል
ፓራላይዝ ወይም ሽባ ያደርጋል የመሄድ እንቅስቃሴን ይገድባል ማንገዳገድ ያመጣል እንዲሁም እይታን ይገድባል።
በሽታው ከ 15 እስከ 60 ዓመት ባሉ ሰዎች ላይ በብዛት ሲፈጠር ሴቶችን የማጥቃት እድሉ ሰፊ ነው።
በህክምና አንድ ሰው ይሄን ስላደረገ ወይ ይሄን ስላላደረገ በሽታው ይፈጠራል የሚያስብል ነገር የለውም። ከመላምት ውጪም አይታወቅም መነሻውም።
በዚህ ህመም የተጠቁ መፍቻ ፈውስ የለውም። ነገር ግን ህመሙ እንዳይባባስ መግቻ መድሀኒቶች አሉት።
እነዚህ መድሀኒቶች ሀገራችን ስለማይመረቱ ዋጋቸው እጅግ በጣም ውድ ናቸው። ለመድሀኒት መግዣ ለአንድ ሰው በዓመት በሚሊየኖች ወጪ ያስወጣል።
መድሀኒቱን አለማግኘታቸው ደግሞ ህመሙን አባብሶት ስቃዩን በባሰ ሁኔታ በመጨመር ማስተካከል ወደማይችሉት ውስብስብ ህመም ይቀየራል።
ብዙ ወጣቶች በዚህ ህመም ምክንያት ከትምህርታቸውና ከስራቸው ተስተጓጉለው ቤታቸው ተቀምጠዋል።
ከዚህም በባሰ መልኩ መድሀኒቱን የመግዛት አቅም ስለሌላቸው ህመሙ እየተባባሰባቸውና የአልጋ ቁራኛ በማድረግ አምራችነታቸውን ገትቷል። ለቤተሰቦቻቸውም ገና በአፍላ ወጣትነታቸው ሸክም ያደርጋል።
የዚህ ተቋም መስራች ከህመሙ ተጠቂዎች አንዱ የሆነው አቡበከር ቃሲም ይገኝበታል። ለ 5 ዓመታት በህመሙ የተጠቃ ወንድማችን ነው።
ይህን ታሳቢ በማድረግ የዚህ በሽታ ተጠቂ የሆነው ወንድማችን አቡበከር የ MS ህሙማንን መርጃ ተቋም በመክፈት በ MS የተጠቁ ወንድም እህቶችን ለመርዳት መንገድ ላይ ነው።
የተቋሙ ሙሉ ስም
የመልቲፕል ስክለሮሲስ ህሙማን በጎ አድራጎት ማህበርን ይሰኛል።
የዚህ ማህበር ዓላማ:-
― ስለ በሽታው ግንዛቤን ማስፋት
―ለ MS ተጠቂዎች የአቅምና የስነ ልቦና ድጋፍ ማድረግ
―ስለ MS የቆመ ፊዚዮቴራፒ ማዕከልን መመስረት
―የህክምና እርዳታን ማድረግ.....
ሆኖም ይህን ለማሳካት የርሶን ትብብር ያስፈልገናልና ተከታዩን ሊንክ በመንካት የቴሌግራም ቻነሉን በመቀላቀል በቻሉት አቅም ይተባበሩ ዘንድ እንጠይቃለን።
https://t.me/joinchat/D3SI7BZzIgTSgvKWPs-57w
ይህን ጥቂት ነገርን በማድረጎት በብዙ የሚቆጠሩ የ MS ተጠቂ ኢትዮጵያዊን ወጣት ህይወት ለመታደግ ሰበብ ይሆናሉ!
#Share #share #share
2 915
አሰላሙ አለይኩም
ዛሬ በአላህ ፍቃድ ሱረቱል አል ኢምራን ከ አንቀፅ 132-135 ያለውን በአጭሩ እናያለን
🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃
وَأَطِيعُوا اللَّهَ وَالرَّسُولَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ
ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህንና መልክተኛውን ታዘዙ፡፡ 3:132
۞ وَسَارِعُوا إِلَىٰ مَغْفِرَةٍ مِّن رَّبِّكُمْ وَجَنَّةٍ عَرْضُهَا السَّمَاوَاتُ وَالْأَرْضُ أُعِدَّتْ لِلْمُتَّقِينَ
ከጌታችሁ ወደ ኾነችም ምሕረትና ስፋትዋ እንደ ሰማያትና ምድር ወደ ኾነች ገነት አላህን ለሚፈሩ የተዘጋጀች ስትኾን ተቻኮሉ፡፡ 3:133
الَّذِينَ يُنفِقُونَ فِي السَّرَّاءِ وَالضَّرَّاءِ وَالْكَاظِمِينَ الْغَيْظَ وَالْعَافِينَ عَنِ النَّاسِ ۗ وَاللَّهُ يُحِبُّ الْمُحْسِنِينَ
ለእነዚያ በድሎትም ኾነ በችግር ለሚለግሱት፣ ቁጭትንም ገቺዎች ከሰዎችም ይቅርታ አድራጊዎች ለኾኑት (ተደግሳለች)፡፡ አላህም በጎ ሠሪዎችን ይወዳል፡፡ 3:134
وَالَّذِينَ إِذَا فَعَلُوا فَاحِشَةً أَوْ ظَلَمُوا أَنفُسَهُمْ ذَكَرُوا اللَّهَ فَاسْتَغْفَرُوا لِذُنُوبِهِمْ وَمَن يَغْفِرُ الذُّنُوبَ إِلَّا اللَّهُ وَلَمْ يُصِرُّوا عَلَىٰ مَا فَعَلُوا وَهُمْ يَعْلَمُونَ
ለእነዚያም መጥፎ ሥራን በሠሩ ወይም ነፍሶቻቸውን በበደሉ ጊዜ አላህን የሚያስታውሱና ለኀጢአቶቻቸው ምሕረትን የሚለምኑ ለኾኑት ከአላህም ሌላ ኀጢአቶችን የሚምር አንድም የለ፡፡ (በስሕተት) በሠሩትም ላይ እነርሱ የሚያውቁ ሲኾኑ የማይዘወትሩ ለኾኑት (ተደግሳለች)፡፡ 3:135
🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃
🌸አምላካችን አላህ (ሱ.ወ) ሁሌም ቢሆን እርሱን ከማስታወስ እንዳንሳነፍ ይነግረናል። እርሱን ከምናስታውስበት መንገድ ትልቁ እና ዋናው ደግሞ ቁርአን ነው። እርሱ መገሰጫ መሆኑንም በብዙ ቦታ ቁርአን ውስጥ እንመለከታለን።
🌸በቁርአን ውስጥ ብዙ ቦታ የተጠቀሰ፣ እንድናስታውስ እና ዘወትር አንድንተገብረው ከሰፈረው አንዱ ተቅዋ (አላህን ፍራቻ) ነው።
🌸አላህን መገዛት መሀርታን እንደሚያስገኝልን ዛሬው በምናየው አንቀፅ መጀመሪያ ላይ እናገኛለን (3:132)
🌸ከዚህ አንቀፅ ከፍ ብለን ስንመለት (3:130) አራጣን እንዳንበላ እና በዛ ምትክ ተቅዋ እንዲኖረን ይነግረናል።
* 3:130*
يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ لَا تَأْكُلُوا۟ ٱلرِّبَوٰٓا۟ أَضْعَٰفًا مُّضَٰعَفَةًۖ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ
እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አራጣን የተነባበሩ እጥፎች ሲኾኑ አትብሉ፡፡ ትድኑም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡
🌸ብዙዎች አራጣን ሚበሉበት ምክንያት የትርፍ መንገድ እንደሆነ በማሰብ ነው። ግን አምካችን አላህ በዚህ ምትክ አላህን በመፍራት ያ የምንፈልገውን ማግኘት እንደምንችል ይነግረናል። በተከታታይም ሪባ /አራጣ መብላት የሌለብንን ምክንያት ይነግረናል።
💫1 የልፋት እና ድካማችንን ፍሬ ማግኘት ከፈለግን መንገዱ አላህን ፍራቻ መሆኑን በመግለፅ (3:130)
💫 2 ለከሀዲያን ተብሎ ወደ ተዘጋጀው ጀሀነም እኛ እንዳንገባ (3:131)
💫3 እርሱን እና መልእክተኛውን (ሰ.ዐ.ወ) እንድንታዘዝ እንደሚገባን (3:132) አስከትሎም
💫4 እርሱን ምህረቱን በመጠየቅ እነዚያ አላህን የሚፈሩ የሆኑት ወደ ሚገቡበት እንድንቻኮል መሆኑን ይነግረናል። (3:133)
🌸(3:133) አንቀፅ ላይ እንደምናየው አምላካችን አላህ (ሱ.ወ) ጀነት እርሱን ለሚፈሩት እነደሆነ ይነገግረናል።
🌸ቀጥሎም እነዚያ አላህን (ሱ.ወ) የሚፈሩት ብሎ ያላቸውን ሰዎች ስብእና ይነግረናል። (3:134) ከዚህም ብዙ ትምህርትን መውሰድ ይገባናል።
🌸እነዚያ አላህን (ሱ.ወ) የሚፈሩ የተባሉት፣ የጀነት የሚሆኑት ሰዎች የሚከተሉት ባህሪያት አሏቸው።
🌟1)በድሎትም ሆነ በችግር ጊዜ የሚለግሱት
የሚለግሱት ብር፣ ሀሳብ፣ ጊዜ፣ አቅም፣ እድሜያቸውን ወዘተ ሊሆን ይችላል። ይህንን ሁሉ ለአላህ ብለው ያደረጉ አላህም ለመልካም ስራቸው ይከፍላቸዋል።
🌟2) ንዴታቸውን የሚቆጣጠሩት
አሁን ላይ ብዙዎቻችን ለትንሹም ለትልቁም መናደድ ይቀርበናል። ልብ ልንል ሚገባው ግን እኛ ለትንሽ ነገር ንዴታችንን መቆጣጠር ሳንችል አላህ ትልቅ የሰራነውን ሀጥያት ይቅር እንደማይለን ነው። ስለዚህም ራሳችንን መቆጣጠር እና ንዴታችንን መግታት መለማመድ ይኖርብናል።
🌟3) ለአላህ ብለን ይቅር ማለትን እና በጎ ስራ መስራትን
ይቅር ስንል ሁሌም ለአላህ ብለን፣ ከእርሱ የምናገኘውን በማሰብ ብቻ ብለን መሆን አለበት። ይቅርታ ማለት በመሰረቱ ያ ሰው ይቅር መባል ስለሚገባው ወይም ጥፋቱ ስለተረዳው መሆን የለበትም። ይልቁንስ አላህ እነዛ እርሱን ከሚፈሩት እንዲያደርገን፣ በዚህም በወዲያም አለም ስኬታማ እንዲያረግን ብለን ከማሰብ ነው መሆን ያለበት።
🌟4) መጥፎ በሰራንም ጊዜ አላህን ሚያስታውሱ(3:134)
አላህን ሚያስቆጣ ስራ ከሰሩ በሁዋላ ቶሎ ወደ እርሱ ተመላሾች ናቸው። አሁንም ማስተዋል ሚገባን እነዚህ የጀነት ሰዎች ናቸው። አጥፍተዋል፣ በድለዋል። ነገር ግን በስራዎቻቸው ላይ አይዘወትሩም። ወዲያውም ወደ አላህ ተመላሾች ናቸው።
ብዙ ጊዜ የበደልነው፣ ያጠፋነው ይበዛብን እና መመለስን እንፈራለን፣ ቀጥለን መልካም ወደሆነ መንገድ መመለስ ለኛ ማይታሰብ መሆኑን ለራሳችን እንነግራለን። ግን ሁሌም ወደርሱ ከተመለስን እነኚህ አላህ የጀነት ካረጋቸው ሰዎች መሆን እንችላለን። ከእርሱ ውጭ ይቅር የሚለን የለምና
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@rmythoughts
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
2 915
💚المشتقا لرؤيا ربها
ወአለይኩም ሰላም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ
እንዴት ናችሁ ያጀመአ !
ወላሂ ባለፈው አልገባኝም ነበር የአቡበከር ህመም አሏህ አፊያ ያድርግህ ወንድሜ በጣም ነው ያሳዘነኝ ሀቂቃ ላኪን አልሀምዱሊላህ አላኩሊሃል አብሽር ለሁሉም በሽታ መድሃኒት አለውና አሏህ ሰበቡን ይፍጠርልህ ወንድሜ በቁርኣንም ሺፋን መፈለግህ አትርሳ
وَيَسْأَلُونَكَ عَنِ الْجِبَالِ فَقُلْ يَنسِفُهَا رَبِّي نَسْفًا
ከጋራዎችም ይጠይቁሃል፤ በላቸው «ጌታዬ መበተንን ይበትናቸዋል፡፡
ይቺን አያት ከርርሃ ለጌታችን የሚሳነው ነገር የለምና አሏህ አፊያ ያድርግህ!
أسأ الله العظيم رب العرش العظيم ان يشفيك
أسأ الله العظيم رب العرش العظيم ان يشفيك
أسأ الله العظيم رب العرش العظيم ان يشفيك
በቅርቡ ጤናህ ተመልሶልህ የምታበስረን አሏህ ያድርግ ያረብ በዱኣ አንረሳህም አብሽር
2 915
💚መድ የሮህማን ባርያ
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ።
ውድ ኢትዩ ጥ& መ እደትናችሁልኝ ጀሚአን እኔአልሀምዱሊላህ ሰላምነኝ
በመቀጠል ለምታደርጉልን እኛን ለማሳወቅ ብላችሁ ጊዜአችሁን መፅዋት ለምታደርጉ አጅራችሁን ጀነተል ፈርዶስ ያድርግላችሁ
ዋርድ ውዷእህቴ መብሩክ አለይኪ በጣም ደስ የምትይ ከመጀመሪያው ጀምረሽ እየተከታተልሽ ያለሽ ነሽ እኛማ በመሀል ጥለነው ጠፋን ከመናደደ ብዛት ያለቀስኩበትንም ቀን አልረሳምነበር የዛሬን አያድርገውና ።
በመቀጠል ውዱ ወንድሜ አብበከር አላህ የፈለገውን ባሪያውን ይፈትነዋል ላተም የሰጠህ ከፈተናዋ አዷነች ኢነላሀ ማአሷቢሪን የምትለውን የአለሰህን ቃል ደጋግመህ አስታውሳት ይህበሽታ ስለያዘህ ትሞታለህ ማለትአይደለም
እኔ የደረሰብኝን ትንሽ ላካፍልህ ወደድኩ እደሚታወቀው ብዙመቻችን እህቶቻችሁ በሰው ሀገር እንገኛለን እኔም እደድል ሁኖ ጌታየ አላህ በበሽታ ይፈትነኝ ነበር ከጭቅላቴ ወደታች ደም ሲፈሰኝ ይሰማኝነበር
በዛላይ ህፃን ልጅነበርኩምንመናገር እዳለብኝኮን ለአሰሪወቸ አላውቅም ግን ግደታ መናገር ነበረብኝና እየተፈጠረ ያለውን ነገር አስረዳሆቸው ምን እዳሉኝ ታውቃለህ ወድሜ
በአፍሽ ደም ሲወጣ ካላየን ሆስፒታል አልወስድሽም አሉኝ ሆስፒታል ያድነኛል ብየ ሳይሆን ስበቡን ማድረስ ነበረብኝ ግን
አንተ ቢያስ ከኛ ትሻላለህ አንደኛ ሀገርህ ላይ ነህ በቋንቋህ ተግባብተህ በሽታህን ተናግረህ መፍትሄ ተሰገኛለህ በዚህም ፈጣሪህን አመስግን ካተም የባሰ እዳለ ተረዳ ያኔ ምንም ነገር እንደሌለብህ ይሰማሀል ወድሜ
እኔም ከአሰሪዎቸ ጠፍቸ ያገሬን ልጆች አግኝቸ ታክሜ በሽታየን አውቄ መዳኒቴን እየተጠቀምኩ ነው አልሀምዱሊላህ
ይህን ሁሉታሪኬን ለመናገር የፈለኩት አሞኛል ብለህ ተስፋ እዳትቆርጥ እና ከአንተ የባሱ እዳሉ እድትረዳነው ላበእስ ጠሁረን ኢንሻ አላህ ወድሜ
በመጨረሻ እህቶቸ እድሁም ወድሞቸ አላህ ለሱስል በጣም የምወደውን ነገር ስተው ከዛነገር የተሻለ ከሱጋ የተወደደን ነገር እድሰጠኝ ቤተሰቦቸም ጋር በአካል እደቀላቅለኝ የተከበረው ወር እየመጣ ስለሆነ በዱአችሁ እዳትረሱኝ ለአላህ ብላችሁ አስታውሱኝ
انا احبكم كثير😘💐🥀🌹
2 915
የ 6ኛው ዙር የተሳታፊዎች አንዳንድ እውነታዎች
🧡ደረጃ ውስጥ ካሉት መካከል ሁለት ሰዎች (hamada abuya እና kheyriya Abdellah) ወንድምና እህት ናቸው።
🧡 khayriya Abdellah አራስ እንደሆነች ሀማዳ ነግሮናል (መብሩክ)
🧡 Abdulmalik kebde (አቡሳብሪን) አንዱ የደረጃ ተወዳዳሪ ሲሆን እስልምናን ከተቀበለ 2 ዓመቱ ነው (አላሁአክበር)
🧡 Abdulmelik እና Abdurahman Zakir ደርቢ ናቸው (አንድ ሰፈር ውስጥ የሚፎካከሩ ሁለት ጓደኛሞች)
🧡 ተጨማሪ እውነታ ቢኖር ደስ ይለን ነበረ😄 ካለ ይንገሩን
2 915
አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ
ትናንት የዚህን ቻነል የደረጃ ተሸላሚ መጽሀፎቹን ለማቀበል ወደ አቡበከር ቃሲም ቤት አምርቼ ነበረ።
ደስ የሚልና ለሂወት ትምህርት ካገኘሁባቸው ውስን ቀናቶች የትላንቱ ቀን ለእኔ አንዱ ነበረ።
አቡበከርን ልጠይቀውና ልማርባቸው የምፈልጋቸውን ጥያቄ በልቤ አዘጋጅቼና አሰናድቼ ነበረ የሄድኩት።
ገና ሳገኘው ፈገግ ብሎ ተቀበለኝ። ረጅም ተስፋ የሚታየው፣ ለመቀመጥ ጊዜ የሌለው፣ ያለውን ነገሮች ሁሉ በተገቢው ለመጠቀም አስቀድሞ እቅድ ያለው ወጣት ሁኖ ነው ያገኘሁት።
በኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ 3 ዓመታትን በ 5 ኪሎ ዩኒቨርሲቲ ተምሮ በህመሙ ምክንያት ሊገፋበት አለመቻሉን አጫወተኝ።
ህመሙ ሲጀምረው የነበሩት የስቃይጊዜያት እሱ እየኖረበት ቢሆንም እኔ ግን ደግሜ ለማሰብ ሁላ በጣም ነበረ የከበዱኘ።
እሱ ላይ የደረሰውንም ህመም ሌላው እንዳይደርስበትና እንዳይሰቃይ በሚል እንቅልፍ የማይወስደው ወጣት።
አቡበከር ህመሙ በጣም እንደጎዳው ማሰብ አያቅትም ነገር ግን ሰፊ ጊዜውን ሰጥቶ ለሁሉም ሰው ግንዛቤን ለማስጨበጥ ሁሌም በጥረት ላይ ነው።
የ MS ህሙማንን ድጋፍ ማድረግያ ተቋም በመመስረትና ተቋሙን በሁለት እግሩ ለማስቆም እንቅስቃሴ ላይ ነው ሚገኘው።
ከአቡበከር ጋር ሰፋ ያለ ጊዜ ወስደን ብዙ ያወራን ሲሆን ሁሉም ለሂወት የሚጠቅም ሁኖ ነበረ ያገኘሁት።
ስላገኘሁክ ደስ ብሎኛል
ምናልባት አቡበከርን ማናገር ማግኘት ለምትፈልጉ
+251922484787 ላይ ይደውሉ።
አቡበከርን ከማግኘቴ በፊት ከ EBS TV ጋር ያደረገውን ኢንተርቪውን ተመልክቼው ነበረ። ምናልባትም ስለ ህመሙ ከራሱ አንደበት ለማድመጥ በተከታዩ ሊንክ ጋብዤያቹሀለው
http://www.youtube.com/watch?v=3zruKBgR3Z4
2 915
💚I Love You
አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ
ወላሂ ይህ ቻናል በጣም አሪፍና ሊበረታታ የሚገባው ልዩ ቻናል ነው። እኔ ለዚህ ቻናል አዲስ ነኝ እስካሁን ባለማወቄና ይሄ ሁሉ ነገር ስላለፈኝ ሀቂቀተን እንዲቆጨኝ አድርጋሗል። አላህ ሁሉንም ጨምሮ ይስጣችሁ እባካችሁ በርቱበት ለሙስሊሙ ወጣት ጥሩ ም መማሪያና ዲኑን እንዲያገናዝብ ሰአቱን ምን ላይ ማሳለፍ እንዳለበት እንዲያውቅ አድርጋችሗል። አላህ ይጨምርላቹ!!! ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ
2 915
የሞባይል ካርዱን ለመውሰድ ሊላክሎት የሚፈልጉትን ቁጥር በውስጥ ያስቀምጡልን
የሞባይል ካርድ አበናፊዎች
ከ werdah bint musemma እስከ kheyriyah abdella ያሉት 9 ተወዳዳሪዎቻቻን
2 915
💚Manesa mohammed
ውድ የኢስላም ወንድሞች እና እህቶች አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ ስለ ጥያቄ ና መልሱ ይህ ነው ብዬ መግለፅ ይከብደኛል the best page ለዚህ ፕሮግራም አዘጋጆች ይሄንን የመሰለ ጣፋጭ ስላከፈታቹልን አላህ በምትኩ የጀነተል ፊርደውስ በር ይክፈትላቹ እንዲሁም ለብርቱ ተፎካካሪዋች አላህ ይጨምርላቹ በመሸለማቹ ተደርቻለሁ አላሁ አክበር×2 👍👍👍👏👏👏 ወንድም አቡበክር ቃሲም አብሽር ያአሂ አላህ ህመም ነፃ እንዲያደርግህ ዱዐዬ ነው ስለ መልቲፕል ስክሎረሲስ አብዛኞቻችን ግንዛቤው የለንም በደንብ ቢሰራበት እላለሁ አላህ ያግዛቹ። አሁን ረመዳን ደርሷል አላህ ይህ ወርን አድርሶን ከሚጠቀሙበት ያድርገን አላሁመ አሚን ሁላቹንም ለአላህ ብዬ እወዳቹሀለሁ አላህ ይጠብቃቹ።
2 915
💚 المشتقا لرؤيا ربها
إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ يَهْدِيهِمْ رَبُّهُم بِإِيمَانِهِمْ ۖ تَجْرِي مِن تَحْتِهِمُ الْأَنْهَارُ فِي جَنَّاتِ النَّعِيمِ
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ ጌታቸው በእምነታቸው ምክንያት (የገነትን መንገድ) ይመራቸዋል፡፡ ከሥራቸው ወንዞች ይፈስሳሉ፡፡ በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ይኖራሉ፡፡
دَعْوَاهُمْ فِيهَا سُبْحَانَكَ اللَّهُمَّ وَتَحِيَّتُهُمْ فِيهَا سَلَامٌ ۚ وَآخِرُ دَعْوَاهُمْ أَنِ الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ
በእርሷም ውስጥ ጸሎታቸው ጌታችን ሆይ! ጥራት ይገባህ (ማለት) ነው፡፡ በእርሷ ውስጥ መከባበሪያቸውም ሰላም መባባል ነው፤ የመጨረሻ ጸሎታቸውም ምስጋና ለዓለማት ጌታ ይሁን (ማለት) ነው።
#አሰላምአለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካትሁ
እንዴት ናችሁ ውድ የኢትዩ ጥ& መ
አዘጋጆችና ተሳታፊዎች
ከኔጋር አልሀምዱሊላህ
ማሻአሏህ እህታችን ወርዳህ እንኳን ደሰ ያለሸ መብሩክ 💐❤️
#ለወንድማችንአቡበከር ለቀሸለት በነበር ኸይር ነበር ወይም ከኛ አንድ ሁለት ይውሰድና ያሸንፍ እያልኩ ነበር ለጓደኛየ 😀
አልሀምዱሊላህ በወንዶች በኩል አቡበከር በጣም በዚህ ዙር የሚደነቅ ነው አሏህ ይጨምርለት! ቀጥልበት ወንድማችን !!
አዘጋጆች ላደረጋችሁት ሁሉ ከጥያቄ ማውጣት ውጤት ከመሰራትና ለኛ ሸልማት እሰከማቅረብ ድረስ ያደረጋችሁትን ሁሉ ምንዳችሁ አሏህ ከፍ አድርጎ በጀነተል ፊርደወስ ይመንዳችሁ!!
አሏህ በቀጣዩ ዙር በሰላም ያገናኘን !
ባረከሏሁ ፊኩም ወነፈኣቢኩም ኢሰላመ ወልሙሰሊሚን!
2 915
💚 አቡ ሙስተጅዓብ
መሸአለህ አላህ ይጠብቀችሁ በዕውቀተችሁ ዕውቀት ይጫምርለችሁ በጣም ደስ የሚል ትምህርት ነው የቀሰምኩት በሰባቡ መፅሀፍቶችን እያገለበጥኩ ነበር ተፎካካሪ ነበርኩ ከ555 ጥያቄ ቡኻለ የግል ጉደይ ገጥሞኝ ብዙም አልተሰተፍኩም ከ4ኛ ደራጀ ወደ 9ኛ አሽቀንጥራችሁ ጠለችሁኝ መሸአላህ በጣም ደስ ይላል ይልማደባችሁ በኛም ይልማድብን እኔ ሰለደንቅ ማለልፈው ነገር ብኖር ሱማያዎችን ነው ወለሂ አጀይብ እያልኩ ነበር ###ወሪደ ቢንት ሙሰማ አላህ ይጫምርልሽ
2 915
💚kheyria abdella and her brother hamada abuya.
አሰላምአለይኩም ያ ጀማአተል ኸይር ፣ እንዴት ናቹህ ፣ በጣም ደስ የሚል የመማማሪያ ግዜ ነበር ያሳለፍነው አልሀምዱሊላህ ፣እናንተንም جزاكم الله خيرا . ላደረጋችሁልን ነገር በሙሉ እናመሰግናለን። ለቀጣዪ ዙር በጉጉት ነው የምንጠብቃቹህ إنشاءالله. From kheyria abdella and my brother hamada abuya.
2 915
💚Ñęimã Ãĥmêd
🌹ወአለይኩምሰላም ወራህመቱላህ ወበረካቱህ🌹
የኢትዮ ጥያቄ ና መልስ አዘጋጆች ጀዛኩሙላህኸይረን
ጊዜችሁን መስዋት አድርጋችሁ የማናውቀውን እንድናውቅ ስላደረጋችሁን አላህ ምንዳችሁን እጥፍ ድርብ አድርጎ ይክፈላችሁ
6ኛ ዙር አሽናፊዎች በሙሉ ፦ማሻአላህ አለይኩም አላህ ይጨምርላችሁ
2 915
💚 አቡበከር ኃይሉ
አሰላም አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ
ውድና የተከበራችሁ የዚህ ቻናል አዘጋጆች አላህ መልካም ምንዳውን ያብዛላችሁ ሙስሊሙን በእውቀት ለማበልፀግ እና የእውቀት አደረጃጀቱን በማመላከት የምታደርጉት ጥረት በጣም የሚያስደስት ነው በርቱ ተበራቱ አላህ ይርዳችሁ ለናንተም ለተሳታፊዎችም ባጠቃላይ ለሁላችንም አለህ እውቀትን ይጨምርል አሚን
የውድድሩ ፉክክር ደስ የሚል ነበር ውጤቱም እንደዛው እህት ወርዳን congratulations ብያለሁ አላህ ይጨምርልሽ ሁላችሁንም ለአላህ ብዬ እወዳችኋለው
ውድ የኢትዮ ኢስላማዊ ጥያቄና መልስ አዘጋጆች ወንድማችን አቡበከር ቃሲም ያቀረበው ሀሳብ ውስጤን ነው የነካው እናም ለእኔ የተዘጋጀው ሽልማት (መፅሀፉና ካርዱ) ለነሱ ማህበር ማበርከት ከተቻለ ለነሱ ብትሰጡልኝ ደስ ይለኛል።
ወሰላም አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ
2 915
💚Abubeker kasim
አሰላምአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ ያ ጀምዐ፣በጣም ደስ የሚል ፉክክር ነበር፤ እህታችን ወርዳ አላህ ይጨምርልሽ፣ጥያቄ እና መልሱን አዘጋጆችም አላህ የዱንያም የአኸራም ምርጥ ምርጡን ይሰጣችሁ.......
ለአላህ ብላቹ በዱአ አግዙኝ፣የ Multiple Sclerosis(MS) ተጠቂ ነኝ፣ከ MS ጋር ለ 5 አመት ኖሬያለሁ፣አልሀምዱሊላህ ከ ጓደኞቼ ጋር በመተባበር "የ መልቲፕል ስክሎረሲስ ህሙማን መርጃ በጎ አድራጎት" ማህበርን መስርተናል፣ስለ MS ግንዛቤውን ለማስፋት facebook ላይም "MS in Ethiopia" የሚል ፔጅ አለኝ፣፣https://www.facebook.com/Multiple-Sclerosis-MS-in-Ethiopia-1449246668728359/
2 915
💚Werdah bint musemma
ወአለይኩም አሰላም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ
በቅድሚያ በኢስላም ጥላ ስር ላስጠለለን፣ የዚህ ምርጥ ስብስብ አካል ላደረገንና አስጀምሮ ላስጨረሰን ሀያሉ አላህ(ሱብሃነሁ ወታዓላ) ተደራራቢ ምስጋና ይገባው (አልሃምዱሊላህ)
በመቀጠል ጠቃሚ እውቀቶችን በመመገብ በተለይ አብዛኞቻችን ፍፁም የማናውቃቸውን የእውቀት ዘርፎች በማስጨበጥ ሁሌም ከነበርንበት በእውቀት ከፍ እንድልን ለምትደክሙት ውድ የኢትዮ ጥያቄና መልስ አዘጋጆች አላህ ጥረታችሁን ወዶ ይቀበላችሁ
ጀዛኩም አላሁ ኸይረን ፊዱኒያ ወል አኺራህ
የ6ኛው ዙር አሸናፊዎች በሙሉ
አላሁ አክበር
አላሁ አክበር
አላሁ አክበር
ማሻ አላህ አለይኩም አላህ በእውቀት ላይ እውቀትን ይጨምርላችሁ
እንደዚሁም እልህ አስጨራሽ ውድድሮችን በማድረግ ይበልጥ ጓግተን እንድንማር ላደረጋችሁን የዚህ መድረሳችን ኮከብ ተሳታፊዎች በሙሉ አላህ(ሱብሃነሁ ወተዓላ) ጠቃሚን እውቀት ይወፍቃችሁ
ወንድማችን Abubeker የዚህ ዙር ጀግና ነበርክ በርታ አኺ
ሀቂቃ በስም ለመዘርዘር ባልችልም ሁላችሁም ምርጥ የኢስላም ልጆች ናችሁ
በመጨረሻም ከምታስተላልፉልን እውቀት በተጨማሪ በተበረከቱልን እጅግ ምርጥ መፅሃፍት ድርብ ደስታ ተሰምቶኛል።
ሀቂቃ በጣም ደስ ብሎኛል አላህ ዘላለማዊ በሆነችው ጀናህ ያስደስታችሁ
ስለሁሉም ነገር ጀዛኩም አላሁ ኸይረን
2 915
የዚህ ቻነል ወናው አላም የተዘጉ ቁርዓን ኪታብና መፅሐፍቶችን አዋራቸውን ጠርገን እንድንከፍትና እንድናያቸው ለማስቻል ነው።
ጥያቄዎቹ ያን ማድረግ ከቻሉ ነው ለኛ ትልቁ ደስታችን። እንደሆነም ባለሙሉ ተስፈኞች ነን።
ዋናው ቁም ነገር ማሸነፍ አለማሸነፍ ሳይሆን ወደ መፅሐፍቶች ተመልሰናል ወይ ነው
ስትሳተፉ የነበራችሁ ሁሉ አሸናፊዎች ናችሁ
እናውቃለን የኔትወርክ ችግር የሰዓት አለመመቻቸት ሁኖ እንጂ ሁላችሁም ማለት በሚያስችል መልኩ በተሳትፏቹ ትክክለኛ መልስ ነበረ ስትሰጡን የነበረው። ጀዛኩሙላኽይረን።
2 915
አላሁመ አሚን
ያው ሽልማቱ ያንስባቹሀል እንጂ ብዙ አደለም።
ለፍታችሁ ጊዜያችሁን ሰውታቹ ከኛ ጋር ስለነበራቹ ማስታወሻ ትሆን ዘንድ ነው ያዘጋጀናት
እናመሰግናለን ከድ
