ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
前往频道在 Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
显示更多1 721
订阅者
+224 小时
-47 天
-1530 天
帖子存档
Meet one of the poets we've spotted following our call to artists. This emerging poet is ready to share her perspectives and express her self through poetry.
#AdomiaFekede #gitemsitem #poeticsaturdays #migbarsiraj
#አዶሚያፈቀደ #ግጥምሲጥም #ግጣምዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
“Feelings along the Sidewalk” is open now!
Find it on the Sidewalk of the Italian Cultural Institute and, online on http://tibebbeadebabay.org
#tba #tibebbeadebabay #digitalart #digitalartfestival #artinaddis
በተለያዩ የግጥም መድረኮች ላይ ተወዳጅ ስራዎቹን የሚያቀርበው ኤሊያስ ሽታሁን የራሱን መጽሐፍ ለአንባቢያን ሊያደርስ በተቃረበበት ጊዜ በጥዑም ግጥም ዝግጅታችን ላይ የምግበር ሲራጅን ግሩም ግጥሞች በሱ አቀራረብ ሊጋብዛችሁ ተዘጋጅቷል።
#ኤልያስሽታሁን #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ
ፍርፋሪ ታሪክ
- - - — - - -
"ከጅምሩ ማን ፍጠር አለህ እንዲህ ያለ ነገር? ይሄ ነው ፍርድህ? ዛሬስ አትወርድም፣ አትጽፍም ከግንባሩ ላይ ኃጢያቱን የሚያጽፍ ድፍን የቀዮ ጎረምሳ ተሰልፏል..."
"ተው አርዮስ! ተው! ከፈጣሪ አትጋፋ!...አዋቂ ነው...ተው"
"ድንቄም አዋቂ! ሲታወቅ እንዲህ ከሆነ እውቀት በአፍንጫዬ ይውጣ። አይገርምህም!"
"ለአንዲት ጋለሞታ ፈጣሪህን...ትክዳለህን!"
"ጋለሞታ? ጋለሞታ አልህ?...የት አየህ ስትዘሙት?...የት?...አዘሟች ከሌለ ዘማዊት ትፈጠር ይመስል።እንደወይራ፣እንደቀጋ አትበቅል ዘማዊት..."
"ይወራል።...ድፍን መቂ እሱኑ ነው የሚያወራው"
"እና አመንህ አንተ?"
"ምን አማራጭ ይኖራል? ሰው ተኩኖ።...ሁሉ አምኗል እኔ ማነኝና ሰው ያመነውን አላምን የምለው?"
"አልገባኝም?"
"አይገባህም። አንተ ብቻ ከሰው፣ ከቀየው ተነጥለህ፣ ለዘማዊት ሴት ጥብቅና የሚያስቆምህ ነገር። ብቻህን ከአድባር ትጋጫለህ?...ሴት ጠፋ? ከሸርሙጣ?"
"ዝም በል አንተ!!...ምፅዋ ሸርሙጣ አይደለችም።"
"ነች!"
"አይደለችም! ምፅዋ ሸ...ር...ሙ...ጣ... አይደለችም!! ትሰማኛለህ...አንተ ካላባለግኃት አንዲት ምስኪን ሯጭ ከመሬት ተነስታ ሸርሙጣ አትሆንም።"
"ትጠረጥረኛለህ?"
"አላምንህም"
"አህመድንስ ትጠረጥራለህ? ከእርሳቸው አፍ ነው ቀድሜ የሰማሁት።"
"እሳቸው ቅዱስ ገብርኤል ናቸው? የማልጠረጥራቸው?"
"እና እርሳቸውንም ጠርጥረህ?"
"እንክት! ምፅዋዬ እኮ ናት!"
"በል ወግድልኝ ልሂድበት መንገዴን! እውነትም አሪዎስ!...ያሳደጉህ የእናትህ ጡት ሳይሆን ስምህ እንደሆነ ገና ዛሬ ገባኝ!"
"የምን መንገድ?...የሰው መንገድ አበላሽቶ ...ወዴት?"
"የማን መንገድ ተበላሸ? አንተ ኩሩሩ ወግድልኝ!"
"የምፅዋ። የምስኪኗ...በወሬ ገፍታችሁ የጣላችኋት።...ህልሟ መንገዷ አልነበረም? እ!"
"የምን ህልም አላት ደግሞ ሸርሙጣ? ምን ትሰራበታለች ቢኖራትስ?"
"አንተም አለህ አይደል፤ አይደል እሷ? ሯጭ ነበረች ታውቃለህ።... አቦ ሸማኔ የሚያሳድድ ፍጥነት ነበራት።...የጥንቸል ሳንባ ምታስተፋ ነበረች ይህን አንተም ታውቃለህ....ምን ያረጋል!"
"ጋለሞቶች።"
"አልገለሞተችም።....አንተ ውሻ እንዳልዘነጥልህ በዚህ ከዘራ!"
"ኧረ በህግ...በህግ አምላክ!...ምን ታረግበት ነው እሱ...ኧረ ኡ!...ኡ!...ኧረ በህግ!..."
"ልጄን!...አይኔን!...በማህፀኗ...እንደያዘች...አስኮበለላችኋት...ምፅዋዬን አሸሻችኋት"
"ተው አሪዎስ!...ተው አንተ ከሐዲ!...ባለውለታህን?"
"የት ብዬ ልፈልጋት እሺ አሁን?...ንገረኝ!...እ!..."
"እንካ ቅመስ ይችን ለምፅዋዬ!!...እ!...ይህችን ደግሞ በማህፀኗ ይዛ ለተሰደደችው ልጄ...እንካ!!"
"ኡ!...ኡ!...ኡ!...ኧረ የሰው ያለህ!!!"
"የት ብዬ ነው የምፈልጋት አሁን?...እ!...ምፅዋዬ...የበኩር ልጄን እናት?"
©ምግባር ሲራጅ
ዘንባባ
ከገፅ 132 - 134
#ዘንባባ #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
ግጥም ሲጥም አዲስ ተሰጥዖ ፍለጋ ባደረገችው ቅኝት ካገኘቻቸው ምርጥ ገጣሚዎች አንዱ የሆነውን ቃለአብ አባይነህን ተዋወቁልንማ።
#ቃለአብአባይነህ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
[♣️እብን ይወክላል ልብን?♣️]
የመውደድ ገላ መዓዛ
ከአሪቲ ዛላ መዝዛ
ሸተተኝ የማፍቀር ለዛ።
ከአልባጥሮስ፣ ከእጣን፤ ከርቤ
የሰማሁት፤ ተደልቄ እንደ ድቤ
ተሽቀንጥሬ እንደ ፈትል
መሬት ስሜ ልክ እንደትል
ፍቅር ተማገኝ መልኩ
ታየኝ የተዘነጋ ልኩ፡፡
♣️
ኮከብ ከመሬት ተለቅማ
ሰማይ እንደ ጉንጭ ተስማ
እንደ ቃላብ ለፍቅር ተሞ
ድምጽ አውጥቶ እንዳታሞ
'ገዳም ሳይቀረው ገሞ'።
♣️
ልቡን መውደድ አሸተው
ድካሙ ዓይኑን ሸተተው
[የጠጠሮች “ቋ..ቀጭ” ዜማ
በአፍንጫው ጠረን ጽፎ
የብሌኑን ሞራ ገፎ]
ሄደ፤ ሄደ በረረ
ሽታው ግን ዕጹብ ነበረ፡፡
ለ ምግባር ሲራጅ
#ቶማሰአድማሱ #ምግባርሲራጅ #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
ለአዳዲስ ከዋክብት ሰማይ ለመሆን ያወጣነውን ጥሪ ተከትሎ ካገኘናችው ምርጥ ገጣሚያን አንዷ - ሮዛ ሽታ (ግሩም ነን መቼም)ን ተዋወቁልን!
#ሮዛሽታ #ግሩምነንመቼም #ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
Gitem Sitem presents you the marvelous Migbar Siraj and his works along with other outstanding poets.
Poetry, Music, Campfire, Foods and Drinks and so much more.
Please RSVP by sending your full name to gitemsitem@gmail.com or @seifdman on telegram.
ግጥም ሲጥም ልዩ ባለቅኔ የሆነውን ምግባር ሲራጅን ከሌሎች እጹብ ገጣሚያን ጋር ይዛላችሁ መጥታለች!
ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ የእሳት ዳር ጨዋታዎች፣ ምግብና መጠጥ እንዲሁም ሌሎች መዝናኛዎች አሉን።
ዝግጅቱን ልዩ ጥሪ የተደረገላቸው እና ቀድመው ቦታ ያስያዙ ሰዎች ብቻ በአካል ይታደሙታል። (መግቢያ አናስከፍልም) ቦታ ለማስያዝ በኢሜይል ወደ gitemsitem@gmail.com ወይም በተሌግራም @seifdman ላይ ሙሉ ስማችሁን እና ስልካችሁን/ የቴሌግራም አድራሻችሁን ላኩልን።
https://goo.gl/maps/EiCpLt2RCoYHLXoK7
በገለጥነው የኛው ቀለም
ጥዑም ግጥም እናጣጥም
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም #ምግባርሲራጅ
https://goo.gl/maps/EiCpLt2RCoYHLXoK7
Gone ... Gone ... Gone
I don't know where I am
Its dark
I only see nothing
Nothingness
That's when I knew I went too far
Too far gone
I don't know where I am or who
I kept on asking
All there was was a road
So I kept on going
gone ... gone ... gone
I don't know where I am
It getting too dark
Too blurry too vague
I only see nothing
Nothingness
Thats when I knew I went too far too far gone
I don't know where I am
or Who
Who I was
Who I am
Who I will be
Even who I am being
I kept on asking
All there was was a road
So I kept on going
There was times
I wished I could go back
I tried...
Some how no matter which way I tried to go all roads seems to lead me to the same destination
Nothingness
Now I am facing the Dark
I couldn't let it sink in to my heart
I didn't wanted to go in to it
I didn't wanted to pass through it
Or "Let it" pass through me
But it felt like I had no choice
I can't go back and
I can't stop either.
Ted Estif
#TedEstif #gitemsitem #poeticsaturdays #artinaddis
የጥቅምትን ወር የግጥም መጽሔት እንሆ አቅርበናል።
በቀጣይ መጽሔታችን የእናንተኑ ስራ እንጠብቃለን።
በ shorturl.at/gwMO6 ገብታችሁ እዩልን፣ አውርዳችሁም የራሳችሁ ልታደርጉት ትችላላችሁ፣ አንብባችሁ ስታበቁ ግን አስተያየት አቀብሉን።
ግጥማቸውንና ምስሎቻቸውን እያቀበሉ ወሩን ላደመቁልን ሁሉ ምስጋና ይድረስ!!!
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥበብበአደባባይ #የግጥምመጽሔት
#gietmsitem #poeticsaturdays #artinaddis #poetrybooklet
Cover Photo Credit: ማርቆስ ዘመንበረ ልዑል
ሠላም ሠላም ጤና ይስጥልን ፣ ቅዳሜ ጥቅምት 28 ቀን 2013 (ከቀኑ 10:00 ጀምሮ) የመስመር ላይ (ኦንላይን) ግጥማዊ ቅዳሜ እናስተናግዳለን! ይህ ምናባዊ የጥበብ መድረክ ለሁሉም ሰው ክፍት ነው።
"ዙም" ላይ ይቀላቀሉ ወይም በፌስቡክ ቀጥታ ይመልከቱን! ለማንበብ ፍላጎት ካለዎት አስቀድመው በውስጥ መስመር መልዕክት በመላክ ያሳውቁን፡፡ እንደ ሁልጊዜው ሁሉ ያለ ቋንቋ፣እድሜ እና ርዕስ ገደብ አምስት ደቂቃ ይኖርዎታል። እዚያው እንገናኝ!
https://us02web.zoom.us/j/71147805916
Hey everyone, this Saturday, November 7th at 4pm, we will host online Poetic Saturdays! Virtual Poetry is open to everyone. Call in and join by Zoom or watch live on Facebook! If you're interested in reading, let us know beforehand or, if you join in on Zoom, send us a private message. As always, you'll have five minutes and we encourage all languages, all ages, and all topics. See you there!
https://us02web.zoom.us/j/71147805916
የምስል ጥበብ ስነ-ግጥምን ስታውቃት. . . !
When photography meets poetry...!
@ribkiphoto
#ርብቃሲሳይ #ribkasisay
#ግጥምሲጥም #gitemsitem
ሰማይ ሆይ!
( #በድጋሚ_የተገረበ )
ተስፋችን አረግንህ
የእግዜር መቀመጫ
አንጋጠን አየንህ
እየጠፋን መውጫ
ይኸው ለዘመናት
ስርህ ተኮልኩለን
ስንባዝን ስንማስን
ስንከስም ስንባክን
ይኸው ለዘመናት
ይዘኸው የላዩን
ስታየን ስታየን
ስታየን ስታየን
ዘመኖች አለፉ
ባንተ እንደተከፉ
የተነኑ እንባዎች እንዳርከፈከፉ
ባትሰማም ታያለህ
አምናለሁ ታያለህ-ይህ ግጥም ከታየህ
ሰማይ ሆይ . . . ከንቱ ነህ!
ቱ!
ሰይፈ ተማም 2003
I kill the poet in me
,
,
I kill the poet in me,
In a way catastrophic
But not sudden or uncalled for
No,
I don't mean the entropic darkness of being a poet,
Which arises from a nature of sensetivity to feel every life,
like absorbing an ocean in a single breath,
Somehow a rather delicate state of the heart
Because at the end,
No matter what, the sigh is about finding an antidote to celebrate the ordeal of being alive.
But mine is indifferent.
I kill the poet In me rather in the process
In the process
Where the heart suffers from too much reason
While the mind from reminiscent of the heart
In a quest either to settle or to conquer
And many attempts in between,
None festive.
In the process to accustom,
of feeling less and thinking more
In an ambition to evolve
to learn
to tame
to detach from memory,
to detach from emotion,
to detach from time,
All consequences of the mind
Kill the poet in me.
But what is a poet without a profound attachment or vulnerability to feel anyway?
And what good does a poet's mind,if not the heart anyway?
Here is a calendar of the major events you might want to attend for the next 15 days. You can just save the image or download the pdf file here: https://bit.ly/369fGZJ. @linkupaddis
እነማንን ይዘንላችሁ እንደምንቅርብ ለማወቅ ገጾቻችንን በቴሌግራም፣ ፌስቡክ እና ኢንስታግራም ተከታተሉን።
https://www.facebook.com/gitemsitem
https://www.instagram.com/gitem_sitem
https://t.me/seifetemam
ዝግጅቱን ልዩ ጥሪ የተደረገላቸው እና ቀድመው ቦታ ያስያዙ ሰዎች ብቻ በአካል ይታደሙታል። በዙም እና ፌስቡክ ደግሞ ያላችሁበት ድረስ እንመጣለን።
በገለጥነው የኛው ቀለም
ጥዑም ግጥም እናጣጥም
#ግጥምሲጥም #ግጥማዊቅዳሜ #ጥዑምግጥም
https://goo.gl/maps/EiCpLt2RCoYHLXoK7
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
