ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
前往频道在 Telegram
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
显示更多1 719
订阅者
-224 小时
-77 天
-1830 天
帖子存档
We are opening up our platform for content creators!
If you think you are a skilled writer and if you have blog articles you have written on social commentary, fashion, lifestyle, entertainment, music, films, etx. submit them via our email linkupaddis@gmail.com or submit them to @linkupaddisofficial.
If they meet our editorial guidelines, we will put them up on our website and our other platforms. @linkupaddis
ኤልያስ ሽታኹን
* * * * *
አሳቢያን
ፍቅር የለም ባይ ናቸው
በቃ እኔ አላስብም
"አፈቀርኹላቸው"
ፈላስፎች
የተጋባን ሁሉ
"ዘይትና ውኃን
እሳትና ብረት
ይመስላሉ"
አሉ፡፡
አፍቃሪያን ደሞ
"ዘይትና ውኃም
እሳትም ብረትም
ተዋህዶ አይተናል
በዕውቀት ለሚኖር ይህ እንዴት ይገባል?"
(ብለናል)
ፈላስፋ ሰልፍ ወጣ
ፊሀፊ ሰልፍ ወጣ
አሳቢ ሰልፍ ወጣ
"ፍቅር የለም" በሚል መፈክር ሸክፎ
አፍቃሪ ግን የለም ከሚስቱ ተቃቅፎ፡፡
* * * * * * * * *
(ኤልያስ ግን የለም ከሚስቱ ተቃቅፎ)
[ አዲስ ንጋት ]
:
ቀስ
ቀስ
ቀስ ቀስ
ሄድ መለስ
እጥፍ ዘርጋ ሰበር ሰካ፣
በውዴታ
አንቺን ዕይ‘ት አንቺን ነካ፣
አመድ ገፄ
በ ፀዳልሽ እስኪፈካ፡፡
ፍክት
እርክት
ደስታን ንክት
ደግሞ
አንዴ ቆም
ከመወዝወዝ
ከመናናጥ ለአፍታ እርፍ፤
ዝለታሙን
መታከቴን ጥልት እንትፍ፤
ከእርፍታ አፀድ
ከእፎይ ዛፍሽ ብርታት ቅጥፍ፡፡
ቅጥፍ
ቅጥፍ
እርፍ
እርፍ
እርግፍ፣
እርግፍ የክፉን ግፍ፡፡
እንትፍ
እንትፍ
ብርታት ሲገኝ
ዝለትን ጣል ብሎ ሀክ እንትፍ፡፡
ደግሞ እንዳዲስ
ላ‘ዲስ ማረፍ
ሄድ መጣ ወረድ ወጣ፣
ድብርታሙ ድባቴዬ
በሀሴት ጅራፍ እስኪቀጣ፣
ለእርካታዬ
አዲስ ንጋት
አዲስ ፀሐይ እስክትወጣ፡፡
ዕልም
ዕልም
በራስ መንደር በራስ ዓለም፣
ንጋት ማየት ነገን ማለም፡፡
ዕይት
ቅኝት
ልይት
በአዲስ ዕለት
ፅልመት ገድሎ
ንጋት ወልዶ ተስፋን መሳብ፣
ከፍ ካለው
ከከፍ እርካብ ከመንፈስ ካብ፣
ተስፋ አግኝቶ
ዛሬን ዐይቶ ነገ እንዲሳብ…!!
©️ዳግም ሔራን
አሪቲ ጎፈሬ
ቄጠማ ከመከም፣
ያስራ አንዱን ደዌ
ዳብሼ ልታከም
ተውረግርጋ መጣች
ኮረዳ መስከረም።
የሰኔ ምንጣፍ ላይ
ሃምሌን ተንተርሳ
ነሀሴዋን ለብሳ
ባያት ደሜ ሞቀ፡
አምና መጣች ብዬ
ጥላኝ መኮብለሏ
ካቅሌ ላይ ተፋቀ።
ጣለኝ ያልኩት ገዴ
ቅኔ ቀን ሲያዝብኝ፡
ጭቃዋ ላይ ወደቅሁ
አደይ በቀለብኝ።
ኮረዳ መስከረም...
ይቺ በላዔ-ሰብ
ይቺ ድራኩላ...
የዘመን መንትያ
ክራንቻዋን ስላ፡
ያረጁ ዐይኖቿን
እንደልጅ ተ´ኩላ
አምናና ካቻምና
ያስተረፈችውን
እድሜዬን ልትበላ፤
መጣች እፍረት የላት
መጣች ረፍት የላት።
እሷ ምን ቸገራት?
ደንግላ ስትመጣ
አቅፌ የምለቀው
ቆዳዋ ይፋጃል...
እሷ እየታደሰች
እሷ እየደምቀች
የኔ ቀን ያረጃል።
መጣች ነጋ ደግሞ
መጣሽ ነጋ ደግሞ...
ኮረዳ መስከረም...
አወይ ጅል መሆኔ
ጡትሽን ማመኔ
ዳሌ ቅንፍሽን
ልታቀፍ ማለሜ፡
ለሚሸሸኝ ገላ
እድሜ መሸለሜ፡
ባከምሽኝ በወሩ
አርጅተሽ ስትሄጂ
ደግሞ መታመሜ፣
በያመት ስትደምቂ
በያመት መክሰሜ።
መስከረም ኮረዳ
ውበትሽ ሊከዳ
ሊሄድ ሊሸሽ ገላሽ
ለምን ይሞቀኛል
ደስ ደስ ይለኛል
አካለ ቢስ ጥላሽ?
ኮረዳ መስከረም
ምን አለሽ አደንዝዝ
ያምና ክዳትሽን
ካይምሮ የሚደልዝ
«ነበር!» የሚያስረሳ
የወደቀን ፍሬ
አብዝቶ ሚያስነሳ፤
ያበረድሽው ደሜን
ከራርሞ የሚያግል
ዝንትዓለም ተኝቼሽ
ያስመሰለሽ ድንግል።
አፍዝ ምን አለሽ?
መስከረም ኮረዳ፡
በአሮጊት እስትንፋስ
በልጅ ልስልስ ቆዳ፣
የሚያውረገርግሽ
ችክችካ ድለቃው
ሄደሽ ተደምስሶ
ትዝታ እስኪቀዳ፡
እንደ አምና ካቻምናው
እስክንከዳዳ፡
እድሜ ምናባቱ
ይሄው ረጲሳ
ይኸው ረገዳ።
(ቼቼ... ሼሼ... ቼቼ)
[እንኳን አደረሰን!]
የአምና ግጥም....
©️ረድኤት አሰፋ
Tibeb is back!
Tibeb Online in collaboration with Tibeb be Adebabay brings a range of physical, digital, and hybrid cultural and creative experiences featuring the works of artists, creatives & curators from different walks of life.
This year’s experience aims to support cultural networks within Ethiopia, facilitate knowledge sharing and build the capacities of creative professionals through free and inclusive platforms for exchange.
With this in mind and with the broad theme “Art to Earth”, we call on artists, creatives and curators from all disciplines to submit their ideas for cultural activities and creative expressions that showcase the overall value of art, as well as its power to address a range of social and environmental issues.
More information is put on the attached posters. Good luck!
@Tibeb_Be_Adebabay
🌼🌼🌼 የኢትዮጵያ አየር መንገድ 🌼🌼🌼
የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ከ ኢትዮጲያ አየር መንገድ ለ ቴሌግራም ገፃችን ተከታታዮች ማበረታቻ የተዘጋጀ የ 50,000 ብር ስጦታ ‼️
ያጋሩ ይሸለሙ 💰💰
በመጀመሪያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ 2013 የበጀት ዓመት ከ 100 ቢሊዮን ብር በላይ በማትረፍ ከ አፍርካ 1 ኛ ከዓለም 9 ኛ ደረጃን በመያዙ የተሰማንን ጥልቅ ደስታ ለመግለፅ እንወዳለን ::
በመቀጠል አየር መንገዳችን ለቴሌግራም ቻናሉ ተከታዮች እንደ ማበረታቸ የሚሆን 1ሺህ ሰዎችን እድለኛ የሚያደርግ የ ያጋሩ ይሸለሙ ፕሮግራም እስከ መስከረም 5 /2014 ድረስ አዘጋጅቷል‼️
የ 50,000 ሺህ ብር ስጦታ አሸናፊ ለመሆን መከተል ያለቦት መመሪያ ከታች እንደሚከተለዉ ቀርቧል 👇👇
በጥንቃቄ ያንብቡ‼️
1/ በመጀመርያም ተሸላሚዉ የቴሌግራም ቻናላችንን ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ መቀላቀል አለበት👇👇👇
https://t.me/joinchat/iAUjPBFY6Lk4ZDhk
https://t.me/joinchat/iAUjPBFY6Lk4ZDhk
2/ በመቀጠል ተሸላሚው ይህን መልዕክት ለ 50 ሰዎች ወይም በተለያዩ ግሩፖች ላይ ሼር በማድረግ 50 ሰዎችን ወደ ቻናላችን ማስገባት ይጠበቅበታል
3/ በመጨረሻም ኩባንያችን ከ ኢትዮ ቴሌኮም በሚያገኘው የዳታ አናላይቲክስ መረጃ መሠረት አሸናፊዎችን በመለየት በእጅ ስልካቸው በመደወል ሽልማታቸውን የሚያስረክብ ይሆናል፡፡
ቻናላችንን ይቀላቀሉ 👇👇
https://t.me/joinchat/iAUjPBFY6Lk4ZDhk
@ethiopian_airIines
✈️ ይፍጠኑ , አይዘናጉ ይህ እድል የእርስዎ ሊሆን ይችላል እስከ 50,000 ብር ያሸንፉ‼️
I was just passing through.
Or time, through me.
I froze or time did.
And just Like that,
Of all the places in the whole world, I had nowhere to be.
I had nowhere to return to.
______
እነበርኩበት ላይ
አምናን
አሁንን
ነገን
ሁሉን መምሰል መስዬ
ያለመለወጤን ሀቅ
ለመለወጥ ምሥጢር ጥዬ
አቆያየቴን
አጠባበቄን
በእርምጃ ሳሰማምር
የሚገፋኝን፤
ቀኔን ልገፋ ስዳክር
ሁሉ ጥሎኝ ከንፎ
ሁሉን ጥዬው እየከነፍኩ
አንቺን ብቻ አትርፌ
ዓለሙን ሁሉ ከሠርኩ!
[የማይደግፈኝን ደግፌ
ወደምቀርበት የምመጣው
የማልበላውን
ተሸክሜ የምወጣው
መቆሜን አልፎ እየቻለ
መንገድ አላራምድ ያለኝ
በእህል ምትክ የሚጎረስ
ሠው፤ ህይወት እየራበኝ...
ይህቺን ታህል...
እያለፍኩበት የምኖረው
አሁን ስፈልግ ነው
ሌላ አሁን ያከተመው!]
Even when I say I haven't changed a bit,
I have changed a lot.
Cos I never used to say that!
Yes I contradict my self.
And that's what kept me in one piece!
ቆሜ
መዳከሜን ላባብለው
የተራመድኩትን ባስተውለዉ
እየሄድኩ አለመድረሴን ሊያስረዳ
የተራማጁ ሲገርመኝ
ጥላዬ እርምጃዬን አስከነዳ...
[በዐይንሽ የልቤ ይደርሳልና
መሰልቸቴን እገስጻለሁ...
አለመምጣት ፊቴ ቆሞ
በመጠበቄ እረካለሁ..
ለመተው ብናስተውለው...
የሚያልፍብን
የምናልፍበት
ጊዜ ይደናበራል
መንገዱ እየነጎደ እግራችን ቆሞ ይቀራል፤
ምንገዶን...
መቆሚያ ካለ
ተስፋ አጥግቦ ያሳድራል!]
እንግዲህ...
እውነቱ እያየነው
ውሸት የሚሆንበት ቀን አለው...
ልክ አለመለወጤን እያስረዳሁ
የከበበኝ በሙሉ አዲስ እየተካ ነጎደ
የምደርስበት ዘንድ ሳልደርስ
የምደርስበት ደርሶኝ ሄደ...
ጊዜ በጎኔ አለፈ
አዲስ ትናንት አስቀረሁ
ያልኖርሁት ዕለት ትዝ ይለኛል...
አልተለወጥኩም ብል ማን ያምነኛል?
[ሁሉ ረግቶ
ሩጫው ላይ
የምረጋበት ቢያሳጣኝ
መቆሜ ነው መጽናኛዬ
ወደጥርስሽ የሚያመጣኝ...
መድረሻዬን ሊመትር መሰለኝ
ጥላዬ ቀድሞኝ ሮጧል
ስንዝር ብጨምር አልቀድመው
ወዴት እራመዳለሁ?
ወደአመጣኝ ዘፍጥረቴ
ወደእቅፍሽ እመለሳለሁ!
በአንቺ ተስፋ ለመለምኩ እንጂ
ለምለም እንጀራ ቢጠቀለል
ለዳረጎት ቢጣል ከአፍ ላይ
ነፍሴ ተርባ አታውቅም
ቀምሳ ከማረፍ ከመንካት
አንቺን ከመጉረስ በላይ..]
ትቼሽ
እንደመቆም
ጥዬ መንገድ እገባለሁ
እንደአሁን
ልክ ስጠራው እንደሚያልፈኝ
እያለፍኩ እጠብቅሻለሁ
I was just passing through.
Or time, through me.
I froze or time did.
And just Like that,
Of all the places in the whole world, I had nowhere to be.
I had nowhere to return to,
I have no where to be, but you!
©️Mark O's
አንድ ሰሞን
በህይወት ሰሌዳ ደስታና መከራ ተፃፈ
ሁሉም አንድ ሰሞን ሁኖብን አለፈ
ሁሉም አንድ ሰሞን
በደስታ መሽሞንሞን
ፌሽታ ላይ አቁሞን
አንዱ ሰሞን ሊያልፍ
በስሜት ሲያንሳፍፍ
ህላዌን ሲያስቀዝፍ
ደሞ ላንዱ ሰሞን ምንዱባን ሲወዝፍ
መከራን ስንረሳ በሀዘን ልንቀጣ
የአንድ ሰሞን ችግር ከቤታችን መጣ
ጥለቱ አደፈ
ኩታችን ጣለን
የዚህ ሰሞን ነገር ሀዘን አስጠለለን
ማቅ እየለበሰን
ሙሾ እያወረድን
ደረት እያስመታን መከራ ላይ ጥሎን
አፈር አስበትኖ
በመቀጣት እንባ አይናችንን ኩሎን
አንዱ ሰሞን ሲያልፍ ለሌላው እየታጨን
ለደስታ እስክስታ ለሀዘን ጠጉር እየነጨን
እኛ እንደሆን አለን
በህይወት ሰሌዳ ደስታና መከራ ተፃፈ
ሁሉም አንድ ሰሞን ሁኖብን አለፈ
የአንድ ሰሞን ትከሻ እስክስታ እንዳልወረደ
በዚህ ሰሞን ዝሎ ደረት ሙሾ አወረደ
እልል ይል የነበረ
አፋችን በፌሽታ
በሰሞን ተቀየረ
በዋይ ዋይ እሪታ
አንዱ ሰሞን ሲያልፍ ለሌላ እየታጨን
ለደስታ እስክስታ ለሀዘን ጠጉር እየነጨን
እኛ እንደሆን አለን
©️ዳጊፋ
#poeticsaturdaya #gitemsitem
እነሆም የመጀመሪያ እርምጃ
እኔ ሕይወትን ብዙ አልችልበትም። እንዳመጣልኝ ነው። እግዚአብሔር ግን እንደ እሱባለው አበራ ያለ ጓደኛ ሰጥቶ ከራሱ ጋር አብሮ የእኔንም አለመቻል ይሸፍንልኛል። ያጎደልኩትን ይኖርልኛል።
ዝርዝሩ ብዙ ነው። ብቻ ግን የመጀመሪያ የልብወለድ መጽሐፌን እኔም እንደ እንግዳ ሆኜ "በየት ገባ?" "በየት ወጣ" ሳልል እጄ ላይ አምጥቶ አስደንግጦኛል። እነሆም የመጀመሪያ መጽሐፌ ዛሬ በገበያ ላይ ውሏል። እንደምትወዱት አስባለሁ። ለደስታዬ ደስ ለሚላችሁ ሁሉ አብዝቼ አመሰግናለሁ።
የመሸበት እንግዳ የምታስተናግዱ ከአሁኑ ሰዓት ጀምሮ መጽሐፉን በጃዕፋር መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ ! መልካም ንባብ !
አሳብ
ስለ ማሰብ ላለማሰብ
ማሰብ ባያስፈልግ
ምንኛ ደግ ነበር አሳብ ተሰንጥቆ
አሳብ እስቲጠግግ
'ካሳብ አሳብ በልጦ
'ላሳብ አሳብ ቆርጦ
አሳብ 'ካሳብ መርጦ
የሚታሰብ አሳብ..?
...ሰበብ!
ላለማሰብ:
ሰበብ... ላለመንቃት
ሳይጀምሩ ማሰብ..
ሰበብ ማበጃጀት
እፍፍፍ...
እውነት: ይሁን ቅዠት!
ቅዠት 'ያሳብ ጉዞ
አሳብ ተያይዞ
ካሳብ ላይ ተመዝዞ
አሳብ ተጎዝጉዞ
በሰበብ ሀዲድ ላይ
እየተጓተቱ
አሳቦች በረቱ
'ላሳብ የሚታሰብ
የአሳብ ዥጉድጉዶሽ
አሳብ ያዝ ለቀቅ
የነገር አባርሮሽ
አሳብ 'ካሳብ ሲሸሽ
ሲፋተግ ሲተሻሽ
ወዴት ልሽሽ?
ይኼም ሌላ አሳብ...
እዚህ ሸብ
እዚያ ሸብ
አሳብ ማሰባሰብ
አሳብ 'ባሳብ መክበብ
አሳብ 'ባሳብ ማጥበብ
ማሳመር መቀንበብ
...ጥበብ!
ጉራማይሌ ንባብ
ባለ ቀለም ምናብ
ድምፅ አልባ ንትርክ
የሽቅድድም ታሪክ
በምናብ ብራና
ቀድሞ የሚተረክ
እንደ ሰማይ ስንጥቅ
ብሩህ ብርቅርቅታ
አድማስ የሚያዳርስ የቀለም ጠብታ
ብትንትን እያለ
አሳብ 'ካሳብ ላቀ
አሳብ 'ላሳብ ፍሞ
አሳብ ተቃጠለ
ባላስብ ምናለ?
ይኼም ሌላ አሳብ...
(የጌታነህ ልጅ)
#poeticsaturdaya #gitemsitem
የ2013 የመጨረሻ ግጥማዊ ቅዳሜ!
22 ከቅዱስ ገብርዔል ሆስፒታል ጀርባ በሚገኘው GUAC-ON ሬስቶራንት ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ቅዳሜን አስውበን እንጠብቃችኋለን!
Come join Poetic Saturdays at GUAC-ON in Hayahulet this coming Saturday, September 4th 2021!
https://www.facebook.com/guaconaddis
- As usual, we will start registration at 2: 00 pm.
- Only perform YOUR ORIGINAL work. The audience is there to listen to your truth!
- Each performer gets 5 minutes total. You can perform as many times but respect the time limit.
- All languages welcome.
All performance art forms welcome!
- We are excited our audiences and honored our performing family is growing. So come by and witness the amazing talents brewing in our city.
- Tell a friend!
የ2013 የመጨረሻ ግጥማዊ ቅዳሜ!
22 ከቅዱስ ገብርዔል ሆስፒታል ጀርባ በሚገኘው GUAC-ON ሬስቶራንት ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ቅዳሜን አስውበን እንጠብቃችኋለን!
Come join Poetic Saturdays at GUAC-ON in Hayahulet this coming Saturday, September 4th 2021!
https://www.facebook.com/guaconaddis
- As usual, we will start registration at 2: 00 pm.
- Only perform YOUR ORIGINAL work. The audience is there to listen to your truth!
- Each performer gets 5 minutes total. You can perform as many times but respect the time limit.
- All languages welcome.
All performance art forms welcome!
- We are excited our audiences and honored our performing family is growing. So come by and witness the amazing talents brewing in our city.
- Tell a friend!
የዓመቱ የግጥማዊ መቋጫ ደረሰች! እንግዲህ ተከሰቱና ክስተት የሆኑ ገጣሚያንን ግጥሞች እንዲሁም ሌሎች የጥበብ ስራዎችን ታደሙ!
I was just passing through.
Or time, through me.
I froze or time did.
And just Like that,
Of all the places in the whole world, I had nowhere to be.
I had nowhere to return to.
______
እነበርኩበት ላይ
አምናን
አሁንን
ነገን
ሁሉን መምሰል መስዬ
ያለመለወጤን ሀቅ
ለመለወጥ ምሥጢር ጥዬ
አቆያየቴን
አጠባበቄን
በእርምጃ ሳሰማምር
የሚገፋኝን፤
ቀኔን ልገፋ ስዳክር
ሁሉ ጥሎኝ ከንፎ
ሁሉን ጥዬው እየከነፍኩ
አንቺን ብቻ አትርፌ
ዓለሙን ሁሉ ከሠርኩ!
[የማይደግፈኝን ደግፌ
ወደምቀርበት የምመጣው
የማልበላውን
ተሸክሜ የምወጣው
መቆሜን አልፎ እየቻለ
መንገድ አላራምድ ያለኝ
በእህል ምትክ የሚጎረስ
ሠው፤ ህይወት እየራበኝ...
ይህቺን ታህል...
እያለፍኩበት የምኖረው
አሁን ስፈልግ ነው
ሌላ አሁን ያከተመው!]
Even when I say I haven't changed a bit,
I have changed a lot.
Cos I never used to say that!
Yes I contradict my self.
And that's what kept me in one piece!
ቆሜ
መዳከሜን ላባብለው
የተራመድኩትን ባስተውለዉ
እየሄድኩ አለመድረሴን ሊያስረዳ
የተራማጁ ሲገርመኝ
ጥላዬ እርምጃዬን አስከነዳ...
[በዐይንሽ የልቤ ይደርሳልና
መሰልቸቴን እገስጻለሁ...
አለመምጣት ፊቴ ቆሞ
በመጠበቄ እረካለሁ..
ለመተው ብናስተውለው...
የሚያልፍብን
የምናልፍበት
ጊዜ ይደናበራል
መንገዱ እየነጎደ እግራችን ቆሞ ይቀራል፤
ምንገዶን...
መቆሚያ ካለ
ተስፋ አጥግቦ ያሳድራል!]
እንግዲህ...
እውነቱ እያየነው
ውሸት የሚሆንበት ቀን አለው...
ልክ አለመለወጤን እያስረዳሁ
የከበበኝ በሙሉ አዲስ እየተካ ነጎደ
የምደርስበት ዘንድ ሳልሄድ
የምደርስበት ደርሶኝ ሄደ...
ጊዜ በጎኔ አለፈ
አዲስ ትናንት አስቀረሁ
ያልኖርሁት ዕለት ትዝ ይለኛል...
አልተለወጥኩም ብል ማን ያምነኛል?
[ሁሉ ረግቶ
ሩጫው ላይ
የምረጋበት ቢያሳጣኝ
መቆሜ ነው መጽናኛዬ
ወደጥርስሽ የሚያመጣኝ...
መድረሻዬን ሊመትር መሰለኝ
ጥላዬ ቀድሞኝ ሮጧል
ስንዝር ብጨምር አልቀድመው
ወዴት እራመዳለሁ?
ወደአመጣኝ ዘፍጥረቴ
ወደእቅፍሽ እመለሳለሁ!
በአንቺ ተስፋ ለመለምኩ እንጂ
ለምለም እንጀራ ቢጠቀለል
ለዳረጎት ቢጣል ከአፍ ላይ
ነፍሴ ተርባ አታውቅም
ቀምሳ ከማረፍ ከመንካት
አንቺን ከመጉረስ በላይ..]
እያለፍኩ
እንደአሁን
እጠብቅሻለሁ
I was just passing through.
Or time, through me.
I froze or time did.
And just Like that,
Of all the places in the whole world, I had nowhere to be.
I had nowhere to return to, but you!
_
Inspired by: The Photograph brought forward for #Gitem_sitem6 challange...
©️ MarkO's
Gitem Sitem 6
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
