ch
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

前往频道在 Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

显示更多
1 720
订阅者
-224 小时
-47
-930
帖子存档
Here is a cool poem shared by Mahder Addis on The Hub. Check out thehub.linkupaddis.com to read the full poem.
Here is a cool poem shared by Mahder Addis on The Hub. Check out thehub.linkupaddis.com to read the full poem.

ትንሽ ቀዳዳ ገላዬን ወዳ በቤቴ ሽንቁር ቀጫጫ ፀሐይ የብርሀን መስመር በፅልመት ሚታይ ብትወረውረው ንጋት ጠብቃ እየቆረጠ የቤቴን ማገር የቤቴን ጭቃ ከቤቴ ገባ የተኛው እኔ ከእንቅልፉ ነቃ፡፡ ውበት ነው ፀሀይ ሙቀት ነው ፀሀይ ንዳድ ነው ፀሀይ የሚያጣጥመው ስለሚለያይ፡፡ ©ብሩክ ኮርሳዊ

አሸንፈናል....ግን ይርበናል? (ሦስት ተከታታይ ክፍል ያለው ህመም) ክፍል-፩ : : ዘመን የየራሱ 'ማይግሬን' አለበት፡፡ ትውልድ የየራሱ ሽባነት አለው፡፡ የሁሉም 'አሁን' ምንጭ 'ትናንት' ነው፡፡ ትናንታችን ውስብስብ ነው ለማለት አሁንን ማየት በቂ ነው፡፡ በየጦርነቱ በየምሽጉ ድል የሚቀናን ህዝቦች ለመሆናችን ምስክር አያሻንም፡፡ አድዋን ለማክበር በየአመቱ ወደ ፒያሳ ከሚወጡት ወገን ነኝ (ወይም ነበርኩኝ):: ወደ እንጦጦ ወደንጉሱ ቤት እሄዳለሁ፡፡ በፀሀይ በረሀብ በድካም፡፡ (ልብ በሉልኝ የድል ቀን ነው) የገጠር ቤት እያየሁ፡፡ ውሃ መብራት በቅጡ የሌለበት የሀገሬን ጎጆ እየታዘብኩ፡፡ ደግነት ያለው ያገሬው ሰው ልቡ ልተለወጠም፡፡ ኑሮውም አልተለወጠም፡፡ የአድዋ ጦርነት ጊዜ በነበረበት ድህነት አለ፡፡ ጥያቄ፡- ያሸነፍናቸው ይጠግባሉ ያሸነፍናቸው በመኪና ነው የሚንደላቀቁት ያውም በነፍስ ወከፍ ገቢ፡፡ እኛስ? ለዛ ነው ትውልዱ መንገድ ላይ ከነኮተቱ እንደቀረ ቤት ተከራይ ላጤ የተደናበረው፡፡ ዕቃ አለው ከትናንት የተረፈው ታሪክ ውርስ ግን ለሱም ለተረፈውም የሚሆን መጠጊያ የለውም፡፡ የተረፈው ነገር ከምን አዳነው? ማሸነፋችን ከምን አዳነን? ከምን? ፡ ከማንነት ዝቅጠት? ከእርስ በእርስ ጦርነት? ከመናናቅ? ከሙስና? ከችግር ከችጋር? በራስ ከማፈር? ከምን? : : በሀቅ መሞገት ያለብን የራሳችን የውስጣችን ጠብ ላይ ነን፡፡ (Inetrnal conflict ) ይሉታል፡፡ ኩራት ራት ሆኖብን ካልሆነ በየመንገዱ የወደቀው ነፍስ ብዛት የአሮጊቶች እንባ ዓለምን በመዳፉ የሰራ ፈጣሪ ማደሪያው ታቦቱ ቀኑ ለመለመኛ መዳፍ ሲጠሩ የ13 አመት ጀምሮ ያሉ ሴቶች ሴተኛአዳሪ መሆናቸው በሞራልም በመንፈስም በአካልም ወድቀን ሳለን .....አሸንፈን የሚለው ቃል መፈክር ብቻ ይሆንበታል ለትውልዱ፡፡ ይመራል፡፡ ግን ሀቅ ነው፡፡ አሸንፈናል .....ግን ይርበናል:: ፡ ያሸነፍናቸው ....የት ናቸው? ፡

I saw a falling star today . It was Black No, No, it’s White Or, was it gray? 🤔 . I saw your face in the middle As it went down in a downhill I was tempted! Heavens know, I was tempted to save us both From the crash that could end all I was tempted . Hope you’ll survive! ©YeGetanehLij #YeGetanehLij

አድዋ የእሳት ልሣን የጀግናዎች የወኔ ቅስም የጨቋኞች የውርደት ስም የጭቆና አርካሽ መድኅን የባርነት ቁስል እንዲድን አድዋ የነፃነት አፍ! የሰውነት ልኬት አጥናፍ!!.. ©ሠይፈ ወርቅ #አድዋ_የእሳት_ልሣን

Rock (Mahder Addis) He is my rock that I lay my back onto, He is my sheild who gets struck by a raining arrow, While he is bl
Rock (Mahder Addis) He is my rock that I lay my back onto, He is my sheild who gets struck by a raining arrow, While he is bleeding I can sleep in sound despite his sorrow. I can smell his stench of sweat through his shirt, I can feel him shivering in the cold of midnight. Yet... I am warm, I am asleep, I am safe. He encapsulates me with his love, His strained eyes, his shaking arm fighting to let me stay in his embrace. An unconditonal love, wants nothing in return, His bones chime their own music that keeps me calm with sound of the rain. My rock, father... My armor, My ray of sunshine in dusk's call. I know this is nothing but words flying, But its what i could do with all my trying... To thank, My heavenly father who got me you of all this existance. To pray, And wish you all the years earth offers. However dreadful it may be, All is perfect with you, staying by my side. go to thehub.linkupaddis.com for more

This Face (Face this Face/Vase Face to Face) I usually don’t smile or laugh a lot I may seem shy and in fact, I am But you won’t believe that Because unlike plastic smiles I wear a plastic seriousness But deep down My heart cries For those poor souls by the road sides For those lucky riches with no souls For the couples without love For the pretty girls who feel nothing without make ups And for all the delusion around us all But behind this face, This face, that always looks frowned Nervous, sad, dejected, Disgusted or downhearted This face that faces terror, fear and anxiety Happiness, bliss and spontaneity All at the same time may be And with the same look may be Yes, behind this face There is a vase of flowers That makes me feel handsome Like I’m the painting by Huysum If you put another look on my face, Just know that you’re breaking that vase And make sure I approve of it And make sure you replace it with something better if there is any … Yes, I am sensitive but I usually don’t smile or laugh or cry a lot This straight face tells that I am straight Nothing less nothing more May be there is something wrong with my world Or my facial nerves But this face, Is not the face I was born with Because at this phase, This face starts wrinkling And I give face with this faith That I won’t be shaking or rumbling But to save face, I would shout out that this face Has nothing to do with you I don’t care whether you like it or not But if you do, kiss it If not, just ignore it Let it frown, let it go straight, just let it be For this face is a face that belongs to me I deal with it! . . . And yes, behind this face There is a vase of flowers That makes me feel handsome And on this vase, there is your reflection So deal with it! (and this face is no ፌዝ) #seifetemam

Jan van Huysum, Vase of flowers, Galleria Palatina
Jan van Huysum, Vase of flowers, Galleria Palatina

የ እሳት ራት እኔ የ ምወደው እሱ እሳት ይወዳል ከ አጥንቴ ማግዶ ከደሜ አርከፍክፎ ሰርክ ያቀጣጥላል ፍም እሳት ፍርሀት እኔ እሳት ያስፈራኛል አጥንቴ ሲማገድ ካለው ህመም በላይ ደሜ ሲርከፈከፍ ካለው ስቃይ በላይ እሳት ያስፈራኛል የፈጣሪን ምስጢር በግልጥ ያወራኛል ከምድር ከርስ ውስጥ የተቀበረውን ካልፈነዳሁ እያለ ሚገነፍለውን ጎመራ ይመስለኛል ሲኦል ይታየኛል የፈጣሪን ቁጣ ሰዶም ወይ ጎመራ የ ኤልያስን መስዋዕት ጥልቅ ዘልቆ ሲበላ ከገነት ደጅ ላይ እየተገላበጠ ሰውን ከፈጣሪ ስላቆራረጠ እሳት ያስፈራኛል እሳት ነውር አያውቅም ይሉኝታ አይዘውም ይፋጃል ያነዳል ከነደደው እሳት ትንሽ ኩስታሪ ከንፈሬ ላይ አረፈች ወጣሁ ከፈጣሪ ራቅኩ ከ አማልክቱ ታላላቅ ሚስጥራት ስለተከፈቱ የቃዬን መስዋዕት የበአል ነቢያት ያነደዱት እሳት ሞትን የተሳፈረ ሰረገላ ይመስላል በሀሩር ሲያነዱት የብርድ መድሀኒቱ ወበቅን ይወልዳል ከደም ወዝ ቀላቅሎ መሲህ ያስጨንቃል ማይታለፍ ፅዋ ለ አምላክ ይቀዳል የፅድቅ ጥያቄን ፍርድን ይመሰላል እኔ የምወደው እሱ እሳት ይወዳል ከ አጥንቴ ማግዶ ከደሜ አርከፍክፎ ሰርክ ያቀጣጥላል ጠራኝ.... ፍቅር እና እሳትን እያመዛዘንኩኝ አንድ ሁለት እርምጃ ወደ እሳት ቀረብኩኝ ጉዴ የጨለመን ምስጢር የሰውነቴን ውስጠት ያልተረጎምኩትን የመላዕክት ልሳን ገሀድ የገለጠ የእሳት ብርሀን ገላዬ ላይ አረፈ ነፍሴ ተገረፈ ሌላ ሚስጥር ወጣ በ እርሱ የፍርድ ወንበር ከ እሳት ፍርሀት በላይ ለ እሱ ያለኝ ፍቅር ©Feben Fancho

እኔ ...? ስንዝር ታህል ከፍ ብዬ ከምድር መኖር ከቻልኩ ... የውነት-የውነት የምር ይህን ነኝ ..ያንንም ክፉውን ..ደጉንም -------- ከጀምበር ጀምበር ስዝዘል ከደም-ስር ስር የምውል ቕርብ ያልለሁ ደሞ ሩቅም መኻን የሆንኩ የወልለድኩም -------- (ከሞት) የመርረርኩ ርግማን (ከህይወት) የጣፈጥኩት ምርቃት ማርያም ድንግሊቷ ደሞ ...ዘምማዊቷ ------ ከዘላለም ቀድሜ የነብበርኩ ጨቅላ ቦቀቅላ አሁን የተወለድኩ ከሳቅም ሳቅ ከጥርስ ያልወድደቅኩ ከእንባም እንባ ግት ሆኜ ያልታበስኩ ቆሜ ልሸና ግንብ (በብልቴ) የተደግገፍኩ ያላጠባ ጡቴን በጨርቅ የሰበስብኩ ------- ቅስናዬ ከመስጂድ ሸኽናዬ ከቤተ ክርስቶስ ያፈጀሁ ያረጅጀሁ ... ዕለት ዕለት ስታድደስ ------- በሲዖል ለም አፈር የተበጀሁ በጀነት እሳት የተፈጅጀሁ ከድቅድቅ ጨለማ የምቀብጥ የብርሃናት ልዑክ እሳት የማምጥ ------- አምላክነት ... ልኬ አይሆንም ሰውነትም ... ከኔ አይገጥምም ጽድቅ እና ኩነኔ ተጠይያቂ ጥያቄ ማን ነኝ፣ ምን ነኝ'ኔ ... ? ©ዳዊት ካሳ

እነሆ : : : " ሰው ፍቅር ናፍቆት" #በገበያ_ላይ_ዋለ!! Join and share…………………👇👇 @heranawi @heranawi @heranawi
እነሆ : : : " ሰው ፍቅር ናፍቆት" #በገበያ_ላይ_ዋለ!! Join and share…………………👇👇 @heranawi @heranawi @heranawi

Gitmawi Kidame (Poetic Saturday) will take place at Fendika Cultural Center and online on Saturday 06 February 2021 from 2:00
Gitmawi Kidame (Poetic Saturday) will take place at Fendika Cultural Center and online on Saturday 06 February 2021 from 2:00pm to 5:00pm. @linkupaddis

ሳራ ወልዱ - እረፍትን መርሳቱ

ሠላም ሠላም ግጥማዊ ቅዳሜያውያን ወርሃዊውን የጥበብ ድግሳችንን ይዘን ብቅ ብለናል! ከረጅም ጊዜ መነፋፈቅ በኋላ ቅዳሜ ጥር 29 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በፈንድቃ የባህል ማዕከል
ሠላም ሠላም ግጥማዊ ቅዳሜያውያን ወርሃዊውን የጥበብ ድግሳችንን ይዘን ብቅ ብለናል! ከረጅም ጊዜ መነፋፈቅ በኋላ ቅዳሜ ጥር 29 ቀን 2013 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በፈንድቃ የባህል ማዕከል በአካል ተገናኝተን ናፍቆታችንን እንወጣ ዘንድ ደግሰናል፡፡ በአካል መገኘት አይችሉም? እንግዲያውስ በዙም ይቀላቀሉና! ሊንኩም ይኸው! https://us02web.zoom.us/j/71147805916 እንደተለመደው ከ8 ሰዓት ጀምሮ ምዝገባችንን እንጀምራለን፡፡ አዳዲስ እና የራስዎን ፈጠራ ብቻ እንዲያቀርቡ ይመከራል ለእያንዳንዱ አቅራቢ 5 ደቂቃ ብቻ ቢፈቀድም የፈለገውን ያህል ማቅረብ ይችላል። ምንም አይነት የቋንቋ እና የይዘት ገደብ የለውም ምንም አይነት የጥበብ ስራ ይበረታታል ይምጡና የጥበብ ቤተሰባችንን ይቀላቀሉ!

እጭ እናቴን ለ9 ወር ያስታቀፍካት ዘር ገረመኝ እኔን ሆኖ ሲገኝ ዘመን ጥላ እየጣለ የእድሜ ተዳፋቱ እንደት ይነጉዳል ቀን እንደት ያረግዳል? ያው ለተራ እንቁላል ጣይነት ደደርኩ ማስካካት ጀመርኩ (ዘሩ በዙር ይቀጥላል ) ትላንቴ እኔን አህሎ ስትጨፈልቀው የማህፀኔ በር የደም እንባ ተናነቀው ጭን'ቅ እያስቀመጠኝ ሲቃ እያስማጠኝ እያስቧጠጠኝ አመለጠኝ .... በትግላችን መሀል የያዝኩት እንቁ'ላል ደርሶ ተሰበረ እንጭጭ እኔነቴ እጭ ህይወት ነበረ ©ባንችአየሁ አሰፋ #ባንችአየሁ_አሰፋ

Somedays I’m done with poetry Some days Poetry is done with me Some days it calls my name And My name stays quiet as if it doesn’t belong to me ©Everted