ch
Feedback
Diinii kee Anaakara (Md Ali)

Diinii kee Anaakara (Md Ali)

前往频道在 Telegram

دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol

显示更多
1 617
订阅者
-124 小时
+67
+2030
帖子存档
خطبة الجمعة ١٢ صفر ١٤٤٤هجري في جامع الإحسان بمدينة لوغيا لفضيلة الشيخ دكتور محمد حسين ويعسى Jumqattâ khutba 🌄 D. Mucammad Cuseyn Mucammad Weeqisa 🌏#تابعونا على #تيليجرام🌏 🌍 Telegramal Me Kataata🌍 Sinni Katasiisih Ruuba #AfarMahaNetwork 🌐🌐🌐🌐🌐https://t.me/AfarMahaNetwork #شبكةالفجرالعفر 🎙👂👂👆Ama linki Xaga 🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸

018.mp310.67 MB

☔️Sehdal faxeenim waanaah, geyaanah! 💎Yallal faxeenim mawaanay geyaanah!! Md Ali ✍ https://t.me/httpsDiiniKeeAnaakara

✅ የአደም ልጅ ገንዘቤ ገንዘቤ ይላል ✅ 🔺عن عبدالله بن الشخير رضي الله عنه قال: أَتَيْتُ النبيَّ صَلَّى اللَّهُ عليه وسلَّمَ وَهو يَقْرَأُ: أَلْهَاكُمُ التَّكَاثُرُ، قالَ: يقولُ ابنُ آدَمَ: مَالِي، مَالِي، قالَ: وَهلْ لَكَ، يا ابْنَ آدَمَ مِن مَالِكَ إلَّا ما أَكَلْتَ فأفْنَيْتَ، أَوْ لَبِسْتَ فأبْلَيْتَ، أَوْ تَصَدَّقْتَ فأمْضَيْتَ ✅ አብደሏህ ቢን ሺሒር እንዳስተላለፈው የአላህ መልእክተኛ ﷺ (ሱረት አተካሱር) እየቀሩ ባሉበት ሰአት ወደሳቸው መጣሁ። በመቀጠልም እንዲህም አሉ ♻️የአደም ልጅ ገንዘቤ ገንዘቤ ይላል። የአደም ልጅ ሆይ ከገንዘብህ 🔺በልተህ የጨረስከውን 🔺ለብሰህ ያጠናቀቅክውንና 🔺በሶደቃ መልኩ ወደ አሔራ ከላከው ውጪ ምን ገንዘብ አለህ❕ 📚 صحيح مسلم: (2958) ✅አንተ የአላህ ባርያ ሆይ አስተውል‼️ 🔺በልተህ ከጨረስከው ውጪ የገዛኸውና እቤትህ ያለው የሸመትከው አስቤዛ እንኳን ያንተ አይደለም ሳትበላው ጥለኸው ልትሄድ ትችላለህና 🔺ሌላው ይቅርና የለበስከው ልብስ ራሱ ያንተ አይደለም እንደለበስከው ሞተህ ሬሳ አጣቢዎች አውልቀው ለቤተሰቦችህ ሊያስረክቡት ይችላልና 🔺ባንክ ያጨናነቀው ሀብትህ ይቅርና በኪስህ ውስጥ ያለው ፍራንክ ራሱ ያንተ አይደለም። ልክ እንደሞትክ ከሁሉ ኪስህ በርብረው አውጥተው ወራሾችህ ይቀራመቱታል። 👉ሚገርመው ግን ለዚህ ዱንያ ብለህ ያሁሉ ለፍተህ፣ ለዚሁ ብለህ ከስንቱ ተጣልተህ፣ ስንት መከራ አይተህና ታግለህ ከሰበሰብከው ሀብት ይዘኸው ምቴድ አንድም ነገር የለም። ሌላው ይቅርና ለዛውም ኪሴ ራሱ የሌለው ሁለት ሜትር ጨርቅ ብቻ ነው ካንተ ሚቀበረው። ሌላው ሁሉ የወራሽ ነው። ♻️የማትኖርበት ያክል ከምትገነባ። የማትበላውን ያክል ከምትሰበስብ ከሀብት የሚበቃህን በልኩና በአግባቡ ይዘህ ሌላው ወደ አሔራ ቤትህ ላከው። #ትርፋማውና_የማትከስርበት_ትክክለኛው_ሀብትህ_ማለት ይህ ነው። ® ፉርቃ የቁርዓን ሕፍዝ ማዕክል በእድሳት ሂደት ላይ የበኩላችንን አስተዋፅኦ በማድረግ በዚህ መልካም ስራ ላይ አሻራችንን እናሳርፍ‼️ 👇👇👇👇👇👇👇👇 #_مركز_الفرقان #MerkezIfurqan

እስከ መቼ? ~ ነጋ ጠባ ስለ ብሄርህ የምታወራ፣ ጧት ማታ "ኦሮሞ፣ ኦሮሞ"፣ "አማራ፣ አማራ"፣ "ትግሬ፣ ትግሬ"፣ "አፋር፣ አፋር"፣ "ስልጤ፣ ስልጤ"፣ "ጉራጌ፣ ጉራጌ"፣ ... የምትዘምር፣ የምታለቅስ፣ ... ከሆነ መመዘኛህ ሁሉ ዘር ነው የሚሆነው። ዘር ተከትለህ ትወዳለህ። ዘር ለይተህ ትጠላለህ። እወቅ! ያንተ ብሄር ከሌላው የሚለየው ቅንጣት ታክል ደረጃ የለውም። ደግሞም በለቅሶውም፣ በሰርጉም፣ በሀዘኑም፣ በፌሽታውም፣ በቤትም፣ በመስጂድም፣ በቡናውም፣ በጫቱም ላይ ሁሌ ስለብሄር ስታኝክ ልታፍር ይገባሃል። በብሄር አጀንዳ በተጠመድን ቁጥር በሌሎች ላይ ጥላቻ እየጨመርን ነው የምንሄደው። አንድ ሰው ዘረኝነት ልቡን ከተቆጣጠረው ሰውነቱን ያጣል። በመንጋ እንደሚጓዝ አውሬ ያለ ምክንያት ያልመሰለውን ሁሉ ይናከሳል። "ቆይ እኛ ቤት ትመጣለህ!" እንደሚል ህፃን ከደጃፉ ያገኘውን ሁሉ ያጠቃል። ደግሞም ሁሌ ሌላውን ብሄር እያብጠለጠልን ከሌላው አክብሮትን ልንጠብቅ አይገባም። Respect is a two-way street! ወንድሜ ሆይ! ሰው ሁን። ጭንቅላትህን ካልተጠቀምክበት ላንገትህ ሸክም ሆኖ ቢንገታገት ምን ይሰራል?! ሰው ሰርቶ ሲለወጥ "ከኛ የሰበሰበው ገንዘብ ነው" አይነት ቅናት የወለደው ብሶት አታንቋር። ከቻልክ እንደሰው ሰርተህ ተለወጥ። ካልሆነልህን እራስህን በቅናት አታቃጥል። "ምቀኛ ከራሱ ማግኘት ይልቅ የሌላው ማጣት ነው የሚያሳስበው" ይባላል። ዘረኝነት ተደጋግፈን እንዳንኖር የተጋረጠ እጅግ አደገኛ በሽታ ነው። በዚህ ዘመን በየቦታው ለሚደርሰው ግጭትና እልቂት ቀዳሚው ምክንያት ዘረኝነት ነው። ሌላው ቀርቶ በየመስጂዱ ሳይቀር እየገባ ሰዎችን ልብ ለልብ እያራራቀ ነው። ችግሩ በዚህ መጠን እንዲያውም ከተገለፀውም በከፋ ደረጃ ቢሆንም የዲን አስተማሪዎች ግን አብዛኞቹ ደራርበው ተኝተዋል። ከፈሎቹማ ጭራሽ የችግሩ አካል ናቸው። ጥቂቶች ደፍረው የሚናገሩ ከኖሩም አንዳንዶቻችን "እኛን ለመንካት ነው" ብለን ደርሰን የምናኮርፍ፣ ልባችን በጥላቻ የሚጓሽ ሆነናል። ይሄ በጣም የሚያሳፍር ነው። ብቻ ህልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም። ጥንብ በሆነው ዘረኝነት የተነሳ ከማንወጣበት አዘቅት ውስጥ እየገባን ዝም ብሎ ማየት አያዋጣንም። ስለዚህ በቃ ልንል ይገባል። እስካሁን የደረሰብን ጉዳት ለመማር ከበቂ በላይ ነው። ነገ የነ ርዋንዳ አይነት እልቂት እንዳይገጥመን ጥርሳችንን ነክሰን ችግሩን ልንጋፈጠው ይገባል። ባግባቡ መወቃቀስ ባለመቻላችን ይሄው በድንቁርናው የሚኮፈስ፣ ድንዛዜውን "በክብር" ሰቅሎ የሚያሳይ ገራሚ ትውልድ መጥቶልናል። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

#Inki_wak_kekka_tu_nee_haytan Inkih gaba edde nassagallem faxximtaah, inkih tan Qafaray irooy addal tani quuriik edde ugutak
+1
#Inki_wak_kekka_tu_nee_haytan Inkih gaba edde nassagallem faxximtaah, inkih tan Qafaray irooy addal tani quuriik edde ugutak arac xagissam faxximta dagoo khayri taama fooca siinik makna. Tohuk Qafar Qulama madduuruk inkih rammo le caddot anuk isinni ummatta tayfoofeeh, milagta qulama kinnim tamixxige. Too Qulamak firqaweh tanim massakaxxa le Ni Qaalim #Shekh_Mucammad_Awwal_Cayaata. Qafar Qunxaaneytay, niya Meqe koobaahisak Ni Sheekhih Merraytu (Makiina) limmoosaanamih cogayso qimmiseenih geytiman. Tahat xiqqa haynam burute kalah gaba nessegellek kontom loomintih missilah bilqa nel akkale. Inkih tan Qafaray, muslimiinih tanik annah tan Qunxa caagiida orbisnu naffarem boola nek diqsitele. Tohih sabbatah ta caagid sissikuk orbisnay🥰🥰 Fakkiime Banki cisab 1000496370167 shek Qali baxa kee shek awwal Darsa migaaqal yanil ta saaqatak abbaxuk xiqtaanam culusa Khayri taamal Digganay🙌

٢صفر١٤٤٤ محاضرة: بعنوان الاستغفار أمان من العذاب Dambi Cabsot Yallal Esseraaanam Digaalak Nagoowu لفضيلة الشيخ دكتور محمد حسين ويعسى 🌄 D. Mucammad Cuseyn Mucammad Weeqisa 🌏#تابعونا على #تيليجرام🌏 🌍 Telegramal Me Kataata🌍 Sinni Katasiisih Ruuba #AfarMahaNetwork 🌐🌐🌐🌐🌐https://t.me/AfarMahaNetwork #شبكةالفجرالعفر 🎙👂👂👆Ama linki Xaga 🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸

ጥቂት ነጥቦች ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ ~ 1. ወገኔ ሆይ! አገርህን አትልቀቅ። ባለፈው ተፈናቃዮች ላይ የደረሰውን አስታውስ። ደብረ ብርሃንና ባህርዳር ለተፈናቃዮች ከማጎሪያ ካምፕ የማይለዩ እንደነበሩ ሲወራ ነበር። አሁን ደግሞ ነገሮች ከቀድሞው ቢብሱ እንጂ የተሻሉ አይደሉም። ፖለቲከኛውን ተወው። ህዝብ እራሱ ኑሮ ስለከበደው ሊጨካከን፣ ሊሰላች ይችላል። ሩቅ አትሂድ። ደሴ ወልዲያን፣ ወልዲያ ቆቦን ሊሰለች ይችላል። የጎደለበት ደግሞ በትንሽ በትልቁ ይከፋዋል። ስለዚህ በተለየ እፈለጋለሁ ብሎ የሚሰጋ ካልሆነ በስተቀር ጦርነቱ ቀጥታ ከሚካሄድባቸው ቀጠናዎች ለጊዜው ዞር ከማለት ውጭ ካገር ርቆ መሄድ ስቃዩን የከፋ ያደርገዋል። 2. ወገኔ ሆይ! ንብረትህን ጠብቅ። ሩቅ ብቻ አትመልከት። እዚያው በዙሪያህ ለዘረፋ ተደራጅተው ከግለሰብ ንብረት እስከ ተቋም ሲዘርፉ የነበሩ እንደነበሩ ይታወቃል። ዛሬም ይኖራሉ። ፍሪጅና ቴሌቪዥን ሳይቀር በግመል እየጫኑ የወሰዱ የገጠር ሰዎች እንዳሉ ሰምቻለሁ። “መብራት የላችሁ ምን ያደርግላችኋል?” ሲባሉ “እንሸጠዋለን” ሲሉ ነበር። ስለዚህ ቅድሚያ ለህይወት ጥንቃቄ ካደረግክ በኋላ በቅርብህ ሆነህ በተቻለህ መጠን ንብረትህን ተደራጅተህ ጠብቅ። 3. ወገኔ ሆይ! ለፈተና እራስህን አዘጋጅ! ወደድንም ጠላንም ፈተና ላይ ነው ያለነው። መጠኑ ከህዝብ ህዝብ በእጅጉ እንደሚለያይ ግልፅ ነው። ፈተናው ምን ያህል እንደሚዘልቅም አናውቅም። የሆነች ያክል የምንዘጋጅባት ሰበብ ካለችን ባለችን መጠን ለሚመጣው ሁሉ ራሳችንን እናዘጋጅ። ምግቡ፣ ወፍጮው፣ ባንኩ፣ መብራቱ፣ ቴሌው፣ መድሃኒቱ፣ ... ብዙ ነገር ይቸግራል። እስካሁንም ብዙ የተፈተነ አለ። ልዩነቱ ብዙ ባይሆን እንኳ የተዘጋጁበትና የተዘናጉበት ፈተና አንድ አይደለም። አላህ ለሁሉም ፈረጃውን ያቅርብልን። 4. ወገኔ ሆይ! ጊዜ አይተህ አትለወጥ! ለሚያልፍ ቀን ትዝብት ላይ አትውደቅ። የትኛውም ቡድን አጠቃኝ በሚል ማመሃኛ ማንንም ብሄር ለይተህ እንዳታጠቃ። የአማራ ህዝብ ሆይ! ህወሓትን መነሻ አድርገህ ለፍቶ አዳሪ ትግሬን አታጥቃ። “ያው ናቸው” ከሚል ስሜት ወለድ ሂሳብ ራቅ። “ህወኃት እከሌን አካባቢ የተቆጣጠረው ተፈናቃይ ትግሬዎችን ተጠቅሞ ነው” እየተባለ የሚናፈሰው ብታምንም ባታምንም ከንቱ ውሸት ነው። እንዲህ አይነት አሉባልታ ይዘህ ደካሞችን እንዳትጎዳ። ትግሬው ሆይ! ህወኃት ሲገባ ጠብቀህ አደባባይ ለጭፈራ አትውጣ። ጠቋሚ፣ አፋኝ፣ አሳፋኝ ለመሆን አትሞክር። ሃይማኖት ወይም ሞራል እንኳ ባይገታህ ቢያንስ ለራስህ ፍራ! ነገሮች የተቀያየሩ እለት መግቢያ ታጣለህ። በባለፈው ግጭት አማራውም፣ ትግሬውም፣ ኦሮሞውም፣ አፋሩም ዘንድ ብዙ ደስ የማይሉ ነገሮች ሲወሩ ነበርና አላህን ልንፈራ ይገባል። 5. ወገኔ ሆይ! ለመጣ ለሄደው አታጨብጭብ። አንድ ኃይል አንድን አካባቢ ሲቆጣጠር ሆ ብሎ መውጣት፤ ሌላው በግሩ ሲተካ አሁንም ሆ ብሎ መነሳት ይሄ ግልብነት ነው። የሃገራችን ፖለቲካ ቂመኛና ተበቃይ ነው። እንኳን የገባበትን፣ የሌለበትንም ጊዜ ተጠግቶ ያጠቃል። ደግሞም በጣም ተገለባባጭ ነው። እዚች አገር ውስጥ ስንት አይሆንም የተባለ ነገር ሆኗል! መንግስት ትግራይን ሲቆጣጠር ህወኃት ዳግም ያንሰራራል ብሎ የገመተ አልነበረም። ህወኃት ሰሜን ሸዋ ከደረሰ በኋላ በዚያ አሰቃቂ ሁኔታ ይመለሳል ብሎ የገመተም አልነበረም። ስለሆነም ጥንቁቅ መሆን ያስፈልጋል። በሁለቱም አይንህ ዛሬ ላይ ብቻ አታፍጥጥ። በአንድ አይንህ ነገን ተመልከት። 6. ወገኔ ሆይ! ህይወት አትርፍ። አጋጣሚዎችን ተጠቅመው የሚጠሉትን ለማጥቃት የማያመነቱ እርኩስ ፍጡሮች ይኖራሉና ቢቻልህ ያለ ጥፋታቸው የበደለኞች ሰለባ ሊሆኑ የሚችሉ ወገኖችን አትርፍ። ከጎናቸው ቁም። በባለፈው ግጭት ህወኃት ሲገባ ጠብቀው ደካሞችን ያጠቁ ሰዎች አሉ። ከነሱ አንፃር ሲታይ ህወኃት በጣም የተሻለ ነበር። መረጃ ያለው ሰው የምለው ይገባዋል። ህወኃት ከወጣ በኋላም እንዲሁ ከየትኛውም ኃይል ጋር ምንም አይነት ንክኪ የሌላቸው ምስኪኖች ተጎድተዋል። ከተቻለን ጊዜ አይተው ከሚያጠቁ ነውረኞች አንድ ነፍስ እንኳ ብናተርፍ ዋጋው የትና የት ነው!! በቅርቡ ኦሮሚያ ውስጥ በነበረውን ግጭት የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለው አማራዎችን ያተረፉ ስንት ኦሮሞዎች አሉ። ግን አላወራንላቸውም። አማራ ውስጥ የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለው ትግሬዎችን ያተረፉ ስንት አማራዎች አሉ። ግን አላወራንላቸውም። የራሳቸውን ህይወት አደጋ ላይ ጥለው አማራዎችን ያተረፉ ስንት ትግሬዎች አሉ። ግን አላወራንላቸውም። ሰው ማለት፣ ሰው የሚሆን ነው ሰው የጠፋለት! 7. ወገኔ ሆይ! ወቅታዊ ግጭቶችንና ተያያዥ ጉዳዮችን ከሃይማኖት ጋር እንዳታጠላልፍ። የየትኛውም ቡድን ደጋፊ ልትሆን ትችላለህ። የኔ የምትለው ወገን ከሌሎች በተለየ እንደተገፋ ሊሰማህ ይችላል። ግን እወቅ! ሌሎችም መሰል ህመም አላቸው። ቢቻል በፖለቲካውም ሞራል ግብረ ገብነት ቢኖርህ እሰየው። ያለበለዚያ ግን የሃይማኖት ተቋማትም፣ አስተማሪዎች እና የደዕዋ መድረኮችም አንተ በምትፈልገው መልክና መጠን እንዲያወሩ፣ የፖለቲካ ፍጭቶች ማራገፊያ እንዲሆኑ አትፈልግ። ማህበራዊ ሚዲያዎችም ላይ ሆነ መሬት ላይ እየተከተልክ በአክቲቪስት ቋንቋ እንዲያወሩ አጉል አትወትውት። ልትረዳ ቢያቅትህ ቢያንስ አደብ ይኑርህ። ከፖለቲከኛ ጋር የለመድከውን እሰጥ አገባ በየደረስክበት አትድፋ። 8. የሃይማኖት አስተማሪ ሆይ! ከመንጋው ተለይ! ብሄርህን ተከትለህ ቅስቀሳ ውስጥ አትግባ። ሌላው አካል ለጦር ቢቀሰቅስ አንድ ሁለት ነገር ተመልክቶ ነው። አንተ ተጨማሪ አርቀህ የምትመለከትበት አላህን መፍራቱ ሊኖርህ ይገባል። ያለበለዚያ በምንህ ነው ከሌሎች የምትለየው? ኢን ሻአላህ ነገ ሰላም ይመጣል። እሱን ታሳቢ አድርግ። መንጋው ሊያግባባህ፣ ሊገፋፋህ፣ አልሆን ሲለው ሊያወግዝህ ይችላል። የፈለገውን ይበል እሱ በቀደደው አትፍሰስ። የሃይማኖት አስተማሪ ሆነው በቀጥታ የግጭት ተሳታፊ፣ ወይም ቀስቃሽ፣ ወይም ደጋፊ፣ ወይም የዘር ጥላቻ ጠማቂ የሆኑ መርዘኛ ሰባኪዎች ሁሉም ብሄር ጋር አሉ። እነዚህ አካላት ነገ ችግሩ ቢያልፍ እንኳ የማያልፍ ጠባሳ እየጣሉ ነው። ጦሳቸውም ከራሳቸው አልፎ ለህዝብ ይተርፋል። ከሃይማኖትህ ተማር። እስካሁን ካለፈው ተማር። ከሌሎች ድክመት ተማር። የትኛውንም ውሳኔ ብትመርጥ ከትችት ላታመልጥ ነገር የሰው ስሜት ተከትለህ እንዳትወስን። አላህን አስብ። በመጨረሻም አደራ የምለው እንተዛዘን፣ እንተሳሰብ፣ ዱዓእ እናድርግ፣ ወደ ጌታችን እንመለስ። አላህ ከገባንበት መከራ አውጥቶ የሰላም አየር የምንተነፍስ ያድርገን። ኣሚን። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor

በኋላ “ቢመለሱ (ተውበት ቢያደርጉ) ለነሱ መልካም ነው” በማለት የተውበት በር እንዳልተዘጋባቸው ያስረዳል። 7. በታሪኩ ውስጥ ሠዕለባ እንደሙስሊምም እንደ ከሃዲም አልተያዘም። ወይ እንደሙስሊም ተቆጥሮ ዘካው አልተወሰደም። ወይ እንደ ከሃዲ ተቆጥሮ እርምጃ አልተወሰደበትም። ይሄ በኢስላም ያልተለመደ አሰራር ነው። 8. ዘገባዎቹ የተምታቱ ናቸው። ለምሳሌ እዚህ በኒፋቅ የተወነጀለበት ታሪክ ላይ በዑሥማን ጊዜ እንደሞተ ተጠቅሷል። ነገር ግን ይህን ታሪክ ሰነዱ ውድቅ ነው በማለት የዘርፉ ምሁራን ሙሐዲሦች ከመሰረቱ ጥለውታል። በሌሎች ዘገባዎች ደግሞ “የኡሑድ ጦርነት ላይ ሸሂድ ሆኗል” የሚል አለ። ኢብኑ ዐብዲልበርና ኢብኑ ሐጀር ባወሱት ደግሞ የኸይበር ዘመቻ ላይ ሸሂድ ሆኗል የሚል አለ። ተመልከቱ! የኡሑድም የኸይበርም ዘመቻዎች የተደረጉት ነብዩ ﷺ በህይወት እያሉ ነው። እውነት ሠዕለባ የሞተው ከነዚህ ጦርነቶች ባንዱ ከሆነ ሠዕለባ ከነብዩ ﷺ ቀድሞ ሞቷል ማለት ነው። የሞተበትን ትክክለኛ ዘመን አላህ ይወቅ። ብቻ ጉዳዩን ይህንን ከግምት አስገብተን ቆም ብለን ካየነው ሳያጣሩ በደካማ ታሪክ ተመርኩዘው ሠዕለባን ለሚወነጅሉ ሰዎች ይበልጥ አስደንጋጭ ይበልጥ አስፈሪ ነው። 9. ዘካ መቼ ነው የተደነገገው? ታሪኩ ላይ ሠዕለባ አለቅጥ በዝተው የሚርመሰመሱ በጎቹን ተከትሎ ከመዲና ከወጣ በኋላ ዘካን የምትደነግገዋ አያ እንደወረደች ያትታል። ያስተውሉ ለመውረዳቸው ሠዕለባ ሰበብ የተደረገባቸው ስለሙናፊቆች የሚያትቱት አንቀፆች አገባባቸው የሚያሳየው በተቡክ ዘመቻ ወቅት እንደወረዱ ነው። የተቡክ ዘመቻ ደግሞ ዘካ ከተደነገገበት ጊዜ ብዙ ዘግይቶ ከሂጅራ በኋላ በ9ኛ ዓመት ነው የተካሄደው። እንዲህ አይነት ህፀፆችን በመመልከት ነው አንዳንዶች ታሪኩን ከመሰረቱ ታላቁ የነብዩ ﷺ ሰሐባ ሠዕለባ ላይ የተፈፀመ አይን ያወጣ ቅጥፈት ነው ያሉት። በዚህ አጋጣሚ ሸይኽ ኢብኑ ዑሰይሚን ስለዚህ ቂሳ አንስተው እንዲህ ይላሉ፡- “በርካታ ሙፈሲሮች የሚጠቅሱትና ብዙ ደስኳሪዎች እንደሚያራግቡት ይቺ አንቀፅ በሠዕለባ ላይ ነው የወረደችው የሚለው ደካማ ነው፣ መሰረት የለውም። እንዲያውም ተመላሽ ከየትኛውም ወንጀል ቢመለስ አላህ ተውበቱን እንደሚቀበለው ከሚታወቀው ግልፅ እምነታዊ መርህ ጋርም የሚፃረር ነው።” [ኡሱሉ ተፍሲር] = (ኢብኑ ሙነወር፣ ነሐሴ 19/2006) የቴሌግራም ቻናል :- https://t.me/IbnuMunewor

🎙የሰላም ዋጋ 🔖 1/6 ወቅታዊ ነጥቦች 🍂t.me/zizuQ

ያልጠበቅነው ነገር ለሂዳያ ሰበብ ሊሆን ይችላል ~ 3 months ago... ወደሆነ ቦታ እየሄድኩ ታክሲ ውስጥ ኢርፎን ሰክቼ ቁርኣን እያዳመጥኩ ነበር... እና ኢርፎኑ በደንብ ስላልተሰካ ወደ ውጪም ያሰማ ነበር... ለካ አጠገቤ የነበረችው ካችፊር ልጅ አብራኝ ትኮመኩም ይዛለች... ቆየት አለችና "ምንድነው ምትሰሚው? በጣም ደስ ይላል" አለቺኝ። እኔም ቁርኣን መሆኑን ነገርኳት... ተዛም "ላኪልኝ" አለችኝ። ግን መውረጃዬ ደርሶ ስለነበርና ቸኩዬም ስለነበር ስልኬን ሰጠኋትና ቴሌግራም ላይ አውሪኝ ብያት ተለያየን... ተዚያም ቴሌግራም ላይ አወራቺኝ... እኔም ቲላዋውን ላኩላት.. የያሲር ዱሰሪይ ቲላዋ ነበር💜...እንደዛ እያልን አልፎ አልፎ ደና ነሽ እንዴት ነሽ መባባል ጀመርን... በጣም ተግባባንም...... ከዛ ቅድም በሌላ ስልክ ደውላ "አሰላሙ ዓለይኪ" አለች... ድምጿን የማውቀው ቢሆንም ግን አሰላሙ ዓለይኪ ስትለኝ እሷ መሆኗን ተጠራጠርኩ.. እና እሷም "ያወቅሺኝ አልመሰለኝም ሀኒኣ እባላለው.. ማለቴ ሃና" አለች.. ለካስ ልጅት ሰልማልኛለች...ከዛ ከገባሁበት ድልቅ የደስታ ስሜት ስወጣ እንዴት ልትሰልሚ ቻልሽ ብዬ ጠየቅኳት። እሷም «ያኔ የላክሽልኝን ቁርኣን ሳደምጠው መሰጠኝና ሌላም አይነት ካለ ለመስማት ፈልጌ ዩቲዩብ ላይ ሰርች አድርጌ ስራዬ ብዬ እያዳመጥኩ መመሰጥ ጀመርኩ... ከዛ ቡሃላ የማዳምጠው ቁርኣን እየተቆጣጠረኝ እንደሆነ ሳውቅ ለምን ስለ ኢስላም አላጠናም ብዬ ተነሳሁ... በርግጥ ከዚ በፊት የተወሰነ Hint ነበረኝ... ከዛ ግን ጠልቄ ሳውቀው ትክክለኛው ሃይማኖት እሱ ነው ብዬ አምኜልሽ አሁን ከሆነች ሙስሊም ጓደኛዬ ቤት ሸሃዳ አሲዛኝ እየወጣሁ ነው» አለቺኝ... ያ ሰላላላም ድብልቅልቅ ያለ ስሜት💜💜 ምን እንደምላት ቃላትም አጠረኝኮ ጎበዝ.. ብቻ አላህዬ ፅናቱን ይስጣትማ🤲 ተፃፈ በ Fatimah Muhammed