ch
Feedback
Diinii kee Anaakara (Md Ali)

Diinii kee Anaakara (Md Ali)

前往频道在 Telegram

دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol

显示更多
1 610
订阅者
+224 小时
+87
+1430
帖子存档
የዝናና ታዋቂነት ጥማት አዲሱ ጣኦት 💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢 ዛሬም ሆነ ነገ፥ በዚህ ምድርም ሆነ በቀጣይ ዓለም በሰውም ሆነ በአላህ ፊት የሚያሳፍር ስፍራ ላይ አትገኝ።፥ የሚያስወቅስ ተግባር ተባባሪ አትሁን። የማህበራዊ ሚዲያ ዓለም አንዴ የጻፍካቸው ጽሑፎች፥ የተናገርከውን ንግግሮች እና የሠራኻቸው ቪዲዮዎች ከአጅህ ከወጡ በኋላ ላይመለሱ ተሰራጭተዋል። ሀሳብህን ብትቀይር ወይም መሳሳትህን አምነህ ይቅርታ ብትጠይቅ እንኳ የተሰራጩት እይታ እያገኙ ይቀጥላሉ። አላህ ዘንድ የምትጠየቀው በአንተ ገጽ ላይ ባሉ ተከታዮች ብቻ አይደለም። ስንቶች ሞተው ጭምር አሻራቸው በማህበዊ ሚዲያ ላይ ለዓመታት ሲዘዋወሩ እያን ነው። ያንተን ፈለግ (አሻራ) ማለት ሀሳብን የተጋሩና የደረሳቸው ሁሉ የሚተገብሩነን ያጠቃልላል። ለነርሱ ተግባራት ሚና ነበረህና የነርሱ መጠየቅ እንዳለ ሆኖ በሚሠሩት ጥፋት ሁሉ አንተም ትጠየቅበታለህ ። ፅሁፍ፦ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል ድምፅ፦ ሐቢብ በሽር

#Taaxagoonuh: Rabi xaagih caagid mango weeqa kee qawwalayla raaqe maral kataysak geytimam baxaa baxaa le waktittel takkeh tan tekkookak nasmitu xiqne. Tohuuk amakkaquk Ta saaqatak xabba haanam #rabi_xaagu elle xayi kee wagtah yan doolat dagarâ kalih mari cankâ caddol faxe qaynatal social medial yaybeleeleqeenim waaso lem aaxaguk garcite waytaanam sin naysixxige. Fidinuk elle aadarenno waqdi Share abaay farmo aabbe wee mara gufusa‼ Afar Kassis Media

አባት! ~ 4 አመት ሳለሁ ፡ አባቴ ከሁሉም ሰው የሚበልጥ ነው። 6 አመት ሳለሁ ፡ አባቴ ሁሉን ነገር ያውቃል። 10 አመት ሳለሁ : አባቴ ጎበዝ ነው፤ ግን ፀባዩ ከባድ ነው። 12 አመት ሳለሁ : ልጅ እያለሁኮ አባቴ ያዝንልኝ ነበር። 14 አመት ሳለሁ ፡ አባቴ በጣም ስሜታዊ እየሆነ ነው። 16 አመት ሳለሁ : አባቴ ከዘመኑ ጋር መሄድ አይችልም። 18 አመት ሳለሁ : አባቴ ጊዜ ባለፈ ቁጥር ሃይለኝነቱ እየባሰበት ነው። 2ዐ አመት ሳለሁ : አባቴን ይቅር ልለው ይከብደኛል። ግን እናቴ እንዴት ቻለችው? 25 አመት ሳለሁ : አባቴ ሁሉን ነገር ነው የሚቃወመው። 30 አመት ሳለሁ : አባቴ ጋር መግባባት ከባድ ነው። 35 አመት ሳለሁ : አባቴ በህይወቴ ሲያሳድገኝ ብዙ ህጎች ነበሩች። እኔም በልጆቼ ላይ እተገብራቸዋለሁ። 40 አመት ሳለሁ : አባቴ ግን እንዴት ይህን ሁሉ ልጅ ማሳደግ እንደቻለ ሳስበው ግራ ይገባኛል። 45 አመት ሳለሁ : ልጆቼን መቆጣጠር በጣም ከባድ ሆኖብኛል። አባቴ ግን እኛን ለማሳደግና ለመቆጣጠር ስንት መከራ ነው ያሳለፈው?! 50 አመት ሳለሁ : አባቴ ግን በብዙ ነገሮች ላይ እይታው ጥልቅ ነበር። የኔ አባትኮ እንደ ሌሎች አባቶች አይደለም! ከሰው የተለየ፣ አዛኝ ነበር። ከሁሉም በላጭ ነበር። የኔ አባት ከሁሉም በላጭ ነው ወደሚለው የ4 አመቱ መነሻ ለመመለስ ይህን ያህል ዓመት ፈጅቷል። አባቱ በህይወት ያለ ሰው ጊዜው ሳያልፍ በፊት መልካም ይዋል። አባቱ የሞተበት ደግሞ አላህ እንዲምረውና እንዲያዝንለት ዱዓእ ያድርግለት። (ከዐረብኛ ፅሁፍ የተመለሰ) = የቴሌግራም ቻናል፦ t.me/IbnuMunewor t.me/IbnuMunewor

Fakut yan taamah arac, faxa marak

Fakut yan taamah arac, faxa marak

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
+1
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ

+2
ACBAASH MA MARAAY ? 🔊 SHEK QALI QABDALLA

ሳይታወቀን የሸር መክፈቻ እንዳንሆን ~ የሆነ ጊዜ አንድ ጎረቤት ከሌላ ጎረቤቱ ቤት እየተጫወተ ይቆያል። ምግብ ቀረበ። ጎረቤት ከምግቡ ጋር የተያያዘ የቀልድ አስተያየት ጣል አደረገ፣ እንዲሁ እየሳቀ
ሳይታወቀን የሸር መክፈቻ እንዳንሆን ~ የሆነ ጊዜ አንድ ጎረቤት ከሌላ ጎረቤቱ ቤት እየተጫወተ ይቆያል። ምግብ ቀረበ። ጎረቤት ከምግቡ ጋር የተያያዘ የቀልድ አስተያየት ጣል አደረገ፣ እንዲሁ እየሳቀ ነበር። አንዳንድ እየተባለ በባልና ሚስት መሃል ያልታሰበ ከባድ ጥል ተከሰተ። ሲመስለኝ የቀደመ ክፍተት ኖሮ ጎረቤት ሳያስበው ሰበብ ሆኗል። የልጅነት ትዝታ ስለሆነ ዝርዝሩ ትዝ አይለኝም። ትዝ ቢለኝም የሚጠቅም አይደለም። ቀጥዬ ለማነሳው ነጥብ ማሳያ ምሳሌ እንዲሆነኝ ነው ያነሳሁት። ሚስትን ከባል፣ ልጅን ከወላጅ፣ ሰራተኛን ከአሰሪ፣ ጓደኛን ከጓደኛ፣ ሸይኽን ከሸይኽ፣ ማጋጨትና ማለያየት የከፋ ሸር እንደሆነ ለማንም ግልፅ ነው። ነገር ግን አንዳንዴ እንዲህ አይነት ጥፋቶችን ክፋትን ሳናስብ ልንፈፅመማቸው እንደምንችል እንዘነጋለን። * ታመህ ሊጠይቅህ የመጣ ሰው ምንም ክፋትን ሳያስብበት እንደዋዛ "እንትና ይጠይቅሃል?" ብሎ የጣለው ቃል ውስጥህን ሊያደፈርሰው ይችላል። * "ባልሽ ለጥሎሽ ያደረገው ይሄው ነው? የወለድሽ ጊዜስ? የኔኮ እንዲህ እንዲህ አድርጎልኛል?" የሚል ቃል ምናልባት ሚስትን በባሏ ላይ ቅሬታ ውስጥ ሊከት፣ እሱንም "አቅሜን እያወቀች ለምን ታጨናንቀኛለች? እንዴት አትረዳኝም?" እያለ ነገር ተጓጉኖ ያልተጠበቀ ውጤት ሊያስከትል ይችላል። * "ጓደኛህ እገሌ ግን ምን ሆኖ ነው ሰርግህ ላይ ያልተገኘው?"፣ "ሰራተኛሽ ምግብ ከናንተው ጋር ነው የምትቀርበው? ይሄማ ማቅበጥ ነው!"፣ "ልጅህ ምን ሆኖ ነው ለዒድ መጥቶ ያልዘየረህ?"፣ ... የመሳሰሉ ጥያቄዎች እና ሀሳቦች እንደዋዛ ጥለናቸው አልፈን ውጤታቸው የከፋ ሊሆን ይችላል። እና ባላሰብነው አቅጣጫ ሰዎችን ማቀያየም፣ ትዳርን ማደፍረስ፣ አሰሪና ሰራተኛን ማለያየት፣ ጓደኛና ጓደኛን ማራራቅ ውስጥ እንዳንገባ እላፊ ቃላትን ከመሰንዘር መጠንቀቅ አይከፋም። የአላህ መልእክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ፦ إن من الناسِ مفاتيحُ للخيرِ، مغاليقُ للشرِ، وإن من الناسِ مفاتيحُ للشرّ، مغاليقُ للخيرِ، فطوبى لمن جعلَ اللهُ مفاتيحَ الخيرِ على يديهِ، وويلٌ لمن جعلَ الله مفاتيحَ الشرِّ على يديهِ "ከሰዎች ውስጥ የኸይር መክፈቻዎች እና የሸር መዝጊያዎች የሆኑ አሉ። ሌሎች ደግሞ የሸር መክፈቻዎች እና የኸይር መዝጊያዎች የሆኑ አሉ። አላህ የኸይር መክፈቻዎችን እጁ ላይ ያደረገለት ሰው ምንኛ የታደለ ነው!! አላህ የሸር መክፈቻዎችን እጁ ላይ ያደረገበት ሰው ወዮለት!!" [አስሶሒሐህ፣ አልባኒይ፡ 1332] = የቴሌግራም ቻናል፦ t.me/IbnuMunewor t.me/IbnuMunewor

+1
1 Haytoh Exxa Acbaash Mamaraay.mp311.59 MB

+1
خطبة مكه١٤ جماد.mp325.56 MB

خطبة د.ادريس.m4a20.09 MB

Bidqa bilqisaanam isih bidqa.m4a66.91 MB

ከጁሙዐ ጋር የተያያዙ ጥቂት ነጥቦች ~ 1- መስጂድ ሳይሞላ በየ ጎዳናው በርቀት ሶፍ ሰርቶ መቀመጥ አይፈቀድም። 2- በቂ ቦታ እያለ ከኢማም ተቀድሞ መስገድ አይቻልም። ቦታ ከተጨናነቀ እና አማራጭ ከሌለ ግን ቢቀደምም ችግር የለውም። 3- ኹጥባ እየተደረገ ማውራት፣ በሰዎች ትከሻ ላይ እያቆራረጡ ማለፍ ክልክል ነው። በሞባይል፣ በሲዋክ (መፋቂያ) ራሱ መጠመድ አይገባም። ያንቀላፋ ከሆነ ብቻ እንቅልፉን ለማባረር ሲዋክ ሊጠቀም ይችላል ይላሉ ኢብኑ ዑሠይሚን። 4- በብዙ መስጂዶች የሚከስተው ጁሙዐ እየጠበቁ ረፋድ ላይ በድምፅ ማጉያ ቁርኣን መክፈት ሱና አይደለም። ሱናው ሱረቱል ከህፍም ሆነ ሌላ ሱራ በራስ መቅራት ነው። በድምፅ ማጉያ መክፈት በግላቸው የሚቀሩትን መወስወስ ነው። በዚህ ላይ የሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ሒዛምን ፈትዋ ማየት ይቻላል። 5- በየትኛውም ቀንና ጊዜ መስጂድ የገባ ሰው ኢማሙ ኹጥባ እያደረገ ቢሆን እንኳን ሁለት ረከዐ "ተሒየተል መስጂድ" መስገድ የጠነከረ ሱና ነው። 6- ጁሙዐ ቀን ዱዓእ እና ሶላት 0ለ ነቢ ማብዛት የተወደደ ነው። እዚህ ላይ ልምዱ አለን ግን? ትኩረት እንስጠው። 7- ለጁሙዐ ገላን መታጠብ ችላ ሊባል የማይገባው ተግባር ነው። ሽቶ መቀባት (ለወንድ)፣ መፋቂያ መጠቀም ተወዳጅ ተግባራት ናቸው። 8- ለወንዶች የጁሙዐ ሶላትን ከነ ጭራሹ አለመጥጣድ ከባድ ጥፋት እንደሆነ ሊያውቁ ይገባል። ተቀጣሪ ሰራተኞችና ተማሪዎች የሚጥጣዱባቸው መስጂዶች መዋጮ በማሰባሰብ እና በረጃጅም ኹጥባ የተነሳ ሰዎች ከጁሙዐ ሶላት እንዳይቀሩ መጠንቀቅ ይገባል። = የቴሌግራም ቻናል:- https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

ጫት ~ ጫት የዲን፣ የጤና፣ የቤተሰብ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊ ህይወት፣ የሃገር እድገት ፀር ነው። በጫት የተነሳ ትውልዱ ወኔው የፈሰሰ፣ ሞራሉ የላሸቀ የወጣት ጡረተኛ ሆኗል። የጫት ሱስ ወንድም በገዛ እህቱ ላይ፣ ወላጆች በገዛ ልጃቸው ላይ፣ ጎረምሶች በገዛ ወላጆቻቸው ላይ እንዲጨክኑ አድርጓቸዋል። በሰው ፊት ተገርፈው፣ ክፉ ደግ አይተው፣ እንቅልፍ አጥተው፣ ተንገላተው የሚያገኙት ገንዘብ ከጉዳት በስተቀር አንድ ቁም ነገር ለሌለው ነገር እንደ ዋዛ መበተን የጭካኔ ጥግ ነው። በዚህ የተነሳ እህቶቻችንና ወንድሞቻችን ለአመታት በሰው ሃገር ደክመው ያጠራቀሙት ጥሪት እንዲሁ መና ቀርቷል። የጫት ጉዳት ከሚገለፀው በላይ የከፋ ነው። ለችግሩ መባባስ አንዱ ሰበብ ደዕዋ ላይ ያሉ ሰዎች የችግሩን ስፋትና ጥልቀት ባገናዘበ መልኩ ተገቢ ትኩረት ሰጥተው አለማስተማራቸው ነው። አሁንም በሚገባ ልንነቃ ይገባል። የወገናችን ጉዳት የሚያመው፣ ከልቡ መቆርቆር ያለው ሁሉ! በሚችለው መድረክ ሁሉ ከዚህ መርዛማ ቅጠል ሰዎችን ሊያስጠነቅቅ ይገባል። በዚህ ቅጠል የተለከፉ ወገኖችን ከሱስ ማውጣት ቢያቅተን እንኳ ቢያንስ ልጆቻቸውን በሚጠብቁበት መልኩ በቂ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ብናደርግ ቀላል ስኬት አይደለም። ~ የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

Acbaash Umaane kee ken uma qaqhiida macaay? Oson Mamaraay? #shekh_qali_q... https://youtube.com/watch?v=nbTHAhaiZ-8&si=lufXiZHhN2WE5mNo

ቁርአን ለመቅራት እያሰብን በsocial media ምክንያት የምንዘናጋ ሰዎች አንድ ናይጄሪያዊው ወንድማችን የሚገርም አፕ ሰሮቷል። ቁርአን መቅራት የምንፈልግበት ወቅትና ለስንት ደቂቃ መቅራት እንፈልጋ
ቁርአን ለመቅራት እያሰብን በsocial media ምክንያት የምንዘናጋ ሰዎች አንድ ናይጄሪያዊው ወንድማችን የሚገርም አፕ ሰሮቷል። ቁርአን መቅራት የምንፈልግበት ወቅትና ለስንት ደቂቃ መቅራት እንፈልጋለን የሚለውን set እናደርጋለን ከዛ ፌስቡክ ወይም ሌላ ማህበራዊ ሚዲያ ለመግባት set ያደረግነው ደቂቃ ያክል ቁርአን መቅራት ይጠበቅብናል ካልሆነ አይከፍትም። በዚህ ሊንክ ተጠቀሙ https://play.google.com/store/apps/details?id=com.app.quranunlock ለአይፎን:- https://apps.apple.com/ng/app/quran-unlock/id6754449406

እንዲህ አይነት ሰዎች በኃላፊነት ላይ እስካሉ ድረስ፤ ኡማው በአላህ ፈቃድ ከኸይር አይወገድም‼ እኚህ ሰው የአማራ ክልል መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ኑረዲን ቃሲም ሲሆኑ፤ በትናንትናው ዕለት በደሴ ከተማ በሚገኘው ደዌ ሜዳ መስጂድ ካደረጉት የጁሙዓህ ኹጥባህ የተወሰደ ነው። ©: Video Credit: ነሲሓ ቲቪ / Nesiha Tv