Diinii kee Anaakara (Md Ali)
前往频道在 Telegram
دروس وفتاوي ومحاضرات باللغة العفرية ★Diini barittooy, fatwaa kee Daqwa Qafar afat Tû mabul=> @Anaakar or @acmadxalol
显示更多1 612
订阅者
+324 小时
+117 天
+1830 天
帖子存档
Repost from 𝐃𝐈𝐈𝐍𝐈 𝐆𝐎𝐎𝐑𝐈 𝐌𝐄𝐃𝐈𝐀
Rufto le xaagu Qilmi barisiyyaKitab: arbaqiin alcadiis sharci Arac: logyak markazul icsaan Barseeni: dr Macammad cusen Uddur: ummaan sabtii kee caadah saaki saalitih laka Mamaata edde bicta marak maraaqina edde bice wayta marak inshaa-allaah a group'il siinih ruubenno https://t.me/diini_goori_media
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ጫት
~
ጫት የዲን፣ የጤና፣ የኢኮኖሚ፣ የቤተሰብ፣ የማህበራዊ ህይወት፣ የሃገር እድገት ፀር ነው። በጫት የተነሳ ትውልዱ ወኔው የፈሰሰ፣ ሞራሉ የላሸቀ የወጣት ጡረተኛ ሆኗል። በጫት ሱስ በደነዘዙ ቤተሰቦች ጭካኔ የተነሳ እህቶቻችንና ወንድሞቻችን ለአመታት በሰው ሃገር ደክመው ያጠራቀሙት ጥሪት እንደ ዋዛ መና ቀርቷል። የጫት ጉዳት ከሚገለፀው በላይ የከፋ ነው።
ለችግሩ መባባስ አንዱ ሰበብ ደዕዋ ላይ ያሉ ሰዎች የችግሩን ስፋትና ጥልቀት ባገናዘበ መልኩ ተገቢ ትኩረት ሰጥተው አለማስተማራቸው ነው። አሁንም በሚገባ ልንነቃ ይገባል። የወገናችን ጉዳት የሚያመው ሁሉ! በሚችለው መድረክ ሁሉ ከዚህ መርዛማ ቅጠል ሰዎችን ሊያስጠነቅቅ ይገባል። በዚህ ቅጠል የተለከፉ ወገኖችን ከሱስ ማውጣት ቢያቅተን እንኳ ቢያንስ ልጆቻቸውን በሚጠብቁበት መልኩ በቂ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ብናደርግ ቀላል ስኬት አይደለም።
~
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ለመጀመሪያ ጊዜ ወይም ለሁለተኛ ጊዜ የተፈታች ሴት ዒዳዋ እስካልተጠናቀቀ ድረስ ለባሏ ፊቷን መግለጥ፣ መዋዋብ፣ ከሱ ጋር ማውራት፣ ተገልሎ መቀመጥ ትችላለች። ግንኙነት የሚፈፀመው ግን ከመለሰ በኋላ ወይም በመመለስ ኒያ ሲሆን ነው።
ዒዳዋ ካላለቀ በቀላሉ መመለስ ይችላል። ዒዳዋ ከተጠናቀቀ በኋላ መመለስ ቢፈልግ ግን አዲስ ኒካሕ ነው በወሊይና ሁለት ምስክር የሚያስረው።
ለሶስተኛ ጊዜ ከፈታ ግን ከዚህ በኋላ መመለስ የሚችለው በትክክለኛ ኒካሕ ሌላ ሰው አግብታ ግንኙነት የተፈፀመበት ጋብቻ ሆኖ ከተፈታች ብቻ ነው። በሃገራችን የተለመደው ለቀድሞ ባሏ ሐላል ለማድረግ ታስቦ የሚፈፀም ጊዜያዊ ጋብቻ እጅጉን የተወገዘ ተግባር ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ልጅህን አባት ያለው የቲም አታድርገው!
~
ልጆች ከአላህ የተሰጡ አማናዎች ናቸው። አማናን ባግባቡ አለመጠበቅ ነውር ነው። ዘመኑ እንደምናየው ከባድ ነው። የልጆችን ህይወት የሚያበላሹ ነገሮች በጣም በዝተዋል። የአደጋ ስጋት ሲጨምር ጥንቃቄያችን መጨመር ነበረበት። እኛ ግን ይበልጥ እየተዘናጋን ነው። በገዛ ገንዘብህ፣ እጅህ ላይ ባለው ሞባይል፣ ቤትህ ውስጥ ባለው ቴሌቪዥን ልጆችህን እያጠፋሃቸው እንዳይሆን ተጠንቀቅ። ልጅህ ልጅ ነው። የነገ ህይወቱን ሳይሆን የዛሬ ደስታውን ነው የሚያየው። ቅፅበታዊ ኩርፊያውን ፈርተህ፣ የእለት ደስታውን ብቻ እያየህ የጠየቀውን ሁሉ አትስጥ። የሚያስፈልገውን እንጂ የሚፈልገውን ሁሉ አታድርግ።
ትንፋሽ እስከሚያጣ አስጨንቀው እያልኩህ አይደለም። ግን ዛሬ ቁርኣን ካልቀራ፣ ዲኑን ካላወቀ፣ ትምህርት ካልተማረ መቼ ሊማር ነው? አባትነት ልጆችን ቆፍጠን ብሎ በስርአት ለማሳደግ ካልሆነ ምን የረባ ትርጉም አለው? አኺራውንም ይሁን ዱንያውን በተመለከተ ስለ ነገ ህይወቱ አንተ ካልተጨነቅክለት ማን ይጨነቅለት? አባትነትህ ለዚህ ካልሆነ ለምን ይሁን?
ስለ ልጅህ ስታስብ ልብሱና ጉርሱ ላይ አትቁም። ነጣ ገረጣ፣ ከሳ ኮሰሰ፣ ሳቀ አኮረፈ ላይ ብቻ አታተኩር። "ለነገ ምን ይዟል?" በል። ለሃላፊነት አዘጋጀው። ህይወት ከባድ ትምህርት ቤት ናት። ብዙ መውጣት መውረድ አላት። ነገ ምን እንደሚገጥመው አታውቅም። ሁሌ አብረኸው አትሆንም። ብትሆንም አቅምህ ውስን ናት። ጥገኝነትን አታለማምደው። ካንተ የተሻለ እንጂ ያነሰ እንዲሆን አትተወው። ከመስመር ወጥቶ ከሆነ በጊዜ ወደ ቦዩ መልሰው።
ይጫወት ፋታ ስጠው። ግና ቁም ነገረኝነትን አስተምረው። ያለበለዚያ አካሉ ቢያድግም ከልጅነት ስነ ልቦና አይወጣም። በሰላሳ አመቱም የሰው እጅ የሚጠብቅ ጥገኛ ይሆናል። ሌሎችን በሚጦርበት እድሜው ተዘፍዝፎ በአዛውንቶች ይጦራል። ከእህቱ እየነጠቀ ሱስ የሚያሳድድ ጅል ፈጥረት ይሆናል።
ባጭሩ ለልጅህ የእውነት አባት ሁነው። ከልብ አንፀው። መኖርህ በልጅህ አስተዳደግ ላይ ትርጉም ያለው ልዩነት ይኑረው። ልጅህን በአደብ፣ በእውቀት ተከትኩቶ እንዲያድግ ካላገዝከው በህይወት እያለህ የቲም አድርገኸዋል። የአባትን መኖር ትርጉም ነፍገኸዋል። የምታሳድገው ልጅ የቤተሰብ ማፈሪያ፣ የማህበረሰብ እዳ፣ የሃገር ሸክም ከሆነ በሃገርም በወገንም ላይ ትልቅ በደል ነው የፈፀምከው። ይሄ ህዝብ ጀርባውን ያጎበጠው ብዙ ሸክም አለበት። ሌላ ሸክም አትጨምርበት። ለራስህም ቢሆን ነገ በፀፀት እጅህን ከመንከስህ በፊት ዛሬ ሃላፊነትህን ባግባቡ ተወጣ። አባት ሁን። አባት!
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሰዑዲያ ዑለማኦች ጥፋት እያዩ ዝም ይላሉ ለሚሉ!
ሸይኽ ሷሊሕ አልዑሶይሚይ - አላህ ይጠብቃቸውና - ድንቅ ምላሽ ይሰጣሉ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሰዑዲያ ዑለማኦች ጥፋት እያዩ ዝም ይላሉ ለሚሉ!
ሸይኽ ሷሊሕ አልዑሶይሚይ - አላህ ይጠብቃቸውና - ድንቅ ምላሽ ይሰጣሉ።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ለምንድን ነው ስደውል ያላነሳሽው?
አስተማሪ ታሪክ
~
ለሆነ ጉዳይ ለሶስት ቀናት መንገድ ወጣሁ። ሌላኛው ሃገር እንደደረስኩ ሚስቴንና አንድ ልጄን ደህንነታቸውን ለማስረገጥ ደወልኩ። ከዚህ በፊት ከነሱ ተለይቼ አላውቅም። እነሱም መራቄን አያውቁትም። ካገባሁ ሶስት አመቴ ነው። የሆነ ሆኖ ስልኬ አልተነሳም። ስልኬ ከእጄ ሳይነጠል ሶስት ቀናት አለፉ። ያለ ግነት በየ እሩብ ሰዓቱ ቢበዛ በየ ግማሽ ሰዓት እደውላለሁ። ምላሽ የለም።
በሃይለኛ ተበሳጨሁ። ወንድሜ እና እህቴ ላይ ደወልኩ። የትንሿን ቤተሰቤን ደህንነት እንዲያረጋግጡልኝ ጠየቅኳቸው። ሰላም እንደሆኑ ነገሩኝ። አላመንኳቸውም።
የሚስቴ እናት (አክስቴ) ላይ ደወልኩ። ሰላም እንደሆኑ ነገረችኝ። ስልካቸውን እንደምጠብቅ ነገርኳት። ብጠብቅ ብጠብቅ አንድም የሚደውል የለም።
ሶስቱ ቀናት ረጃጅም ሶስት ወራት ያክል ሆነው አለፉ። አንዳንዴ ቁጣዬ ከውስጥ ሲገነፍል ይሰማኛል። ሌላ ጊዜ በሁኔታው በጣም እየተገረምኩ ምክንያቱን ለማወቅ እሞክራለሁ።
ሸይጧን አስፈሪ ጉትጎታዎችን ደግሞ ደጋግሞ ያመጣብኛል። ቀናቱ አለፉ። ወደ ሃገሬ ተመለስኩ። እግሬ እንደረገጠ ወደ ቤቴ ነበር የበረርኩት። እንደደረስኩ በሩን አንኳኳለሁ። እሱም ሳይበቃኝ ደወሉን ላይ በላይ እደውላለሁ። ባለቤቴ በሩን ከፈተች። ከነ ሙሉ ውበቷ፣ ከነ ሙሉ ድምቀቷ። ባማረ በደመቀ ሁኔታ ተቀበለችኝ። ከባድ አጋጣሚ ነበር። ልጄ ከኋላዋ አለ። አይኖቹ በደስታ ይጨፍራሉ። ሊያቅፈኝ እየሮጠ መጣ። እኔ እንደደነዘዘ ሰው ሆኛለሁ። ሰበቡም ጠፋኝ። በፍጥነት በቁጣዬ ቦታ ግርምት ተተካ።
ባለቤቴን የዚህ ሁሉ ቸልትኝነት ምክንያቱ ምን እንደሆነ ጠየቅኳት። ጉዞዬን አቋርጬ በፍጥነት ልመለስ ተቃርቤ ነበር። አጉል ጥርጣሬ ከያቅጣጫው ወሮኝ ነበር።
ባለቤቴ ተረጋግታ መለሰችልኝ። "ለእናትህ ደውለሃል?" አለችኝ። ለምን እንደጠየቀችኝ ምክንያቷ ባይገባኝም እንዳልደወልኩ ነገርኳት። ንግግሯ ገዳይ ነበር ። እንዲህ አለችኝ፡ "በነዚህ ቀናት ውስጥ ስሜትህ ምን እንደሆነ አየህ አይደል? የእናትህም ስሜት ይሄው ራሱ ነው፣ ለቀናት ሳትደውልላት ስትቆይ። ናፍቆት ለብልቧት፣ ስጋት ገብቷት እሷ ካልደወለች በቀር አንተ ደውለህ ድምጿን አትሰማም። ይሄን ጉዳይ በተደጋጋሚ ላስረዳህ ሞክሬያለሁ። የምትረዳ ግን አልሆንክም። ክቡር ባለቤቴ! ከዚህ የተሻለ መልእክቴን የማደርስበት መንገድ አላገኘሁም።
እድሜዋ ትንሽ ዐቅሏ ግን ትልቅ የሆነችዋን ሚስቴን አፈርኳት። አንገቴን ደፋሁ። ትምህርቱ በሚገባ ነው የደረሰኝ። የመኪናዬን ቁልፍ እያቀበለችኝ ወደ ጀሮዬ ጠጋ ብላ "ጀነትህ እየጠበቀችህ ነው" አለችኝ።
እድሜ ልኬን የማልረሳውን ትምህርት ከጠቢቧ ሚስቴ ተምሬ ወደ መጀመሪያዋ ውዴ ወደ እናቴ ሄድኩኝ። ፀፀት በማይጠቅምበት ቀን ከመፀፀት ነፍሴን ስላተረፈችኝ ውለታዋን መቼም አልረሳም። ለዚች ጠቢብና አስተዋይ ሚስት ምስጋና ይገባታል። አሳምራ ኮትኩታ ላሳደገቻት እናቷ ምስጋና ይገባታል። እሷን ለመረጠችልኝ እናቴ ምስጋና ይገባታል።
እሷን ሰበብ አድርጎ በእዝነቱ ከእንቅልፌ ያነቃኝ ጌታ ምስጋና ይገባዋል።
እናቴ! እናታቶቻችሁ ! በዱንያ ያሉ ጀነቶቻችን ናቸው። ሌላው ቢቀር በየቀኑ በመደወል እንኳ ቢሆን አትርሷቸው። ይሄ ትንሹ ነገር ነው። ልቦቻቸው እኛን ይጠብቃሉ። ለኛ ዱዓእ ያደርጋሉ። በየ ሰዓቱ ስለኛ ይጨነቃሉ። እያሰቡ እየተጨነቁም ደጋግመው በመደወል እንዳይረብሹን በመስጋት ከመደወል ይታቀባሉ። ባሎቻችሁን፣ ሚስቶቻችሁን ወላጆቻቸውን እንዲያስቡ በማስታወስ አግዙ።
ከ0ረብኛ የተመለሰ
የብዙዎቻችን በተለይም የወንዶች ችግር ነውና እንድንማርበት ብታሰራጩት ባረከላሁ ፊኩም።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 26/ 2017)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
محاضرة على محاسبة النفس
جامع الإحسان
بمدينة لوغيا إقليم عفر إثيوبيا 🇪🇹.
محاضرة على محاسبة النفس: فضيلة الشيخ الدكتور محمد حسين
22جمادى الأولى 1446ه
شبكة فجر العفر -Afar Maha Network:
https://t.me/AfarMahaNetwork/937?single
Repost from 𝐃𝐈𝐈𝐍𝐈 𝐆𝐎𝐎𝐑𝐈 𝐌𝐄𝐃𝐈𝐀
Meqe toobokoy siinih warisneh sugne tajwiid darsi Inshaa-allaah abar 2:00 pm qinbimele cule kal yan marak culaay bical suga
https://t.me/qhuraantajwid
Repost from 𝐀𝐟𝐚𝐫 𝐊𝐚𝐬𝐬𝐢𝐬 𝐌𝐞𝐝𝐢𝐚
Wagga hayisaay, badita mari yenek share aba. " Yallih farmoytih (q.s.w) Cadiis moggolna" iyya maray sinam badisah yanih gacsa tamakkel geya.
https://youtu.be/3e3qwddo7-w
خطبة الجمعة
جامع الإحسان
بمدينة لوغيا إقليم عفر إثيوبيا 🇪🇹.
الخطيب : فضيلة الشيخ الدكتور محمد حسين
20جمادى الأولى 1446ه
شبكة فجر العفر -Afar Maha Network:
https://t.me/AfarMahaNetwork/937?single
Repost from Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹
ጥቂት ስለዚህ ነገር‼
===============
✍ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሃገረ ሳዑዲ ዓረቢያ በተለይም በዋና ከተማዋ ሪያዽ አንዳንድ የሚያሳዝኑና የሚያሳፍሩ ነገሮችን እየታዘብን ነው። በተለይም በፈረንጆቹ 2019 ላይ በሃገሪቱ General Entertainment Authority በኩል የተጀመረው Riyadh Season (موسم الرياض) ብለው በየአመቱ የሚያዘጋጁት የመዝናኛ ፈሳድ ፕሮግራም ከጊዜ ወደ ጊዜ የሃገሪቱን ሰናይ ገፅታ በሙስሊሙ ዓለም ዘንድ እያጠለሸው ነው። ሃገሪቱ በሁሉም ዘርፍ ተግታ የያዘችው Vision 2030 እንደ ማጠናከሪያ አድርገው ያሰቡት ይህ ፈሳድ፤ የሃገሪቱን ኢኮኖሚ ከነዳጅ ጥገኝነት ለማውጣት ከሚያግዙት መንገዶች መካከል አንዱ ነው ተብሎ ቢታሰብም ከዲን አንፃር ኪሳራ ነው።
ይህንን ድርጊት ጤነኛ ሙስሊም ሁሉ ያወግዘዋል። እንዳውም ይህን በማውገዝ ረገድ ሳዑዲን የሚወዱ ይቀድማሉ። ምክንያቱም የምትወደው አካል ላይ መጥፎ ማየት ስለማትሻ! ግን የሚያወግዙት ከዚህ ፈሳድ የባሰ ፈሳድ በማያመጣ መልኩ እንጂ ይህን ተገን አድርጎ ቀድሞውንም የነበረን ጥላቻ መሰንዘሪያ አይደለም።
እንደ አለመታደል ሆኖ፤ እንኳን እንዲህ አይነት ፈሳድ ሲሠራ ተመልክተው ሳዑዲ የትኛውንም መልካም ነገር ብትሠራ ምንም የማይመስላቸው አካላት፤ ሁልጊዜ የርሷን መጥፎ ገፅታ ሰዎች ዘንድ አጉልተው በማሳየት በሙስሊሙ ዓለም ጭራቅ ተደርጋ እንድትሳል በብዙ ዘመቻዎች ይፈታተኗታል። ሩቅ ሳንሄድ እዚሁ እኛው ሃገር ውስጥ ያሉ ህልማቸው ከሽፎባቸው መሃል መንገድ ላይ ሟምተው የቀሩት ኢኽዋኖች እና ቀድሞውኑም ሳዑዲን የውሃብያ መፈልፈያና ደጋፊ አድርገው የሚስሉት አሕባሾችና ሱፍዮች እንዲሁም ወይ በግልፅ ሺዓህ አልሆኑ አሊያ የለየላቸው ኢኽዋን ወላዋዮች፤ እንዲህ አይነት ነገሮችን ሳዑዲ ላይ ማየታቸው መተቻ መንገድ ስላገኙ ድርጊቱ ሰርግና ምላሽ ነው።
በተሽሞነሞኑ ቃላት፣ ተቆርቋሪ በሚመስል ስሜታዊ ሰበካ የአዞ እንባ እያነቡ ሳዑዲን የሚተቹት በተፈፀመው ድርጊት አዝነውና የእውነት ለዲን ተቆርቁረው ሳይሆን፤ ጥላታችን የሚሏትን ሳዑዲ ከህዝበ ሙስሊሙ መነጠያ ዘዴና ጥሩ አጋጣሚ ስለመለሰላቸው ነው።
ለዛም ነው በዚህ ድርጊት ላይ ተረማምደው ብርቅዬ ዑለሞቿን ቂጣ በቀደደ አፋቸው ያለ አቅማቸው ተንጠራርተው የሚወርፉት፣ እንደ ጥቅል እንደ ጭራቅ የሚስሉትንና የፈሳድ ህልማቸው አክሻፊ የሆነውን ሰለፊያ ዳዕዋን በደፈናው የሚተቹት።
እነዚህን የፈሳድ ቪድዮዎችና ምስሎች ከልክ በላይ አቀናብረውና አጋነው ተቆርቋሪ በመምሰል ሲያሰራጩ፤ ለዲኑ የሚቆረቆረው ንጹሕ ሙስሊም ቅድሚያ ለዲኑ ይሰጣልና ሳዑዲን ይወርፋል፤ ቀስ በቀስ ወደ ዑለሞቿም «ለምን አያወግዙም!» ብሎ ይወርፋል። ያውግዙ አያውግዙ አይተሃል? እንኳንን ይህንን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተጀመረ ግልፅ ፈሳድ፤ እንደነ ኢብኑ ባዝ ያሉ ታላላቅ ዑለማዎች የሳዑዲን የምስረታ ቀን ማክበርንም ሳይቀር አውግዘዋል። ግን የሃገሪቱ መሪ በዑለሞች የተወገዘውን ሁሉ ሰምቶ ሁሉንም ይተገብራል ማለት አይደለም። የዑለማዎቹ ሥራ በሸሪዓው መሠረት ሐራምን ሐራም፣ ሐላልን ሐላል ማለት እንጂ ጦር ሰብቆ መንግስት ላይ ማዝመት አይደለም።
ደግሞ አንዳንዶች ቅዲሲቷን ሳዑዲ የምትሉት «ከመካና መዲና» ውጭ ቅዱስ ስፍራ አለ እንደ? ሪያዽ ቅዱስ ስፍራ ነው ያለው ማነው? ባይሆን ቅዱስ ካልሆነ ፈሳድ ይሠራበት እያልኩ አይደለም። አላህ የትም ቢሆን መታመፅ የለበትም። ነገር ግን እይታችንን አናጥበው ለማለት እንጂ!
በነገራችን ላይ ሳዑዲን ለመተቸት ከመቋመጣቸው የተነሳ ሰሞኑን እንደ አዲስ እያሽከረከሩት ያለውና በካዕባህ አምሳያ የተሠራ ብለው እያሽከረከሩት ያለው ከታች ያያዝኩት ምስል ባለፈ አመት በ2023 የነበረ ነው። የእውነት የሐቅ ተቆርቋሪ ከሆኑ ያኔውኑ ለምን አላወገዙትም? ግን ሰሞኑን በፈለስጢን ጉዳይ የሆነ ጠበቅ ያለ ተቃውሞ አሰምታለች መሰል ያንን ሸፋፍነው ይህንን ካለፈ ቪድዮ ቆርጠው አምጥተው እያሰራጩት ነው። በርግጥ ሌላ አለ ዘንድሮ ያዘጋጁት። የሰዎቹ ነገረ ሥራ እንጂ ጉዳዩ ባለፈ አመትም ይሁን ዘንድሮ የሚወገዝ መሆኑን ልብ ይሏል።
እነዚህ ሰዎች ኢራን ወይም ቱርክ ወይም ኳታር ወይም ሑቲዎች ወይም ሒዝቡ-ል'ሏህ ቢፈሱ፤ ፈለስጢንን ለማገዝ "ወደ እስራኤል ሚሳኤል እያስወነጨፉ ነው!" ነው የሚሉት፤ ሳዑዲ ወደ እስራኤል ብትተኩስ ግን "ሙከራ ለማካሄድ አስባ በስህተት አቅጣጫ ስቶባት ነው!" ብለው ሊፈስሩት ይችላሉ።
ለማንኛውም ሰዎች እንዳይሸወዱ በማሰብ፣ ማስተማርን በማሰብ፣ ሸሪዓውን ባማከለ መልኩ የሚደረገውን ፈሳድ ሁሉ ጥቅምና ጉዳቱን አመዛዝነን ሳናሽሞነሙን እንቃወማለን። ሳዑዲም ትፈፅመው ኢራን አሊያም ቱርክና ኳታር!
ግን ይህ ማውገዛችን ስሜታቸውን ጋልበው ለሚሄዱ ሳዑዲ ጠሎች የልብ ልብ በሚሰጥና እኩይ አላማቸውን ለማሳካት በር በሚከፍት መልኩ መሆን የለበትም።
ምክንያቱም ፈሳድ ለማውገዝ የግድ ፈሳድ መፈፀም አያስፈልግምና! ሽንት በሽንት ስለማይፀዳ!
አላህ ሳዑዲንና መሪዎቿን፣ ዑለማዎቿንና ህዝቦቿን ይጠብቃቸው፣ በዚህ ፈሳድ ላይ ለተሰማሩ ሁሉ አላህ ቀጥተኛውን መንገድ ይምራቸው።
♠
||
t.me/MuradTadesse
x.com/MuradTadesse
fb.com/MuradTadesseOfficial
Repost from 𝐃𝐈𝐈𝐍𝐈 𝐆𝐎𝐎𝐑𝐈 𝐌𝐄𝐃𝐈𝐀
RUFTO LE XAAGUAssalaamu qaleykum Waracmatullaahi wabarakaatuh Qhur-aan kak yaanam yallih yaabaay , dudda hee mari elle oobe gurral kaa yakriyeenim faxxinta 👌 Yeey meqe toobokoy axcem faxam nanu qafarak 100% muslim kinnino inna takkay ikkah muslimiinik ugutuh yan qhur-aan nagay bicisaah kaal qalalaah dubuh kay taama le mari nek mayan /dagoh , away qaalamal qhur-aanal mango qalayli (musaabaka) takke laakin qafar baxa edde ablu affareh tah kak takku duddem macaay? Barasa marih wayti innaa??? Dumih inna hinnay away qafar addal (#qashru_qhiraa-a) qhur-aan 10 weelol inkih yikriye toobokoytay madiinah jaamiqak dooqaysime naddal yan ta toobokoyti qafar ummatta barittoh leh yan waktik tu keenih hayuh gulguluh yan Axcih umman baaxol yan qafar baxi kah bartannah Telegram channel fakah gaytima Darsi dagoo ayrooraak lakal qinbise leemih taagah a channel subscribe abaay sinni kataysiisih warisa Darsi namma weelol akkele تجويد قراءة Tonna kinnuk qhur-aan iccfizza hee marak a Link xagak subscribe aba https://t.me/ustazsirajhummo
#Qunxaaneyti rihimam faxximtaamal yabta khutba.
🎙 Khutba lem: Shek Cuseen Acmad Cafizahullaah
⤵️⤵️⤵️
https://t.me/Kassisfaage
+1
Limo kaak 51 alfiiy aham fanah facebookul abne uguugusul 3,720 culeh yan.
Duddaanam
[Name] Ahmed Ali Hussen
[Account] 1000370821783
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
