ch
Feedback
Central Ethiopia Regional Health Bureau

Central Ethiopia Regional Health Bureau

前往频道在 Telegram

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ 🔵 https://m.facebook.com/centralethiopiarhb 📞 📩

显示更多
4 312
订阅者
无数据24 小时
+87 天
+2330 天
帖子存档
የማ/ኢት/ክ/መ/ ጤና ቢሮ "ውጤታማና ቀልጣፋ አገልግሎት ለሀገር ግንባታ በሚል መሪ ቃል ከቢሮ ጠቅላላ ሰራተኞች ጋር ውይይት እየተደረገ ነው። በ2017 ዓ.ም የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ንቅናቄ ማስፈፀሚያ ዕቅድ ላይ ውይይት በማድረግ በ2016 ዓ.ም በጥንካሬ የተለዩ ጉዳዮችን በማጠናከር በጉድለት በሚለዩ ጉዳዮች ላይ የማጎልበቻ ስልት ለመንደፍ አጋዥ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል። በውይይት መድረኩ ውጤታማና ቀልጣፋ አገልግሎት ለሀገር ግንባታ በሚል መሪ ቃል በቢሮ ነባራዊ ሁኔታ በተዘጋጀው የ2017 ዓ.ም የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ንቅናቄ ማስፈፀሚያ ዕቅድ ሰነድ በክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የአስተዳደርና ፋይናንስ ዘርፍ በአቶ መሀመድ አሚን ቀርቧል። በቀረበው ሰነድ መነሻ ችግር ፈቺ ውይይት እየተደረገ ይገኛል። የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ

ዜና ሹመት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ እንዳሻዉ ጣሰዉ የ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ የተግባራት አፈጻፀምን መነሻ በማድረግ ባደረጉት የአመራር ምደባና ሽግሽግ መሰረት:- የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ሀላፊ የነበሩት አቶ ሽመልስ ዋንጎሮን በአደጋ ስጋት ስ/አ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነርና አደጋ መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ሆነው እንዲያገለግሉ በዛሬው ዕለት ተሹመዋል፡፡ የተከበሩ የአቶ አቶ ሽመልስ ዋንጎሮ የቀድሞ የስራ ባልደረቦች በሄዱበት መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንልዎ ተመኝተዋል ።

ዜና ሹመት የተከበሩ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ ሆነዉ ተሾሙ፡፡ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ እንዳሻዉ ጣሰዉ የ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ የተግባራት አፈጻፀምን መነሻ በማድረግ የአመራር ምደባና ሽግሽግ አድርገዋል ። በዚህም መሰረት:- የተከበሩ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል ። የተከበሩ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የስራ ሀላፊዎችና ሰራተኞች መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንልዎ ተመኝተዋል ።

የቆሻሻ አወጋገድን በማስተካከል ውብና ማራኪ ስፍራን መፍጠር እንደሚገባ ተገለፀ ። ሃምሌ 12/2016፣ወልቂጤ፣የቀ/ል/ወ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት በቀቤና ልዩ ወረዳ ፅዱ መንደርን ለመፍጠር እና የተዘጉ ዲቾችን በመክፈት የወባ በሽታን ለመከላከል ያለመ የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል፡፡ የአከባቢ ፅዳት ዘመቻውና የዲች ከፈታ ስራው በልዩ ወረዳው ኬላ አከባቢ ጀምሮ እስከ ቀቤና ባህል አዳራሽ ድረስ በቀቤና ልዩ ወረዳ ብልፅግና ፅ /ቤት አስተባባሪነት ተካሂዷል ። በፅዳት ዘመቻውና በዲች ከፈታው ስራ ላይ በስፍራው የተገኙት የቀቤና ልዩ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አቡበክር ዱላ እንደተናገሩት በየአካባቢው የሚጣሉ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻዎች ለጤና ጠንቅ በመሆናቸውንና ቦዮችን በመዝጋት ለወባ ትንኝ መራቢያ ምቹ ሁኔታ ስለሚፈጥር ቆሻሻ በአግባቡ ሊወገዱ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በተጨማሪም ህብረተሰቡ አካባቢውን በማጽዳት ከተላላፊ በሽታዎች እራሱንና ቤተሰቡን መጠበቅ ይኖርበታል ሲሉ አሳስበዋል። ኃላፊው አክለውም የፅዳት ዘመቻው የክረምት በጎ ፍቃድ አንድ አካል በመሆኑ በዘላቂነት እንደሚሰራ ገልጸው የልዩ ወረዳው ከተማ ልማት ጽ/ቤትም በልዩ ትኩረት በመስራት ለአካባቢ ጽዳትና ውበት የድርሻውን መወጣት አለበት ብለዋል። የቀቤና ልዩ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ድርባ ቡልቡላ በበኩላቸው እንደተናገሩት ህብረተሰቡ ከግቢውና ከንግድ ተቋሙ የሚወጡ ቆሻሻዎችን በአግባቡ ማስወገድ እንደሚገባው ጠቁመው በቀጣይም ጽ/ቤቱ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። በፅዳት ዘመቻው የቀቤና ልዩ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የስራ ኃላፊዎች ፣ የልዩ ወረዳው ካቤኔና አመራሮች፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ የወጣቶች ሊግ፣ የማህበርና ፌዴሬሽን አባላት አመራርና ወጣቶች ተገኝተው አፅድተዋል ። *** #ውጤታማ ተግባቦት ለሀገር አንድነት ❗️ ለቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ዘገባ የማ/ኢት/ክ/መ/ ጤና ቢሮ

የጨቅላ ህጻናት እና የህጻናት ጤና አገልግሎት የ2016 ዓ.ም የ11 ወራት አፈጻጸም ግምገማ በመካሄድ ላይ ነው።  የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ የእናቶች ህጻናትና ስርዓተ ምግብ አገ/ት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሌጂሶ መንግስት የጨቅላ ህጻናትን እና የህጻናትን ጤና ከማሻሻል አኳያ በርካታ ተግባራትን አያከናወነ እንደሚገኝ በመግለጽ ውጤቶች መመዝገባቸውን አመላክተዋል። ማህበረሰብ ተኮር የጨቅላ ህጻናትና የህጻናት ጤና አገ/ት በጤና ኬላ የሚሰጥ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ተስፋዬ የተኝቶ ህክምና አገ/ት በጤና ጣቢያ እና በሆስፒታል የሚሰጥ አንደሆነ ገልጸዋል። የጨቅላ ህጻናት እና የህጻናትን ጤና በማሻሻል ረገድ በጤና ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን በልዩ ትኩረት መፈጸም እንደሚገባ የተናገሩት ዳይሬክተሩ የጨቅላ ህጻናት እና የህጻናትን ጤና በማሻሻል የሚጠበቀውን ውጤት ለማስመዝገብ የጤና ባለሙያው እና ሁሉም ባለድርሻ አካላት አይተኬ ሚናቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። በዚህ መድረክ የጨቅላ ህጻናት እና የህጻናት ተኝቶ ጽኑ ህክምና አገ/ት፣ የጨቅላ ህጻናት እና የህጻናት ጤና አገ/ት 11 ወራት አፈጻጸም፣ በዞን እና በክልል ደረጃ የተሰሩ የጨቅላ ህጻናት እና ህጻናት ሜንተር ሺፕ ሪፖርቶች ቀርበው ሰፊ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል። የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ

ጤናው የተጠበቀ ማህበረሰብ ለመፍጠር ሜዳ ላይ ከመጸዳዳት ነፃ ቀበሌያትን ማስፋት እንደሚገባ ተገለፀ። የምዕራብ አዘርነት በርበሬ ወረዳ የምዕራብ ሙጎ ቀበሌ የተሻሻለ መጸዳጃ ቤት መስፈርቶችን አሟልቶ ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነጻ ሆኖ ተመርቋል። "የተሻሻለ መጸዳጃ ቤት ሽፋን በማሳደግ ጽዱ ኢትዮጵያን እውን እናድርግ" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የፅዱ ኢትዮጵያ ፕሮግራም ተጠናክሮ ቀጥሏል ። ቀበሌው የግልና የጋራ መጸዳጃ ቤት በጥራት በመስራት እያንዳንዱ ቤተሰብ የራሱን ጤና ከመምራት ባለፈ ማህበራዊ ሃላፊነትን ወስዶ በተደራጀና ቀጣይነት ባለው መልኩ የአከባቢውን የጤና ሁኔታ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በትኩረት እየሰራ ይገኛል ። የምዕ/ሙጎ ቀበሌ በተለያዩ ተግባራት  ሞዴል መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በጽዱ ኢትዮጵያ ፕሮግራም ላይም እያደረገ ያለውን ተግባር አጠናክሮ በመቀጠል የፅዱ ኢትዮጵያን ምዕራፍ በማሻገር ዘላቂ የጤና መፍትሄ መፍጠር እንደሚገባም ተገልጿል ። ከለላ ያለው፣ ወለሉ መታጠብ የሚችል፣ ጣሪያው ዝናብ የማያስገባ፣ ግጣም(ክዳን) ያለው፣ ውሃና ሳሙና ያለው፣ ከ1 ሜትር ከፍታ በላይ ያለውና ሌሎችም የተሻሻለ መጸዳጃ ቤት መስፈርት መሆኑን በዕለቱ ተመላክቷል። በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የምዕራብ አዘርነት በርበሬ ወረዳ ዋና አፈ ጉባዔ ክብርት ወ/ሮ ለይላ ራመቶ ፣ የወረዳው ጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አ/ፈታ መሀመድ፣  የሴቶችና ህጻናት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሸቦ ሳይድ፣ ጤና ኤክስቴንሽኖች፣የጤና ጣቢያና ጤና ጽህፈት ቤት ባለሙያዎች እንዲሁም የጤና ልማት ሰራዊትና ሌሎችም ተገኝተዋል። ህብረተሰቡ ከተለያዩ ተላላፊ በሽታዎች ራሱን መጠበቅ የሚችለው የግልና የአከባቢ ንጽህና በመጠበቅ መሆኑን አውቆ የመጸዳጃ ቤትና ሌሎች መሰል ተግባራትን  በጥራት ማከናወን እንደሚገባ ተጠቁሟል ። በመጨረሻም ለዚህ ፕሮግራም መሳካት ጉልህ አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት እውቅና የተሰጠ ሲሆን ተግባሩ የአንድ ጊዜ ብቻ አለመሆኑን በመገንዘብ ስራዉ ከዚህ በተሻለ መልኩ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በምርቃ ፕሮግራሙ ማጠቃለያ  ላይ  ተገልፆዋል። ለስልጤ ዞን ጤና መምሪያ ዘገባ የማ/ኢት/ክ/መ/ጤ/ ቢሮ

የበሪዮ ቀበሌ ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ ሆኖ ተመረቀ። ሰኔ 29/2016፣ ወልቂጤ፣ የቀ/ል/ወ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የበሪዮ ቀበሌ 18ቱን የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅ ተግባራዊ በማድረጉ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። በስፍራው የተገኙት የቀቤና ልዩ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብድልማሊክ አብደላ እንደተናገሩት ህብረተሰቡ የግልና የአካባቢውን ንጽህና በመጠበቅ ከተላላፊ በሽታዎች ራሱን መጠበቅ እንዲሁም ለህክምና የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎችን በቀላሉ አካባቢን በማፅዳት አና የተሻሻለ መፀዳጃ ቤት ገንብቶ በመጠቀም መከላከል እንደሚቻል ተናግረው ቀበሌው ፅዱ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። የልዩ ወረዳው ጤና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አብድለሀይ ኑርሀሰን እንደተናገሩት በፅዱ መንደር ፕሮግራም የተመረጡ ቀበሌዎች 10 መሆናቸውን በማስታወስ የበሪዮ ቀበሌ ሲመረቅ ዘጠነኛው ነው ብለዋል። በተጨማሪም በቀበሌው የተጀመሩ የጤና ኤክስቴንሽን ስራዎችን ለማስቀጠል ትኩረት ሰጥቶ መስራት ይገባል ያሉ ሲሆን ቀበሌው ሜዳ ላይ ከመፀዳዳት ነፃ በመሆኑ እና ሞዴል ቀበሌ ሆኖ በመመረቁ ለቀበሌው ነዋሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። በመጨረሻም በቀበሌው የተሰሩ የግልና የአካባቢ መጸዳጃ ቤቶችን ተዟዙረው የተመለከቱ ሲሆን እየተሰሩ ያሉ ሰሰራዎች አበረታች በመሆናቸው ተጠናክረው እንዲቀጥሉና የአንድ ቀን ተግባር ሆነው እንዳይቀሩ ጥብቅ መልዕክት በማስተላፍ ቀበሌው ሞዴል እንዲሆን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና ሰርተፍኬት ተሰጥቷቸዋል። **** #ውጤታማ ተግባቦት ለሀገር አንድነት ❗️ ለቀ/ል/ወ/መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ዘገባ የማ/ኢት/ክ/መ/ጤና ቢሮ

"ኤግዚቢሽኑ ከዝቅተኛ የህክምና ግብዓት አምራችዎች ጀምሮ በዘርፉ ለተሰማሩ አምራችዎች የእርስ በርስ ግንኙነትን ለማጠናከር እና የሀገር ውስጥ ምርትን ለማሻሻል ጠቃሚ ነው!!" ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ____ የአገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ከሰኔ 15/2016 ዓ.ም ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ መካሄዱ እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ በኤግዚበሽኑ ጉብኝት ላይ ተገኝተው አጠቃላይ ስለ ኤግዚቢሽኑ መረጃ የሰጡት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንዳሉት በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በተዘጋጀው የአገር ውስጥ የህክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽንን በርካታ ጎብኚዎች እየተሳተፉበት እንደሆነ አንስተው በሁለቱ ቀናት ውስጥ ሃያ ስምንት ሺህ ጎብኚዎች ጎንኝተውታል ብለው በኤግዚቢሽኑ በርካታ የመረጃ ልውውጥና የዕውቀት ሽግግር እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ የህክምና ግብሃትንና መሳሪዎችን በሀገር ውስጥ በማምረት ሀገሪቱ ለመድሃኒትና ለህክምና ግብአት የምታወጣውን ወጪ በመቀነስ የጤናውን ዘርፍ የገንዘብ አቅም ማሻሻል እና የመድሃኒትና የህክምና ግብዓት አምራችዎችን የእርስ በርስ ግንኙነትን ለማጠናከር እና የሀገር ውስጥ ምርት አጠቃቀምን በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረው የህክምና ግብዓት አምራችዎችን ፣ተቆጣጣሪ አካላትን፣የጥናትና ምርምር ባለሙያዎችና ዩኒቪርስቲዎች ፣ህክምና ግብዓት ምርት ፈላጊዎችንና ወኪል ድርጅቶችን እንዲሁም ባለድርሻ አካላትን ለማገናኘት ጉልህ አስተዋጽ እንዳለውም ዶ/ር መቅደስ አብራርተዋል፡፡ ኤግዚቢሽኑን የጎበኙት የመንግስት ግዢ አገልግሎት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ክፍሌ ገ/ማሪያም በበኩላቸው በኤግዚበሽኑ ምንያህል የሀገር ውስጥ አምራችዎች እንዳሉና የምርት አይነቶችን እንደሚገኙ መመልከት እንደቻሉ ተናግረው ከዚህ በፊት ከሀገር ውስጥ ምርት 6ከመቶ ብቻ ግዢ ይፈጸም የነበረው በአሁን ሰዓት ወደ 36 ከመቶ ማደጉን ጠቁመው ወደፊት የጤናውን ዘርፍ የህክምና ግብዓት አቅርቦትን ማሻሻል ከተቻለ የሀገር ውስጥ ምርት ፍላጎትና አቅርቦትን ማሳደግ እንደሚቻል አክለዋል፡፡

የህብረተሰቡን የጤና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በእዉቀት ላይ የተመሠረተ ጥናትና ምርምር መስራት እንደሚገባ ተገለፀ። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት ዳይሮክተሬት ጥናትና ምርምር ስነ ምግባር ኮሚቴ /ቦርድ/ ወደ ስራ እንዲገቡ እገዛ የሚያደርግ ስልጠና ለሚመለከታቸው አካላት በወራቤ ዩኒቨረሲቲ ቅጥር ግቢ ዉስጥ እየተሰጠ ይገኛል ። የማ/ኢ/ክ/ የህ/ጤ/ኢንስትቱዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ለገሰ ጴጥሮስ የስልጠናዉን መድረክ ባስጀመሩበት ወቅት ላይ እንደገለፁት የህብረተሰቡን የጤና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በእዉቀት ላይ የተመሠረተ ጥናትና ምርምር ለመስራት እስከ ታችኛዉ መዋቅር ድረስ በመዉረድ በጋራ እና በልዩ ትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል። አቶ ለገሰ አክለዉም የጤና አገልግሎትን ጥራትን ለመጨመር በህብረተሰብ የጤና እክል ላይ ችግር ፈቺ የሆኑ ጥናት እና ምርምሮችን ማድረግ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ዙሪያ ከፍተኛ ልምድ ባላቸዉ ተመራማሪዎች ወቅቱን የጠበቀ ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስራዎችን በመስጠት በርካታ ለዉጦችን ማስመዝገብ ይቻላል ብለዋል። ዶክተር ሰራዊት ሀንዲሶ በትም/ሚኒሰቴር የጥናትና ምርምር የማህበረሰብ ትስስር ጉዳዮች ሀላፊ የስልጠናውን ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት ላይ እንደተናገሩት ጥራት ያለዉ ጥናትና ምርምር ለማድረግ በቂ እዉቀት ማምረት እና መፍጠር እንዳለብን ገልፀው በርካታ መረጃዎችን ለማደራጀት ሁላችንም የጋራ የሆነ እቅድ በማዘጋጀት በመተጋገዝ እና በመረዳዳት ተናበን መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። እንደ ዶ/ር ሰራዊት ገለፃ ጥናትና ምርምር ስናደርግ የዜጎችን የጤና ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ ባሻገር የህብረተሰቡን አንድነት ፣እኩልነት ፣ባህላቸዉን፣ማንነታቸውን እንዲሁም መብቶቻቸውን በማይነካ መልኩ መስራት እንደሚገባ አስረድተዋል። በስልጠናው ላይ የሀገር አቀፍ ጥናትና ምርምር ስነምግባር ገምጋሚ ኮሚቴ ቦርድ አባላትን ጨምሮ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ፣የክልሉ ፖሊሲና ጥናትና ምርምር ተቋም፣የዋቻሞ፣ የወልቂጤና ወራቤ ዩኒቨርስቲ ተወካዮች እንዲሁም የሆሳዕና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ የክልሉ ጤና ቢሮ የማኔጅመንት አባላት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ስልጠናው በነገው ዕለትም እንደሚቀጥል ተገልጿል ። የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ