Christ and Him Crucified
前往频道在 Telegram
As we navigate the journey of life together, let’s focus on pursuing truth, holiness, and godliness. Let's to gently confront sin, along with the influences of the world & the flesh. CORAM DEO.
显示更多3 104
订阅者
+224 小时
+127 天
+2930 天
帖子存档
የቻይና ሮቦት መስሎ በሰው ሰራሽ ዱቄት መፈካት የውበት መለኪያ ሁኖ ከመቆጠሩ በፊት፣ ትውልዱ በማንነቱ ሳይደናገጥ አስቀድማችሁ በትዳር የተጣመራችሁ ቅዱሳን በእውነት እድለኞች ናችሁ።
የዚህ ዘመን ሴቶች አመለካከት እጅግ ያስፈራል። ወንዱም ቢሆን ወንድነቱን ከዘነጋ ቆይቷል። ብቻ ምን አለፋችሁ... የእኛ ዘመን ይለያል። የሰው የማሰብ ችሎታ ከእጅ ስልኩና ከኢንተርኔት የሚያልፍ አይደለም።
ከዚህ ፍርኻት መውጣት እየከበደ ይመጣል... እንዲያውም ሁኖ ግን ጌታ ሰው አለው። ተስፋ አትቁረጡ 😊😀
Repost from Puritans pool
ስለ መጨረሻዉ ፍርድ ማስተማር ኃጥኣንን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት መቆም፣ሁሉን በሚያዉቅ፣ሁሉን በሚችል፣ሁሉን በሚያይ በሕያው እግዚአብሔር እጅ መዉደቅ እጅግ አስፈሪ መሆኑን ከማስተማር ባለፈ፤እግዚአብሔርን ለሚፈሩ የመጽናኛና የተስፋ መልእክት ነው። በክርስቶስ ጽድቅ የተሸፈኑ ስለሆኑ፣ የኀጢአተኞች ክፉ ሥራ ፍትሐዊ ፍርድን እንደሚቀበል፣ እነርሱም በእግዚአብሔር ፊት ለዘላለም የተባረኩ እንደሚሆኑ በማወቅ መጽናናትን ያገኛሉ። በዚህ በአሁኑ ሕይወትም መከራዎች መካከል፣ ከዓለም፣ ከሥጋ፣ ከዲያብሎስም የሚመጣባቸውን ተቃውሞ ሲታገሉ፣ በዚህ እውነት እውነተኛ መጽናኛና እረፍት ሊያገኙ ይችላሉ።
Sin and Hell are married unless Repentance proclaim the divorce!
- CHARLES H. SPURGEON
@Christisallsufficient
“ስለዚህ ይህን እነግራችኋለሁ፤ በጌታም ዐደራ እላለሁ፤ በአስተሳሰባቸው ከንቱነት እንደሚኖሩት እንደ አሕዛብ ልትመላለሱ አይገባም። እነርሱ ከልባቸው መደንደን የተነሣ ስለማያስተውሉ ልቡናቸው ጨልሟል፤ ከእግዚአብሔርም ሕይወት ተለይተዋል። ኅሊናቸው ስለ ደነዘዘ በማይረካ ምኞት፣ በርኩሰት ሁሉ እንዳሻቸው ለመኖር ቅጥ ለሌለው ብልግና ራሳቸውን አሳልፈው ሰጥተዋል።
እናንተ ግን ክርስቶስን ያወቃችሁት እንደዚህ ባለ መንገድ አይደለም፤ በርግጥ ስለ እርሱ ሰምታችኋል፤ በኢየሱስም እንዳለው እውነት በርሱ ተምራችኋል። ቀድሞ ስለ ነበራችሁበት ሕይወትም፣ በሚያታልል ምኞቱ የጐደፈውን አሮጌ ሰውነታችሁን አውልቃችሁ እንድትጥሉ ተምራችኋል፤ ደግሞም በአእምሯችሁ መንፈስ እንድትታደሱ፣ እውነተኛ በሆነው ጽድቅ እንዲሁም ቅድስና እግዚአብሔርን እንዲመስል የተፈጠረውን አዲሱን ሰው እንድትለብሱ ነው።
ስለዚህ ውሸትን አስወግዳችሁ፣ እያንዳንዳችሁ ከባልንጀራችሁ ጋራ እውነትን ተነጋገሩ፤ ሁላችንም የአንድ አካል ብልቶች ነንና። “ተቈጡ፤ ነገር ግን ኀጢአት አትሥሩ፤” በቍጣችሁ ላይ ፀሓይ አይግባ። ለዲያብሎስም ስፍራ አትስጡት። ይሰርቅ የነበረ ከእንግዲህ አይስረቅ፤ ነገር ግን ለተቸገሩት የሚያካፍለው ነገር እንዲኖረው በገዛ እጆቹ በጎ የሆነውን እየሠራ ለማግኘት ይድከም።
እንደ አስፈላጊነቱ ሌሎችን የሚያንጽና ሰሚዎችን የሚጠቅም ቃል እንጂ የማይረባ ቃል ከአፋችሁ አይውጣ። ለቤዛ ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔር መንፈስ አታሳዝኑ። መራርነትን ሁሉ፣ ቍጣና ንዴትን፣ ጭቅጭቅና ስድብን ከማንኛውም ክፋት ጋራ ከእናንተ ዘንድ አስወግዱ። እግዚአብሔር በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ፣ እናንተም ይቅር ተባባሉ፤ እርስ በርሳችሁ ቸሮችና ርኅሩኆች ሁኑ።”
ኤፌሶን 4:17-32 NASV
@Christisallsufficient
“ስለዚህ ይህን እነግራችኋለሁ፤ በጌታም ዐደራ እላለሁ፤ በአስተሳሰባቸው ከንቱነት እንደሚኖሩት እንደ አሕዛብ ልትመላለሱ አይገባም። እነርሱ ከልባቸው መደንደን የተነሣ ስለማያስተውሉ ልቡናቸው ጨልሟል፤ ከእግዚአብሔርም ሕይወት ተለይተዋል። ኅሊናቸው ስለ ደነዘዘ በማይረካ ምኞት፣ በርኩሰት ሁሉ እንዳሻቸው ለመኖር ቅጥ ለሌለው ብልግና ራሳቸውን አሳልፈው ሰጥተዋል።
እናንተ ግን ክርስቶስን ያወቃችሁት እንደዚህ ባለ መንገድ አይደለም፤ በርግጥ ስለ እርሱ ሰምታችኋል፤ በኢየሱስም እንዳለው እውነት በርሱ ተምራችኋል። ቀድሞ ስለ ነበራችሁበት ሕይወትም፣ በሚያታልል ምኞቱ የጐደፈውን አሮጌ ሰውነታችሁን አውልቃችሁ እንድትጥሉ ተምራችኋል፤ ደግሞም በአእምሯችሁ መንፈስ እንድትታደሱ፣ እውነተኛ በሆነው ጽድቅ እንዲሁም ቅድስና እግዚአብሔርን እንዲመስል የተፈጠረውን አዲሱን ሰው እንድትለብሱ ነው።
ስለዚህ ውሸትን አስወግዳችሁ፣ እያንዳንዳችሁ ከባልንጀራችሁ ጋራ እውነትን ተነጋገሩ፤ ሁላችንም የአንድ አካል ብልቶች ነንና። “ተቈጡ፤ ነገር ግን ኀጢአት አትሥሩ፤” በቍጣችሁ ላይ ፀሓይ አይግባ፤ ይሰርቅ የነበረ ከእንግዲህ አይስረቅ፤ ነገር ግን ለተቸገሩት የሚያካፍለው ነገር እንዲኖረው በገዛ እጆቹ በጎ የሆነውን እየሠራ ለማግኘት ይድከም።
እንደ አስፈላጊነቱ ሌሎችን የሚያንጽና ሰሚዎችን የሚጠቅም ቃል እንጂ የማይረባ ቃል ከአፋችሁ አይውጣ። ለቤዛ ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔር መንፈስ አታሳዝኑ። መራርነትን ሁሉ፣ ቍጣና ንዴትን፣ ጭቅጭቅና ስድብን ከማንኛውም ክፋት ጋራ ከእናንተ ዘንድ አስወግዱ። እግዚአብሔር በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ፣ እናንተም ይቅር ተባባሉ፤ እርስ በርሳችሁ ቸሮችና ርኅሩኆች ሁኑ።”
ኤፌሶን 4:17-26, 28-32 NASV
@Christisallsufficient
አገራችን አሁን ላለችበት ምስቅልቅል ሁለት መሠረታዊ ችግሮች አሉ። ሁለቱም የግብር መጠሪያ ስማቸው አንድ ነው፤ ብልጽግና። አንዱ ምድራዊ ሕይወትን አጁዛ ያደርጋል፣ ሌላኛው ደሞ ነፍስ ያጎሳቁላል።
መፍትሔውስ? ለመጀመሪያ ፊደል መቁጠርና ወንድና መኾን፣ ለሁለተኛው ደሞ ወደ ቀደምት እምነታችን መመለስ።
እነኾ አገራችን በሰማይ ነው! እነኾ እዚኽም ምድር ማረፊያ ለሰው ልጆችም ሰላምና ደህንነት ያስፈልጋል። የንጹሐን ሞት፣ የድኾች መፈናቀል፣ የፍትሕና የፍርድ መዛባት ዝም ልባል አይገባም!
“እኔ የእግዚአብሔርን ስም ዐውጃለሁ፤ የአምላካችንን ታላቅነት አወድሱ! [4] እርሱ ዐለት፣ ሥራውም ፍጹም ነው፤ መንገዱም ሁሉ ትክክል ነው፤ የማይሳሳት ታማኝ አምላክ፣ ቀጥተኛና ጻድቅ አምላክም እርሱ ነው።”
ዘዳግም 32:3-4 NASV
@Christisallsufficient
ሞኝነት ሆኖ አይደለም ፍቅሩን ቀምሼ ነው
ና ሲለኝ የተከተልኩት ነፍሴ ተማርካ ነው
ጠቢባን ያላዩት ዕውቀት ለኔ ተገልጦ ነው
የጌታን የማዳን ሚስጢር ነፍሴ ተረድታ ነው
ከወርቅ ከእንቁ በልጦብኝ ነው
ከማንም በላይ ተመችቶኝ ነው
የቱ ነው ታዲያ ሞኝነቴ
ለኔስ ጥበብ ነው ጌታን ማወቄ እሄሄሄእሄሄሄ
አምላኬን ማወቄ
- ዳንኤል አምደሚካኤል
የዘንድሮው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በብዙ አስደናቂ ክስተቶች የተሞላ ነው። ከተወዳዳሪነቱና ከደስታው ባሻገር ግን የእኔን ልብ የሳበውና እጅግ ያስደሰተኝ ክስተት፣ አንዳንድ ክርስቲያን ተጫዋቾች ከጨዋታ ፍጻሜ በኋላ የሚያደርጉት መንፈሳዊ ተግባር ነው።
የሜዳው ፉክክርና ፍልሚያ አብቅቶ፣ ከተለያዩ አገራት የመጡ ተጫዋቾች አንዱ ከሌላው ወገን ጋር አብሮ ተንበርክኮ ሲጸልይና አምላኩን ሲያመሰግን ማየት እጅግ ድንቅ ነው። ለእኔ እንደ ክርስቲያን እንዲህ ዓይነቱን ትዕይንት በዓለም አደባባይ ማየት ትልቅ ብርታትና ደስታን ይሰጣል።
ይህ ነጻነትና መነቃቃት በዘንድሮው ስታዲየም ጎልቶ እንዲታይ ካደረጉት ታሪካዊ ምክንያቶች አንዱ የውድድሩ አስተናጋጅ አገራት (በተለይም አሜሪካ) ያሉበት ምኅዳር እንደሆነ ይታመናል። አሜሪካ ምንም እንኳን በአሁኑ ወቅት የብዙ እምነቶችና ፍልስፍናዎች መናኸሪያ ብትሆንም፣ ታሪካዊ አመሠራረቷ ግን በክርስቲያን ፒልግሪሞች (Pilgrims) እና በክርስትና እሴቶች ላይ የተገነባ መሆኑ አይካድም።
ከዚህም ባለፈ፣ የምዕራቡ ዓለም ሥልጣኔና ዕድገት ከክርስትና እምነት ጋር በእጅጉ የተሳሰረ ነው። የሕግ የበላይነት፣ ሰብአዊ መብቶች እና የሞራል እሴቶች (Virtues) መነሻቸው ከመጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ ጋር ጥልቅ ቁርኝት አለው። ይህ በነጻነት የመጸለይና እምነትን በይፋ የመግለጽ ባህልም፣ በነዚሁ አገራት ውስጥ ባለው የሃይማኖት ነጻነት ሥር የሰደደ ሥርዓት ምክንያት ለተጫዋቾቹ ምቹ መድረክ ፈጥሮላቸዋል። ሆኖም ግን፣ ከዚህ ከምድራዊው የታሪክ አውድ በበለጠ፣ በሜዳው ላይ የታየው አንድነት መሠረቱ ሰማያዊ ነው።
ይህ በስፖርቱ መድረክ ያየነው ክስተት፣ በሥጋና በደም ከአገር፣ ከሕዝብና ከቋንቋ የተለያዩ ሰዎች በክርስቶስ ደም ሲዋጁና በአንድ መንፈስ ሲገናኙ የሚኖራቸውን ሰማያዊ ውበት በተግባር ያሳየን ነው። በሰዎች መካከል ያለውን የዘር፣ የቋንቋና የባህል ልዩነት (የጥል ግድግዳ) አፍርሶ ሰዎችን በአንድ ማዕድ የሚያስቀምጥ እውነተኛ ኃይል የክርስቶስ ደም ብቻ ነው።
ተጫዋቾቹ በሜዳው ላይ የየአገራቸውን ማሊያ ቢለብሱም፣ ከጨዋታው በኋላ ግን ለአንድ ንጉሥ ተንበርክከዋል። ይህ የሚያሳየው የክርስቶስ ደም ከየትኛውም ምድራዊ ድንበር፣ ብሔርና ቋንቋ በላይ ሰዎችን የማስተሳሰርና አንድ የማድረግ ፍጹም አቅም እንዳለው ነው። በዚህ በሕይወት አጋጣሚ (በዓለም ዋንጫ) የተገናኙት ቅዱሳን፣ የወደፊቱን የሰማያዊውን ቤት ክብር ጥቂት ፍንጭ አሳይተውናል።
በአጠቃላይ፣ የዘንድሮው ዓለም ዋንጫ የስፖርት ድግስ ብቻ ሳይሆን፣ የክርስቶስ ወንጌልና በደሙ የሆነው አንድነት በየትኛውም ሥፍራና የሕይወት ዘርፍ ሁሉ ደምቆ መውጣት እንደሚችል የታየበት ታሪካዊ አጋጣሚ ሆኖ ቀጥሏል።
ብቻ ግነ የአፍሪቃ ቡድን እየደገፋችሁ ከመቃጠል ተቆጠቡ። እኔ ከአንድም ሁለቴ ታምሜ ተስፋ ቆርጫለኹ 😁
@Christisallsufficient
"በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ፣ ከምስጋናም ጋራ ልመናችሁን በእግዚአብሔር ፊት አቅርቡ እንጂ ስለ ማንኛውም ነገር አትጨነቁ።"
ፊልጵስዩስ 4:6 (NASV)
@Christisallsufficient
እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ልቧ እንደ ንጋት ጤዛ የጠራ ነው፣ እንደ መቅደስ እጣንም ደግሞ መዓዛው እጅጉን ያማረ ነው።
እሷ በዝምታዋ ውስጥ ታላቅ ኃይልን፣ በትህትናዋ ውስጥ ደግሞ ሰማያዊ ክብርን የሰነቀች የእግዚአብሔር ድንቅ ስራ ናት። ሐሳቧም ከፍ ስል ስለ እግዚአብሔር፤ ዝቅ ስል ደግሞ ስለቤቷ ነው። ከነ ድካሟም ቢሆን ስለቤቷና ስለ ልጆቿ ዘወትር ከመጸለይ አትቦዝንም።
And she is my mom!
Repost from Pro-life Generation in Ethiopia 👼
#የምር_ግን_Normal_ነው_?
ሰይጣን Normal ያልሆኑ ነገሮችን Normal እንደሆኑ እንድናስብ ተግቶ የሚሰራ ይመስለኛል ። ትላንት ትላንት ስንሰማቸው በድንጋጤ አፋችንን የሚያሲዙን ነገሮች አሁን አሁን እንኳን ስንሰማ መደንገጥ ስናደርጋቸው ራሱ Normal ናቸው። ነገርየው ሲቆይ ሲቆይ Normal ሆኖ ሳይሆን ሳናስበውም ቢሆን Normal እንዲሆንብን ሆኗል ። በገዛ ስልካችን screen በኩል ተጠቅሞ Normal እንደሆነ አሳምኖናል።
በዚህ ዘመን ግን ክርስቲያን መሆናችን መለያው ምንድነው ? ምንድነው ከሌላው ማህበረሰብ እኛን የሚለየን የሃይማኖታችን ስም ? ወይስ የምንሄድበት ቤተ ክርስቲያን ? ወይስ አለባበሳችን ? ወይስ ንግግራችን ? ወይስ ተግባራችን ? ወይስ መዝሙራችን ? ምንድ ነው መለያችን ? በወሬያችን መሀል "በኢየሱስ ስም" ማለታችን ? ወይስ " ጌታን " ብለን መማለችን ? ምንድነው ልዩነታችን ? #በክርስቶስ_ደም_የተዋጁ_የሰማያዊው_መንግስት_ልጆች_መሆናችን_ምድር_ላይ_በምንድነው_የሚገለጸው ? 🤔 ለኛ Normel ነገር ምንድነው ? ምንድነው Normal ያልሆነውስ ?
😭 " ...ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን... "
@prolifeGenerations
ይህ ከደቡብ ይመስለኛል... ድንበር ዘለል ቋንቋ እናገራለሁ እያለ ነው። ሳስበው የሞኙ ጩፋ ወይም የከሰረ ዳንሳ ልጅ ነው 😀
