ch
Feedback
Construction Proxy

Construction Proxy

前往频道在 Telegram

#1 construction portal to get: ✅ construction news ✅ construction market ✅construction materials price ✅engineering estimates ✅ Sub contract https://constructionproxy.com Address any comment to admin👨‍💼 @ConproxyBot

显示更多

📈 Telegram 频道 Construction Proxy 的分析概览

频道 Construction Proxy (@constructionproxy) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 19 509 名订阅者,在 商业 类别中位列第 3 466,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 727

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 19 509 名订阅者。

根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 1,过去 24 小时变化为 0,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 31.99%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 6 243 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 30

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
#1 construction portal to get: ✅ construction news ✅ construction market ✅construction materials price ✅engineering estimates ✅ Sub contract https://constructionproxy.com Address any comment to admin👨‍💼 @ConproxyBot

凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 商业 类别中的关键影响点。

19 509
订阅者
无数据24 小时
-17
+130
帖子存档
Anyone who have dump trucks for rent in Addis Ababa call 0911761658 telegram @teniba ገልባጭ ያለው ለአዲስአባ ውስጥ ማከራየት የሚፈልግ 0911761658 ይደውሉ telegram @teniba

Anyone who have dump trucks for rent in Addis Ababa call 0911761658 telegram @teniba ገልባጭ ያለው ለአዲስአባ ውስጥ ማከራየት የሚፈልግ 0911761658 ይደውሉ telegram @teniba

photo content

photo content

ከ6.1 ቢሊዮንብር በላይ በሆነ ወጪ 299 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡ •1 የፕሮጀክቱ ስም፦ ኅሙሲት -እስቴ የመንገዱ ርዝመት ፦ 76.6 ኪ.ሜትር • የመንገዱ ደርጃ፡- አስፋልት ኮንክሪት • ጨርታዉን ያሸንፈዉ ተቋራጭ ፦ Ningxia communication construction Co. Ltd. • የማማከርና የቁጥጥር ስራ የሚሰራው፦ ኬቲም እና አላሚ አማካሪ መሐንዲሶች ከኮር አማካሪ መሐንዲሶች የግል ኃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ጋር በመተባበር • የግንባታ ወጪ፦1,395,881,640.48( • የግንባታዉን ወጪ የሚሽፈነዉ አካል፦ የአረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት BADEA/OFID & GOV በመተባበር የሚሸፈን ይሆናል። • ግንባታውን አከናውኖ ለመጨረስ የተሰጠው ጊዜ፦ የሶስት ዓመት •2 የፕሮጀክቱ ስም፦ጩላሴ - ሶያማ (ሎት፦2) • የመንገዱ ርዝመት ፦79.5 ኪ.ሜትር • የመንገዱ ደርጃ፡- አስፋልት ኮንክሪት • ጨርታዉን ያሸንፈዉ ፦ቻይና ሪል ዌይ 14 የተባለ የቻይና የስራ ተቋራጭ • የግንባታ ወጪ፦1,800,000,000.00 • የግንባታዉን ወጪ የሚሽፈነዉ አካል፦በኢትዮጵያ መንግስት ግንባታውን አከናውኖ ለመጨረስ የተሰጠው ጊዜ፦ ሶስት ዓመት •3 የፕሮጀክቱ ስም፦ የአደሌ- ግራዋ • የመንገዱ ርዝመት ፦ 55 ኪ.ሜትር • የመንገዱ ደርጃ፡- አስፋልት ኮንክሪት • ጨርታዉን ያሸንፈዉ ፦ሂቤ የስራ ተቋራጭ • የግንባታ ወጪ፡- 1,436,300,000.00 • የግንባታዉን ወጪ የሚሽፈነዉ አካል፦ በኢትዮጵያ መንግስት • ግንባታውን አከናውኖ ለመጨረስ የተሰጠው ጊዜ፦ የሶስት ዓመት •4 የፕሮጀክቱ ስም፦ጎዴ - ቀላፎ (ሎት፦1) • የመንገዱ ርዝመት ፦ 88.5 ኪ.ሜትር • የመንገዱ ደርጃ፡- አስፋልት ኮንክሪት • ጨርታዉን ያሸንፈዉ ተቋራጭ፦ ቻይና ሪልዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ • የማማከርና ቁጥጥር ስራውን፦ ስታዲያ የመሃንዲሶች አማካሪ ድርጅት ነው። • የግንባታ ወጪ፦1,530,000,000 ( አንድ ቢሊየን አምስት መቶ ሰላሳ ሚሊየን ) • የግንባታዉን ወጪ የሚሽፈነዉ አካል፦ በኢትዮጵያ መንግስት • ግንባታውን አከናውኖ ለመጨረስ የተሰጠው ጊዜ፦ ሶስት ዓመት ከግማሽ

Do not do bet, but if you do make it scientifically. https://t.me/betsprofessor

የኮንሰልታንት ወርሀዊ ደመወዝ በሀገራችን በየአመቱ የተለያዩ መንገዶች ግንባታቸው ተጠናቆ በመመረቅ ላይ ናቸው፨ ታዲያ እነዚህ መንገዶች በጥራት እንዲሰሩ ትልቁን አስተዋፅኦ እያበረከቱ የሚገኙት በሱፐርቪዥን የተመደቡ የኮንሰልቲንግ ሰራተኞች ናቸው፨ የዛሬ አስር አመት ለአንድ መንገድ የሚመደበው ከፍተኛው በጀት 600 ሚልዮን ብር አካባቢ የነበረ ሲሆን በአሁን ሰአት 1.7 ቢልዮን ደርሱዋል፨ ነገር ግን በመንገድ ቁጥጥሩ ከፍተኛውን ድርሻ የሚወጡት የኮንሰልቲንግ ሰራተኞች ከ 10 አመት በፊት የአንድ ሱፐርቫይዘር ደሞዝ 3,100 ብር የነበረው በአሁን ሰአት 3,800 ብር ነው፨ ሌላው የቀጣሪያቸው ዋና መስሪያ ቤት ለአንድ ሰው የሚጫረቱበት ደሞዝ የዛሬ 10 አመት ከነበረው አሁን በ 100 ፐርሰንት አድጉዋል፨ አብዛኛውን የጥራት ሀላፊነት ወስዶ የሚሰራው ሱፐርቫይዘር በ 10 አመት ውስጥ የ 800 ብር ለውጥ ብቻ አግኝትዋል፨

Deadline December 13, 2019
Deadline December 13, 2019

ተክለ ብርሃን አምባዬ በ73 ሚሊዮን ብር ግብር ስወራ ተከሰሰ! . የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ተክለ ብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽንን ጨምሮ አምስት ከፍተኛ ተቋራጮችን በግብር ስወራ በፌዴራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በስምንተኛ እና ዐስረኛ ወንጀል ችሎቶች ክስ መሰረተ። በኢትዮጵያ ካሉ የደረጃ አንድ ተቋራጮች መካከል እንዲሁም ከፍተኛ አቅም ካላቸው መካከል የሆነው ተክለ ብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽን፣ ከ 2005 እስከ 2008 ባለው ጊዜ መክፈል የነበረበት እና ከተለያዩ ፕሮጀክቶች የተገኘ 70.3 ሚሊዮን ብር የትርፍ ግብር ባለመክፈሉ ክሱ ተመሥርቷል። የንግድ ግብሩ ግዢ ባልተፈፀመባቸው ሐሰተኛ ደረሰኞች በመጠቀም የተሰወረ እንደሆነ እና ደረሰኞቹንም የቆረጡት ድርጅቶች በአካል የሌሉ መሆናቸውን ጠቅሶ ነው ዐቃቤ ሕግ ክሱን የመሠረተው። ከተለያዩ ፕሮጀክቶች ከ 25 ሚሊዮን እስከ አንድ ሚሊዮን ብር የሚደርስ ገቢን ድርጅቱ ሰውሯልም ሲል ዐቃቤ ሕግ ክሱን አሰምቷል። በተጨማሪም ከተለያዩ አገልግሎቶች የተሰበሰበ ሦስት ሚሊዮን ብር የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ በተመሳሳይ ከ 2005 እስከ 2008 ባለው ዓመት ለመንግሥት ሳይከፍሉ ቀርተዋል ሲልም ነው ዐቃቤ ሕግ ክሱን በስምንተኛ የጉምሩክ ችሎት የመሠረተው። በተመሳሳይ ቻይና ቁጥር ሦስት ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ከ 2007 እስከ 2010 ባሉት ዓመታት ካገኘው 375.3 ሚሊዮን ብር ውስጥ 256 ሚሊዮን ብር ባለማሳወቅ የተሳሳተ መረጃ ለገቢዎች ሚኒስቴር በማሳወቅ ክስ ተመሥርቶባቸዋል። በተመሳሳይ በስምተኛ የጉምሩክ ችሎት የተመሠረተው ይኸው ክስ፣ ሐሰተኛ ሰነዶችን በመጠቀም የድርጅቱን መረጃ በመደበቅ በመንግሥት ላይ ጉዳት አድርሰዋል ሲል በተሻሻለው የገቢዎች አዋጅ መሠረት ዐቃቤ ሕግ ክሱን አሰምቷል። ድርጅቱ ከተጨማሪ እሴት ታክስ የሰበሰበውን 3.6 ሚሊዮን ብር ላይ አንድ ነጥብ ዘጠኙን በመቀነስ በተመሳሳይ ለመንግሥት ገቢ መሆን የነበረበትን ገቢ አስቀርተዋል በሚል ተከሷል። ቻይና ፈርስት ሃይ ዌይ ከ2006 እስከ 2008 ድረስ ባለው የግብር ዓመት ከውጪ ምንዛሬ የተገኘ 32 ሚሊዮን ብር ሐሰተኛ መግለጫ በማቅረብ ሰውረዋል ያለው ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ፣ ያለ ደረሰኝ በመገበያየት እና ሽያጫቸውን በመሰወር ወንጀል ፈፅመዋል ሲል በክሱ ላይ አስፍሯል። እንዲሁም በተመሳሳይ የግብር ዓመት ካገኘው 91 ሚሊዮን ብር ውስጥ 45 ሚሊዮን ብሩን በመሰወር ግብሩን አላሳወቀም ተብሏል። ከተጨማሪ እሴት ታክስ የተሰበሰበ ኹለት ሚሊዮን ብር ሳይከፍል ቀርቷል በሚል ነው ክስ የተመሰረተበት። በአጠቃላይም 81.2 ሚሊዮን ብር ለመንግሥት መከፈል የነበረበትን ግብር በመሰወር ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ክሱን መሥርቷል። ፓወር ኮን የተሰኘው ሌላው ድርጅት 34 ሚሊዮን ብር ግዢ ሳይፈፅም እንደፈፀመ አድርጎ በማቀረቡ ክስ ልመሠርትበት ችያለሁ ሲል ዐቃቤ ሕግ ለመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የጉምሩክ ችሎት አቤቱታውን አሰምቷል። 59 ሕገ ወጥ ደረሰኞች ከ 12 ድርጅቶች በመጠቀሙ ሆነ ተብሎ በተሰወረ ገቢ መንግሥት ላይ ጉዳት ደርሷል ሲል በክሱ አስረድቷል። ፍርድ ቤቱም ተከሳሾች በፍርድ ቤት ቀርበው ክሱ ተነብቦላቸው ወደ ፍርድ ሂደት እንዲቀርቡ በሚል መጥሪያ የላከ ሲሆን፣ በተደጋጋሚ ጥሪ ተደርጎለት ያልቀረበው ቻይና ፈርስት ሃይዌይ ኮንስትራክሽን ኅዳር 29 በፖሊስ ተይዞ እንዲቀርብ የሚል ትዕዛዝ አስተላልፏል። እንዲሁም ቻይና ሬልዌይ ቁጥር ሦስት ኢንጂነሪግ ታኅሳስ አንድ በተላከለት መጥሪያ መሰረት እንዲቀርብ መጥሪያ ፍርድ ቤቱ መስጠቱንም አዲስ ማለዳ ያገኘቸው መረጃ ያስረዳል። ለተክለ ብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽንም መጥሪያ ከፍርድ ቤቱ የተላከ ሲሆን፣ ለታኅሳስ 13 ተከሳሽ እንዲቀርቡ ታዝዟል። ከአንድ ዓመት በላይ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ ፌዴራል ፖሊስ እና ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ከ 33 በላይ ደረጃ አንድ ተቋራጮች በተለይም የምርመራ ኦዲት ሪፖርትን መሰረት ያደረገ የምርመራ ሥራ ሲያከናውኑ እንደነበር ሲገለጽ ቆይቷል። ከእነዚህ ተቋራጮች በወቅቱ ከኹለት ቢሊዮን ብር በላይ ተሰውሮብኛል ሲል የነበረው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ፣ አብዛኛውን ገንዘብ መሰብሰቡን ቆይቶ አሳውቆም ነበር። ነገር ግን ፖሊስ የግብር እዳቸውን መክፈላቸው ከፍትኀ ብሔር እዳ እንጂ የወንጀል ምርመራ ከማካሔድ ጋር አይገናኝም በሚል ከጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጋር ወራት የፈጀ ምርመራ ሲያካሒዱ ቆይተው፤ ስድስት ድርጅቶች ላይ ክስ መሥርተዋል። የገቢዎች ሚኒስቴር አዲሱ የበጀት ዓመት ከገባ ጀምሮ ባሉት ተከታታይ አራት ወራት ውስጥ 90 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን እንዳስታወቀ ይታወሳል። (Addis Maleda)

OFFICE ENGINEER Mikada Engineering and Trading PLC OFFICE ENGINEER 10 VIEWS Address: Bole Medanialem behind Moneco yard Date Posted November 24, 2019 Deadline Date December 6, 2019 Job Requirement M.Sc/B.Sc Degree in Civil or related Engineering fields GENERAL EXPERIENCE: 6 years SPECIFIC EXPERIENCE ON :road 2 years PLACE OF WORK:HO A.A Renewed professional license:Required How to Apply Interested applicants may submit their CV supported with relevant testimonials and renewed professional licenses to our office located at Bole Medanialem behind Moneco yard Or you may email in mikadajobs@gmail.com within 10 working days after the advertisement. For further information, call on Tel 0116500643

CONSTRUCTION ENGINEER Yotek Construction Plc Job Requirements - B.Sc degree in civil engineering or related fields with six years of general experience in road projects out of these three years of specific experience as a construction engineer. place of work:- project ✍️ How to Apply Interested applicants should apply via the following address: Yotek construction plc, in front of African union Email: yotekconplc@gmail.com For more information: call on 0115573196/0115573198 Make sure that to send us both the original and copy of your CV, Transcript, and experience ✂️Deadline: Dec 03 2019

Construction Proxy - Telegram 频道 @constructionproxy 的统计与分析