Never give up
前往频道在 Telegram
显示更多
未指定国家未指定类别
472
订阅者
+124 小时
+97 天
+830 天
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+16
在1个频道中
八月 '26
+181
在2个频道中
Get PRO
七月 '26
+371
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 11 九月 | +1 | |||
| 10 九月 | +1 | |||
| 09 九月 | +2 | |||
| 08 九月 | +1 | |||
| 07 九月 | +2 | |||
| 06 九月 | +4 | |||
| 05 九月 | +4 | |||
| 04 九月 | +1 | |||
| 03 九月 | 0 | |||
| 02 九月 | 0 | |||
| 01 九月 | 0 |
频道帖子
🌼 እሰይ አዲስ አመት 🌼
በባለፈው ዘመን ብዙ ተገላተናል
የተረገመ አመት ብለን አመረናል
አዳዴም አማሮን አዳዴም አስቆን
በመልካም እረክተን በክፉ ተጨቀን
አሳለፍነው መቼም ስት መከራ አይተን
🌼 እንኳን አደረሳቹ 🌼
አዲስ አመት መጣ ከአሮጌው እርቆ
ብሩ ተስፋ ይዞ በአደይ አበባ አምሮ
አሸብርቆ
በእንስቶች ግጥም አበባዮሽ ጨዋታ
ቀኑ ተበሰረ አበባው ተስሎ ሲመጣ ስቶታ
ዘመድ ተሰብስቦ ጎረቤት ባድነት
መአዱን ተቋርሰን በፍቅር ባብሮነት
አመት አመት ደርሶ ለከርሞ አይለየን
እዲው እዳማረብን ደግሞ ይሰባስበን
አሜን በሉ እንመራረቅ🙏🙏
ፀብ ግርግሩ የማይሰማበት
በዘር በሀይማኖት የማንባላበት
እርስ በእርሳችን ምንዋደድበት
ሀገራችን ደምቃ የምትታይበት
ፍቅራችን ጨምሮ የምንኖርበት
እዳይሆን አዲሱ የማንከፋበት
በፍቅር ባብሮነት በእድገት ጎዳና ምንሻገርበት
ያድርግልን እሱ ቸር በጎ በጎ ከእጁ ማያልቅበት
🌼አሜን 🌼አሜን🌼አሜን🌼
መልካም አዲስ አመት⚡️⚡️🌼🌼
| 2 | .............😇ህልሟ😇.............
ከደስታ በር ቆሜ
ወደእኔ መጣች ፤ ሳታልፈኝ አስቆምኳት
ጠየኳት
ምን ትፈልጊያለሽ ፤ ህልምሽን ንገሪኝ?
ትንሽ አመንትታ
መኪና ቤት አለች ፤ የቀደመን አይታ
ከዛም አለፈችኝ
ስትሄድ ሸኘኋት ፤ ዞራም አላየችኝ።
ከደስታ በር ቆሜ
ወደእኔ መጣች ፤ ሳታልፈኝ አስቆምኳት
ጠየኳት
ምን ትፈልጊያለሽ ፤ ህልምሽን ንገሪኝ
ትንሽ አመንትታ
ትዳር ከዛም ልጆች .... የቀደመን አይታ
ከዛም አለፈችኝ
ስትሄድ ሸኘኋት ፤ ዞራም አላየችኝ
ከደስታ በር ቆሜ
ወደእኔ መጣች
ደክማለች
መሮጡ ታክቷታል
ያፍላነት እሳቷ ፤ በጊዜ ተረቷል
ሳታልፈኝ አስቆምኳት
ጠየኳት
ምን ትፈልጊያለሽ
ህልምሽን ንገሪኝ?
ዝም አለችኝ ላፍታ ፤ አየችኝ በአንኩሮ
ከሳሁ ጠቆርኩ ፤ ልበን ደርሻለሁ ፤ የለሁም ዘንድሮ
የነፍሷ ጥሪ ፤ የመንፈሷ ለቅሶ ... ነበርኩ
ስጋዋ የከዳኝ ፤ በስሜት የታሰርኩ
አነባች ለአፍታ
በሀዘኗ እውነት ፤ እውር አይኗ በራ
ይሉኝታም ተረታ
ለአፍታ ህይወቷ ፤ ትላንት ለኖረችው
ሞተ ገደለችው
አነባች አዘነች ፤ ከዛም ቀበረችው።
ዳግም ተወለደች
እኔን ያዘችና ፤ አይኖቿን ጨፈነች።
በህይወት ሸራዋ ፤ እጇ ላይ ታች አለ
ልቧም ደም አነባ ፤ አለም ተነከረ
ማንም አላያትም
ዳኝነት ይሉኝታም ፤ ተኝተው ነበረ
ጊዜዋም ሲያበቃ
አይኗን ገልጣ ፤ ፈገግ አለች
መጨረሻም ህልሟን ሳለች
እሱም ውብ ነበር! | 1 851 |
| 3 | እስቲ ላፍቅር ደሞ…
ሰው አጥር ወጥቼ - ፅጌረዳ ልቅጠፍ፥
አበባዬን ይዤ - እግሯ ሥር ልነጠፍ፤
ጨረቃ ላይ ላፍጥጥ - ከዋክብትን ልቁጠር፥
የቦይ ውኃ ልምታ - በለቀምኩት ጠጠር፤
በመስኮት ላማትር - በሚወርደው ዝናብ፥
ቀን ተሌት ልተክዝ - በፈጠርኩት ምናብ።…
እስቲ ደሞ ላፍቅር…
እሷው ፖለቲካ - እሷው ሰበር ዜና፥
እሷው ባለንዋይ - እሷው ባለዝና፥
እሷው የ’ምነቴ ቄስ - እሷው ቅድስና፥
ዓለም በቃኝ ብዬ - በሷው ወሬ ልጽና።
ከፈገገች ልሣቅ - ካለቀሰች ልሙት፥
እኔ አለኹ ለቀልዷ - ደደቦች ባይሰሙት።…
እስቲ ላፍቅር ደሞ…
መንገድ ስሟን ልጥራ - አበደ ይበሉ፥
እሷ ውስጥ እንዳለኹ - የማያውቁ ኹሉ፤
ጥዑም ዜማ ይኹን - የምትጨቀጭቀኝ፥
የሰለቸኝ ኹሉ - ባ’ንድ አዳር ይናፍቀኝ፤
እንዴትም ትስደበኝ - ስሜን ታጥፋው አኹን፥
ብቻ ስሜን ትጥራ - ብቻ ካፏ ይኹን።…
እስቲ ላፍቅር ደሞ…
ዘፈን ትርጉም ይስጠኝ - ደሞ ላንጎራጉር፥
ስለመቃ አንገት - ስለሀር ጸጉር፤
ላንዲት እንስት ልውደቅ - ሎሌነቴን ልግመድ፥
የያዝኩትን ልጣል - ዐዲስ ጌታ ልልመድ።
እስቲ ላፍቅር ደሞ! | 2 017 |
| 4 | .
ዛሬም እዛው ቁማ - ትጠብቀዋለች
ይመጣል አይቀርም - በር በሩን ታያለች
ሁልጊዜ እየመጣ - ሁልጊዜ እያየችው
ከቀን ቀን ሲገፋ - በጣም ወደደችው
አናግሯት አያቅም - ድምፁን አታቀውም
ተሳስቶ እንኳ ላንዴ - አፉን አይከፍተውም
ሳያያት አይውልም - እሱም ግን ወዷታል
ሚገዛው ባይኖርም - ዝም ብሎ ይገዛታል
አንድ ጊዜ ሳሙና - አንዳንድ ጊዜ ኦሞ
ጠቁሞ ይገዛታል - ከበሩ ዳር ቆሞ
በጣም ሰልችቷቷል - እሱን መጠበቁ
በቅጡ አላወሩ - ወይ አልተዋወቁ
ልፈትነው ብላ - እሱ እንደሚወዳት
ከሌላ ጋር አይቶ - ቀንቶ እንዲያናግራት
ከወንድ ጋር ሆና - ሱቋ ጠበቀችው
ወደሷ ሲጠጋ ፊቱ ሲለዋወጥ...
...ከሩቅ ላይ አየችው
ከሌላ ጋር ሲያያት - በጣሙን ተከፋ
ከዛ ቀን በኋላ - ሳታገኘው ጠፋ
ከሳምንት በኋላ - ስለሱ ጠየቀች
ያ ልጅኮ ጠፋ - የት ሄዶ ነው አለች
አልሰማሽም እንዴ - ያ ልጅኮ ሞቷል
በሲባጎ ገመድ - ራሱን አጥፍቷል
የሚወዳትን ልጅ - ከሌላ ጋር አይቶ
ሞቱን አፋጠነ - ራሱን አጥፍቶ
ስትል የነበረ - ለምን አይነግረኝም
ድምፅ አውጥቶ ባፉ - ወደድኩሽ አይለኝም
እውነቱን ስታውቀው - ስሜቷ ተነካ
ያ የምትወደው ልጅ - 'ዱዳ' ነበር ለካ
| 3 066 |
| 5 | ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
(((ይህ ነው ላንቺ ፍቅር)))
ውዴ.....
እኔ ፍቅር ያልኩት
በአንቺ አጠራር ደግሞ....
ለፍቅር የማይቀርብ
መልመድ የተባልኩት...
....................
እኔ አፈቀርኩሽ ስል
ለካ ይሄ ፍቅር...
መፋቀር አይደለም...
ላፈቀሩት መኖር
መታደል ባይሆንም....
................
እንዲያውም እንዲያውም
ስም ስጪልኝ ስልሽ
ግንኙነታችን....
ይህ ፍቅር አይደለም
መላመድ ብቻ ነው...
የነበሩን ግዜ
እነዚያ ወረቶች
ለካ ውሸት ናቸው
ተላመድን እንጂ
መቼ ተፋቀርን
ብለሽ ባልሽባቸው
እነዚያ አፎችሽ....
እንዴትስ ሌላ ወንድ
ወደድኩህ ትያለሽ....
ባቀፋኝ እጆችሽ
ሌላውን ታቅፊያለሽ....
በሳሙኝ ከንፈሮች
ልትስሚባቸው....
የለመዱት ገላ
ሊቀየርባቸው...
በውሸት ~ በሀሰት
ደግመሽ ሌላ ክህደት
ልትፈፅሚባቸው...
ባዘጋጀሻቸው
እነዚያ ልቦችሽ.....
ሌላ ትለምጃለሽ....
በወደድሽው መጠን
ትላመጂዋለሽ....
ተላምደሽ.....
ተላምደሽ....
........
ጊዜያት ሲበሩ...
ከሱ የተሻለ
ያማረ ሲመጣ...
ደግሞ ሊቀየሩ
በሌላ ብልጭልጭ
ጨርቃጨርቅ ሊተኩ.....
....................
ካዲያ ይህ ነው ፍቅር፤
ይሄ ነው ንፁህ ልብ፤
ግራ በቸጋባ ባደፈ ማንነት፤
በተቆራረጠ በቆሻሻ እውነት፤
በዛ ውስጥ መኖር....
.
.
.
ይህ ነው ላንቺ ፍቅር??
| 2 715 |
| 6 | ሆያ ሆዬ 👌👌👌.mp3 | 2 061 |
| 7 | ለላይኛው ሰማይ፣ ለመኖሪያ አድራሻህ
ፀሎት እንልካለን፣ መልሱን ግን እንዳሻህ
ብቻ እንድንፅናና…
ተመላላሽ ሞገድ መሃላችን አፅና
‘ለምን?’ ማለት ጥሩ…
ሺ ምልጃዎቻችን በዚያው ከሚቀሩ
መቼስ በዓለም ዙሪያ…
ወይ ስራ በዝቶበት
ወይ ሲጨፍር አድሮ፣ አናቱ ዙሮበት
ሳይፀልይ ያደረ ይኖራል አንድ ሰው
ጠይቀንህ የለ? መልሱን ለሱ አድርሰው!
እኛም እንላለን…
‘ፀሎቴ መች ቀረ?
ሞገድ ወስዶ ወስዶ አቅጣጫ አስቶታል
‘ቢሆንልኝ’ ያልኩት፣ ዘመዴ ደርሶታል።
አሜን! | 2 467 |
| 8 | ⊶⊷⊶⊷❍ የእብደት ሚስጥሬ ❍⊶⊷⊶⊷
ፍቅሬን በቃላቶች ~ ደርድሬ ባልገልፀው
የኔ ነሽ የምልሽ ~ ያንቺ ነኝ የምለው
ድምፅሽ መዳኒቴ ~ የህይወት እጣዬ
አካልሽ ጉልበቴ ~ የስኬት ማማዬ
ሌላ ማንም የለም ~ ባንቺ ነው ማማሬ
እውነት እልሻለሁ ~ የእብደት ሚስጥሬ
| 3 739 |
| 9 | ናፍቆት
.
.
እንዲህ እንደዛሬ...
በመሀከላችን
ንፋስ ሳይግባብን ፣ ፍጥረት ሳይፈጠር
በኔና አንቺ መሀል...
የነበረው ክፍተት ፣ አንድ ስንዝር ነበር።
አንቺ ሰማይ ሆነሽ እኔ ደግሞ ምድር!!!
............................................
በዚህ ስንዝር መሀል....
እስትንፋስ ያላቸው ሰዎች ተፈጠሩ
እነዚህ ሰዎችም....
ቅርብ ላለች ሰማይ
የምድርን ሀጥያት ይነግሯት ጀመሩ።
"ምድር ዘማዊ ነው
ምድር ሀጣዊ ነው
ብትሸሺው ይሻላል ይህ ዓለም ጠፊ ነው"
እያሉ ሲነግሯት የሰው ወሬ ሰምታ
ሰማይ ፊኛ ሆና...
ትለጠጥ ጀመረ ከኔ ተለይትል
በሰዎች እስትንፋስ...
ወደ ላይ ተነፍታ
ወደጎንም ሰፍታ።
.......................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
................................................
እንደውም እንደውም...
በዛ ስንዝር መሀል ያኔ የተፈጠሩ
እዛሬ ላይ ሆነው..
"ሰማይ ቅርብ ነበር" እያሉ ሚያወሩ
እድሜ የሰጣቸው
ጥቂት ሰዎች አሉ
የኔና ያንቺ ፍቅር የሚመሰክሩ።
.............................................
እንደውም እንደውም....
ሌላ አይነት ማስረጃ ሌላ አይነት ምስክር
ሰማይ ቅርብ ሳለሽ ምጣድ ሆኜ ምድር
እንዲህ እንደዛሬው...
ነፋስ አቀጣጥሎት
ነፋስ የሚያጠፋው እሳት ሳይፈጠር
የሰው ልጆች ሁሉ
በፀሐይ በርሀን ምግብ ያበስሉ ነበር።
.............................................
ፀሐይ ውበትሽ ነው ጠዋት የምሞቀው
ቀን ተቃጥዬበት ሌት የምናፍቀው።
ለሊት ላይ ያመኛል ህመሜም አንቺው ነሽ
ቀኑ ጨለማ ነው...
ነግቶ እስካይሽ ድረስ ትናፍቂኛለሽ።
...........................................
መቼ ነው ሚነጋው?
ፀሐዩ ውበትሽ ምድርን የሚከድነው
መርዙ መድሀኒትሽ...
በሽታዬን ገድሎ ህመሜን ሚያድነው
ካፈቀሩት ጋራ....
እንኳን ላንድ ለሊት
ላፍታ ያህል እንኳን መለያየት ሞት ነው።
.............................................
መቼ ነው ሚነጋው ልቤን ይበርደኛል
ንጋት ላይ የሚሸሽ..
ወረተኛ ፍቅር ጤዛው በዝቶብኛል
አንቺ የሌለሽበት...
ራሴን ሳስበው ራሴን ያዞረኛል።
ለራስ ምታት ህመም..
መድሀኒት እንዲሆን
በሽታን የሚገድል መርዝ ነው ሚቀመም።
...................................
እንጂማ አውቃለሁ እንጂማ ታውቂያለሽ
የሰው ወሬ ሰምቶ ልብሽ ባይረበሽ
እንዲህ እንደዛሬ.
ሳትርቂኝ በፊት ሰማይ ቅርብ ነበርሽ።
........................
እየሔዱ መጠበቅ | 4 178 |
| 10 | 🚺✅ምርጥ አስተማሪ ታሪክ! ካልጨረሳችሁት አትጀምሩት
#እናቱን የሚወድ ሁሉ ሊያነበው የሚገባ ፅሁፍ መልካም ንባብ !
ከባለቤቴ ጋር ትዳር ከመሰረትን 21 ዓመት ሞላን ባለቤቴ አንድ እራሴን እንድፈትሽበት ያደረገኝን ጥያቄ አቀረበችልኝ ሃያ አንድ ዓመት ካንተ ጋር ስኖር አንድም ቀን ከእናትህ ጋር ለመዝናናት ስትወጣ አይቼክ አላውቅም ዛሬ ማታ እናትህን እራት ምሽት ጋብዛትና አዝናናት አለችኝ።
ውዷ ባለቤቴ ባቀረበችልኝ ሃሳብ ከመገረም በላይ መሰጠኝ ተስማማሁኝ እናም ወደ እናቴ ጋር ደወልኩላት እማ ዛሬ ካንቺ ጋር ሽርሽር መውጣት ፈልጋለሁ አልኳት ደነገጠች "ምነው ሰላም አይደል ልጆችሕ ምን ሆኑ ባለቤትህስ ሰላም አይደለች እንዴ ?" በማለት የድንጋጤ ጥያቄዎቿን አርከፈከፈችብኝ።
አብሽሪ እማ ሁሉም ሰላም ነው ካንቺ ጋር ለመዝናናት ፈልጌ ነው"አልኳት በጣም ደስ አላት ተስማማች ወደማታ ተዘጋጅተሽ ጠብቂኝ አልኳት በቀጠሮዬ ሰዓት ወደ እናቴ ጋር ሄድኩኝ እናቴ በረንዳው ላይ ቆማ እየጠበቀችኝ ነበር እናቴ ሁለመናዋ ተቀያይሯል እርጅና ተጫችጭኗታል ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ወደ መኪናዬ አስገብቺያት ጉዞ ጀመርን።
እናቴ በጣም ደስታ ይነበብባታል "ልጄ ዛሬ ካንተ ጋር ሽርሽር እንደምወጣ ለሰፈር ሰዎች ሁሉ እንዲሁም ለዘመድ አዝማዶቼ በሙሉ ተናግርያለሁኝ" በጣም ከመደሰቷ የተነሳ አንድም የምታውቀው አልቀራትም ወሬውን ለሁሉም አዳርሳዋለች ወደ ሆቴል ይዥያት ሄድኩኝ አስተናጋጁ የምግብ ዝርዝር ወረቀት የያዘ ኩፖን ሰጠን "እማ ምረጪ" አልኳት ፈገግ አለች ከእርጅና የተነሳ ማየት እንደማትችል ተረዳሁ ላንብብልሽ አልኳት "ልጅ እያለህ ሆቴል ቤት ገብተን ልንመገብ ስንል የምግብ ዝርዝር አነብልህ ነበር አሁን እዳህን ክፈል" ብላ ፈገግ አለች እኔም ፈገግ ብዬ አነበብኩላት።
የለበሰችውን ልብስ ስመለከት ከአስራ ዘጠኝ ዓመት በፊት የሞተው አባቴ የገዛላት የመጨረሻ ልብሷ እንደነበር አስታወስኩ ምግቡ ቀርቦ እናቴ ከደስታ የተነሳ ምንም እየበላች አልነበርም ደስታ በደስታ ሆናለች
በሕይወቴ እኔም በጣም የተደሰትኩበት አጋጣሚ ነበር ከእናቴ ጋር ተዝናንተን ስናበቃ ይህ ምሽት እንዲደገም ፈልጌ "እማ መቼ ተመልሼ ልምጣና ልውሰድሽ..?" አልኳት በእንደዚ ቀን ና ነገር ግን እኔ ነኝ የምጋብዝህ ከተስማማህ ና " አለቺኝ ፈገግ አልኩኝ ትጋብዥኛለሽ አልኳትና ተለያየን።
በመሃል እናቴ ታመመች ከህመሟ ድናልኝ አብርያት የማሳልፍበትን
ምሽት ናፈቀኝ ነገር ግን ከእናቴ ጋር ዳግም አልወጣንም እናቴ ወደ
ማይቀረው የሞት ጉዞ ተጓዘች በጣም አዘንኩ አለቀስኩ ከእናቴ ጋር ቀጠሮ ይዘን ወደነበረው ምሽት ከአንድ ታዋቂ ሆቴል ቤት ተደወለልኝ ዛሬ እራት ከባለቤትህ ጋር በነፃ ተጋብዛቹሃል።
ግራ ተጋባው ማነው እንዴት ለማንኛውም እሺ እንመጣለን ብዬ ስልኩን ዘግቼ ምሽት ላይ ከባለቤቴ ጋር ሄድኩኝ ግብዣው ከደብዳቤው ጋር ቀረበልን ደብዳቤውን ከፈትኩት እንዲህ ይላል :-"ልጄ ሰላም ላንተ ይሁን የእራቱን ግብዣ ስንቀጣጠር መገኘት እንደማልችል አውቅ ነበር
የሞት ቀጠሮዬ እየተቃረበ እንደነበር ነፍሴ ይነግረኝ ነበር ልጄ ይኸው እኔ በቃሌ መሰረት ጋብዥሃለው በኔ ፋንታ ውዷባለቤትህ አብራህ እንድትሆን ፈቅጃለሁ!" ይላል ሳይታወቀኝ እንባዬ ወረደ አለቀስኩ 21 ዓመት ሙሉ የዘነጋሁትን ውድ ዕቃ አሁን ነው ማጣቴን ያወኩት...!
ስንቶቻችን ይሆን ካገባን በኋላ እናቶቻችንን ወላጆቻችንን የምናስታውሰው ? ...ስንቶቻችን ነን ለራሳችን ስንሯሯጥ ወላጆቻችንን የረሳነው..? ቤት ይቁጠረን...!! | 3 846 |
| 11 | """"ንገሯት ለእናቴ""""
ልጄ ልጄ ስትል ስሜን ስታዎሳ፣
ልሂድ አይኗን ልየው.....
ልጠይቃት ብላ እግሯን ስታነሳ፣
እዳትመጪ በሏት ብትላችሁ እሽ፣
ልጅሽን ለማዬት እግርሽን አታንሽ፣
በቁሟ ሙታለች ብትችይ አታስታውሻት፣
ከነመፈጠሯ ከመኖሯም እርሻት፣
በሏት.....
አደራ ንገሯት አጥብቃችሁ ሞቴን፣
ብትናፍቀኝም.....
ላያታ አልፈልግም እንዲህ ሆኜ እናቴን፣
ወይም እዲህ በሏት ብላለች አትምጪ፣
ልጅሽ ክዳሻለች በቃ እርምሽን አውጪ፣
ወልደሽ አሳድገሽ ልጦርሽ ሲገባ፣
እናቷን ከሀዲ ሆነች የማትረባ፣
በሉልኝ ብታምን፣
አልባሷ ቡትቶ ስራዋ ምናምን፣
ይቅርና ለናቷ ያልሆነች ለነብሷ፣
እርኩስ.... የረከሰች.....
ለሁሉ ከፍ የሚል ወለቂ ቀሚሷ፣
እንኳንስ ሊኖሯት ልጆችና ትዳር፣
ቤት የላት መጠጊያ አዳሯ መንገድ ዳር፣
ንገሯት ለናቴ ኑሮዬን ትረዳ፣
አትሆንም ለዘመድ አጠቅምም ለባዳ፣
ድሮ የምታቂው በልጅነት አለም፣
ያ የሚያምረው መልኳ ገፅታዋ የለም፣
በውስጥሽ ያለውን የልጅነት ምስሏን፣
አጥፊ ተያት እርሻት አታስታውሻት እሷን፣
በሏት......
አይ.... አይ.... አትበሏት.....
ይቅር አትንገሯት እውነታውን ለእማ፣
የሚጨክን አንጀት ይህን እየሰማ፣
ጆሮ ዳባ የሚል አካል ስለሌላት፣
በቃ እደውም ተዋት፣
እሽ አትልም ትምጣ፣
ልቀበላት እና አይታኝ እርሟን ታውጣ። | 3 648 |
| 12 | ተላለፍን
አይቼው አይቶኛል
አይቶኝ ተያይተናል
ልቤ በእጥፍ መቷል
ልቡም በእጥፍ መቷል
ልቡ በደረቴ ምቱ ተሠምቶኛል
ቅፅበታዊ እይታ ጀምረን መገርመም
ዞር አልኩኝ ዞር አለ በቃ አልተያየንም
ልባችን መዳፉ ጣቱ ተቆላልፎ
እግራችን በሜዳ በሩቅ ተሠልፎ
መሥመር ለይቶናል አልተገናኘንም
ኑሮ ደልድሎናል አልተተዋወቅንም
ውስጥን በሚገዛ የአብሮነት ጥላ
መተዋወቅ ጠፍቶን የአድነት ከለላ
እየተፋለግን በልብ መሻሻት
አልተገናኝተንም ባሠመርነው ህይወት
የህይወት መንገድ ነው ድንገት ያገናኘን
ይኸው መንገድ ነበር ይባስ የለያየን
ለየቅል መንገድ ነው ጉዞ የጀመርነው
በራሣችን አለም የተለያየነው
በጭራሽ አንገጥምም አብረን እንኳ ብንሄድ
የርሱ እየዘገየ የኔ ልቤ ሲነጉድ
እኔ እሱን ስጠብቅ እሱ ሲሆድ ቀድሞኝ
በመጣበቅ ምኞት መጠባበቅ ሳንችል
እልፍ የጋራ መንገድ ኖሮን የምንዘልቀው
የጣምራ አለም ኑሮ በምኞት ሊቀር ነው
በዚያ ሠልፍ መሀል ....
ዞር አልኩኝ ዞር አለ አመንኩ እንዳላየኝ
በልቤ አዝዬው ሰልፌን ተከተልኩኝ
እሱም ተከተለ ሄደ ተሳፈረ ሄድኩኝ ተሳፈርኩኝ
አልተገናኝቶም ነን
በቃ ተላለፍን
| 4 106 |
| 13 | 🌞day#
በቀዝቃዛ ሌሊት - ውድህን አቅፈሃል
በኮከብ ታጅበህ - ከንፈሯን ስመሃል
ጨረቃዋን አይተህ - አለም ነው ብለሃል
ፀሐይ ወጣች ቀረች ምን ያደርግልሃል ?
በገባዖን ሰማይ - እምነቱን ተጠቅሞ - ፀሐይዋን አስቁሞ
ተዋግቷል ኢያሱ ፤
እስኪ ተሻል ከ'ሱ !
ጭር ባለው ሌሊት
ከምትወዳት ልጅ ጋር በስልት ደንሱ ።
ሰማይና ምድር ለዛሬ ባይነጉም
ዘላለም ነውና የአንዲት ቅፅበት ትርጉም
ይቺን ጨረቃ አስቁም ። | 4 805 |
| 14 | ❦ ══•⊰❂ ከታሪክ ማህደር ❂⊱•══ ❦
አይጧ
አይጧ የግድግዳውን ቀዳዳ በመጠቀም የቤቱ ባለቤት በታሸገ ካርቶን እቃ ይዞ ሲገባ ትመለከታለች፡፡ አይጧ “ዛሬ ደግሞ ምን አይነት ምግብ ይዞ መጣ!?” ብላ ተደስታለች፤ ነገር ግን ሰውዬው ለባለቤቱ ሊያሳያት የታሸገውን ካርቶን ሲከፍተው ወጥመድ ነው፡፡
አይጧ ደነገጠች፤ ወዲያውኑ ወደ እርሻው ተመለሰችና ጮክ ብላ “በዚህ እርሻ ውስጥ የምትገኙ እንስሳቶች ሆይ! የአይጥ ወጥመድ እየተጠመደላችሁ ነው፤ ወጥመድ! መጥመድ!!” በማለት ትናዘዛለች፡፡
ይህን ድምፅ በንቃት የሰማችው ☞"ዶሮ"፦
"ካጎነበሰችበት ቀና በማለት “አይጦ" ላንቺ ምን ያህል እንደሚያስጨንቅሽ ይገባኛል፤ ነገር ግን እኔን አይመለከትም እዛው ጣጣሽን ቻይ” ትላታለች፡፡
"አይጥ" "በግ" ወደ ሚገኝበት ቦታ ትሄድና የቤቱ ባለቤት ወጥመድ ገዝቶ እንደመጣ ትነግረዋለች፡፡ በጉ በንቀት አይን እየተመለከታት “ይቅርታ አድርጊልኝ አይጦ ምንም ልረዳሽ አልችልም” ይላታል፡፡
እቤት ውስጥ ከሚኖሩት እንስሳቶች የቀረው አንድ "በሬ"
ነበር፤ "አይጦ" እርሱንም እርዳታ ለመጠየቅ ወዳለበት
ትሄዳለች፡፡ “ወጥመድ ወጥመድ የአይጥ ወጥመድ ይዘው
መጡ” ትለዋለች፤ በሬው ምንም ሳይመስለው እየሳቀ
“አይጦ ምን ነክቶሽ ነው! እኔ እንደሆን ቆዳዬን እንኳ
አይጎዳውም፤ ጣጣሽን ቻይ” በማለት ያባርራታል፡፡
አይጧ በጣም ተበሳጭታ አንገቷን አቀርቅራ የገበሬውን
ወጥመድ ብቻዋን ልትጋፈጥ ወደ ቤቷ ትመለሳለች፡፡
በዚያው ቀን ምሽት ሰው ሁሉ በተኛበት ወጥመዱ ከፍተኛ
ድምፅ አሰማ፡፡ የገበሬው "ሚስት" አስቸጋሪዋ "አይጥ"
ተያዘች በማለት ወጥመዱን ጎተታ ይዛው እንዳትሄድ አስባ ወደስፍራው ታቀናለች፡፡ የአይጧ ጭራ መስሏት በወጥመዱ የተያዘውን አደገኛ "እባብ" አፉን ነበር የያዘችው፡፡ እባቡ ነደፋት፡፡ ገበሬው በፍጥነት ወደ ሆስፒታል ይወስዳታል፤ ከታከመች በኋላ ወደ ቤት ትመለሳለች። ጎረቤቱ ሁሉ እየመጣ ይጠይቃት ጀመር በዚህ መሀል "የዶሮ" መረቅ መደሃኒት ነው ይታረድላት ይባላል። "ዶሮዋም" ታረደች።
በቶሎ እንድታገግም "በግ" ይታረድላት ሲባል ከቀናት በኋላ "በግ" ታረደ። ይህ ሁሉ እየተደረገላትም ህመሟ እየበረታ ሄደ፡፡ በመጨረሻም ሴትዬዋ ሞተች። ለለቀስተኛው "በሬው" ታርዶ ተበላ።
አይጧ ይህንን ሁሉ ድርጊት በዚያች የግድግዳ ቀዳዳ ትመለከት ነበር፡፡ በድርጊቱ በጣም አዘነች፡፡
አለመደማመጥ ለችግራች የጋራ መፍትሄ አለመፈለግ፣ በተናጠል ችግሩ ራሱ ያጠፋናል። | 5 854 |
| 15 | ❦ ══•⊰❂ ከታሪክ ማህደር ❂⊱•══ ❦
አይጧ
አይጧ የግድግዳውን ቀዳዳ በመጠቀም የቤቱ ባለቤት በታሸገ ካርቶን እቃ ይዞ ሲገባ ትመለከታለች፡፡ አይጧ “ዛሬ ደግሞ ምን አይነት ምግብ ይዞ መጣ!?” ብላ ተደስታለች፤ ነገር ግን ሰውዬው ለባለቤቱ ሊያሳያት የታሸገውን ካርቶን ሲከፍተው ወጥመድ ነው፡፡
አይጧ ደነገጠች፤ ወዲያውኑ ወደ እርሻው ተመለሰችና ጮክ ብላ “በዚህ እርሻ ውስጥ የምትገኙ እንስሳቶች ሆይ! የአይጥ ወጥመድ እየተጠመደላችሁ ነው፤ ወጥመድ! መጥመድ!!” በማለት ትናዘዛለች፡፡
ይህን ድምፅ በንቃት የሰማችው ☞"ዶሮ"፦
"ካጎነበሰችበት ቀና በማለት “አይጦ" ላንቺ ምን ያህል እንደሚያስጨንቅሽ ይገባኛል፤ ነገር ግን እኔን አይመለከትም እዛው ጣጣሽን ቻይ” ትላታለች፡፡
"አይጥ" "በግ" ወደ ሚገኝበት ቦታ ትሄድና የቤቱ ባለቤት ወጥመድ ገዝቶ እንደመጣ ትነግረዋለች፡፡ በጉ በንቀት አይን እየተመለከታት “ይቅርታ አድርጊልኝ አይጦ ምንም ልረዳሽ አልችልም” ይላታል፡፡
እቤት ውስጥ ከሚኖሩት እንስሳቶች የቀረው አንድ "በሬ"
ነበር፤ "አይጦ" እርሱንም እርዳታ ለመጠየቅ ወዳለበት
ትሄዳለች፡፡ “ወጥመድ ወጥመድ የአይጥ ወጥመድ ይዘው
መጡ” ትለዋለች፤ በሬው ምንም ሳይመስለው እየሳቀ
“አይጦ ምን ነክቶሽ ነው! እኔ እንደሆን ቆዳዬን እንኳ
አይጎዳውም፤ ጣጣሽን ቻይ” በማለት ያባርራታል፡፡
አይጧ በጣም ተበሳጭታ አንገቷን አቀርቅራ የገበሬውን
ወጥመድ ብቻዋን ልትጋፈጥ ወደ ቤቷ ትመለሳለች፡፡
በዚያው ቀን ምሽት ሰው ሁሉ በተኛበት ወጥመዱ ከፍተኛ
ድምፅ አሰማ፡፡ የገበሬው "ሚስት" አስቸጋሪዋ "አይጥ"
ተያዘች በማለት ወጥመዱን ጎተታ ይዛው እንዳትሄድ አስባ ወደስፍራው ታቀናለች፡፡ የአይጧ ጭራ መስሏት በወጥመዱ የተያዘውን አደገኛ "እባብ" አፉን ነበር የያዘችው፡፡ እባቡ ነደፋት፡፡ ገበሬው በፍጥነት ወደ ሆስፒታል ይወስዳታል፤ ከታከመች በኋላ ወደ ቤት ትመለሳለች። ጎረቤቱ ሁሉ እየመጣ ይጠይቃት ጀመር በዚህ መሀል "የዶሮ" መረቅ መደሃኒት ነው ይታረድላት ይባላል። "ዶሮዋም" ታረደች።
በቶሎ እንድታገግም "በግ" ይታረድላት ሲባል ከቀናት በኋላ "በግ" ታረደ። ይህ ሁሉ እየተደረገላትም ህመሟ እየበረታ ሄደ፡፡ በመጨረሻም ሴትዬዋ ሞተች። ለለቀስተኛው "በሬው" ታርዶ ተበላ።
አይጧ ይህንን ሁሉ ድርጊት በዚያች የግድግዳ ቀዳዳ ትመለከት ነበር፡፡ በድርጊቱ በጣም አዘነች፡፡
አለመደማመጥ ለችግራች የጋራ መፍትሄ አለመፈለግ፣ በተናጠል ችግሩ ራሱ ያጠፋናል | 1 |
| 16 | ናፈቀኝ
""""""""
ወደሰማዩ ሳይ በደመና ምስል፣
ባይኔ ተከሰተ እርሱን የሚመስል፣
ጉብታውን ስቃኝ ተራራ ዳገቱ፣
ተመሳሰለብኝ ከኮራ ደረቱ፣
ንፋስ የሚገፋው ያየሩ መአዛ፣
እርሱን አስታወሰኝ ናፍቆት እየገዛ፣
እያንዳንዱ ነገር ያሳለፍነው ጌዜ፣
ገደለኝ ትዝታው ሆነብኝ ትካዜ፣
ጩኬ የሰደብኩት ያኔ ሲያበሳጨኝ፣
ትውስ አለኝና ባርባር አለኝ ቆጨኝ፣
መጣብኝ ጫዎታው መጣብኝ ሞገሱ፣
ናፈ'ከኝ ብል እንኳን አይሰማኝም እሱ፣
ናፍቆኛል ጨንቆኛል ግን ባይመለስስ፣
ዝም ልበልና ጎርፍ ዕንባዬን ላፍስስ። | 6 907 |
| 17 | ያንተ ሞርጫ
እጇ አለንጋ
ቁመተ ሎጋ
አመለ ሸጋ።
አንተ ፋንጋ
ያንተ ምኞት
ተረከዘ ሎሚ
ሂል ተጫሚ
ፀጉረ ዞማ
አይነ ቡናማ
የቀይ ዳማ
ጉንጨ ሮማን
ቅርፇ ያማን
ያንተ ኪንኪ
ቁመተ ኮርኪ
ጥፍረ መጥምጥ
ቦርጭህ ዝርጥጥ
አፋንጫህ ድፍጥጥ
ለምን ብሎ ይከፋሀል
እኔ አንተን በመዉደዴ
የድስት ግጣሜ ማለት አንተ አይደለሀኝ እንዴ?🤔 | 7 957 |
| 18 | ❦ ══•⊰❂ ፍቅሬን በግጥM ❂⊱•══ ❦
ያንተ ሞርጫ
እጇ አለንጋ
ቁመተ ሎጋ
አመለ ሸጋ።
አንተ ፋንጋ
ያንተ ምኞት
ተረከዘ ሎሚ
ሂል ተጫሚ
ፀጉረ ዞማ
አይነ ቡናማ
የቀይ ዳማ
ጉንጨ ሮማን
ቅርፇ ያማን
ያንተ ኪንኪ
ቁመተ ኮርኪ
ጥፍረ መጥምጥ
ቦርጭህ ዝርጥጥ
አፋንጫህ ድፍጥጥ
ለምን ብሎ ይከፋሀል
እኔ አንተን በመዉደዴ
የድስት ግጣሜ ማለት አንተ አይደለሀኝ እንዴ?🤔 | 1 |
| 19 | .... በርግጥ በኔ ዘመን .....
እምነት እንደ ጉሊት ሲቸበቸብ ያድራል
ቃል አክባሪ ግትር ተብሎ ይወቀሳል::
እዎ በኔ ዘመን......................
ፍቅር ከጭን ዳሌ ውሉን ያሳሰረ
የገበያው ዘዴ ሳይለዩ መግዛትን ብሂል የሰበረ::
በፍቅር ቅኝት ስም ሴሰኝነት ነግሶ
የነፍስ ፍቃዷ ተድሶ
በየ ጥጋ ጥጉ አስክሮ ሚያዳራ
ሺህ ጭኖችን ታቅፎ ሺህ ነፍስ የሚያሳጣ
የዘመናት ዋጋ.......
ወጣትነት ልኩ.........
መዝናናት ታቅፎ ውስጡ እዥ ያዘለ
በፈረሰ ደስታ ጠማማ ምሰሶ ታቅፎ የዋለ::
የእድሜ ጣሪያ ልስን
በእኔ ከሞትኩ ሰርዶ
በሺ አይኖር ወርዶ
በውሽት ቅብ ውበት ከላይ የተዋበ
አራዳ የሚያስብል አንዳንድ ስግጥና እለ:: | 9 169 |
| 20 | አዲስ ነገር የለም
""""""""""""""""""""""
ከሰማዩ በታች የለም አዲስ ነገር፣
ጊዜ የገዛትን ታሪካዊት ምድር ጠይቋት ትናገር፣
ካንዱጋር ዳንኪራ ከሌላጋር ሀዘን፣
አንዱ ሲረጋጋ አንደኛው መባዘን፣
መጪ ስንቀበል ሌላው ተሰናባች፣
ተወለደ ሲባል እዛጋ ደሞ ሟች፣
የለም አዲስ ነገር ሆኖ እንጂ ለየቅል፣
ጊዜ ንጉስ ሆኖ አውርዶ ሲሰቅል፣
እኛም ሆነንለት ተጎናባሽ አሽከር፣
እንከተላለን ....
በመሬት ዙሪያላይ ይዞን ሲሽከረከር፤
በዚች በቆምኩባት ባለሁበት ምድር፣
የወለደ ሲሞት ያሳደገ ሲድር፣
ጥንዶች ሲጫዎቱ የፍቅር ጫዎታ፣
ያረገዘች ስትወልድ ያገባ ሲፈታ፣
አማኝ የገዳም ሰው ወይም በግልባጭ፣
ጠንባዛ ሰካራም አንቡላ አንጫላጭ፣
መፍትሄ ጠፍቶበት ኑሮ ያቀወሰው፣
አይቻለሁ ባይኔ ....
ጨርቁን ጥሎ ሲያብድ ጤነኛ ያልኩት ሰው፤
አዲስ ነገር የለም
ስጠይቅ እራሴን ....
ለምን እንደሆነ አንዱ አለፈ ሲባል ሌላው የሚተካ፣
ሲገባኝ እውነቱ ....
ክብ አለም መዞር ነው ሂዎት ማለት ለካ። | 10 288 |
