የቀጠናው ተመልካች
前往频道在 Telegram
በአለማችን ቀጠናዎች የሚከሰቱ ክስተቶችን ይዘግባል፣ ሳይቀዘቅዝ በትኩሱ። ለጥያቄና ለአስተያየቶች በኢሜል asuleyma246@Gmail.com ብላችሁ ፃፉልኝ።
显示更多未指定国家未指定类别
4 312
订阅者
-124 小时
-167 天
-8330 天
帖子存档
4 312
🇺🇸⚡️🇮🇷ትራምፕ፡ ኢራን ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካን ለመገናኘት ቀጠሮ ይያዝልኝ ብላ በጠየቀችው መሠረት፣ ነገ በኳታር ዶሃ ችግሮቿን ለመስማት እንገናኛለን።
ኢራን፡ አልጠየቅም፣ ውሸቱን ነው፣ ግን እንገናኛለን።
4 312
🇷🇺 ሩሲያ የኪየቭን የተኩስ አቁም ሐሳብ ውድቅ አደረገች።
ቭላድሚር ፑቲን፣ የኪየቭን መንግሥትን ማዳን የሩስያ እቅድ አካል እንዳልሆነ ገልፆ፣ ኪየቭ ያቀረበችውን የተኩስ አቁም ሐሳብ አጣጥሎታል።
የአሜሪካ ልዑካን አባላት፣ የኢራን ጉዳይ 'ረገብ ሲል'፣ ወደ ሞስኮ በቅርቡ ይመጣሉ ብለን እናምናለን፣ ሲልም ተናግሯል።
*-*-*-
ፑቲን የዩክሬንን ሐሳብ ውድቅ ያደረገበት ምክኒያት፣ እንደሚመስለኝ፣ ሐሳቡ የለበጣ መሆኑን እና ሲሪየስ ያልሆነ ፕሮፖዛል እንደሆነ በማወቁ ነው።
ዩክሬን ሩሲያን እያሳተቻት ያለችው፣ አንዴ እርቅ፣ ሌላ ጊዜ ጦርነት፣ አንዴ ተኩስ ማቆም፣ ሌላ ጊዜ ድርድር እያለች የሩሲያን ልብ ለሁለት በመክፈል እና ቆርጦላቸው ሙሉ ትኩረታቸውን መዋጋት ላይ እንዳያደርጉ በማድረግ ነው።
ተሳክቶላታል። ፑቲንም አውቋታል፣ እኛም እያየነው ነው። ዩክሬን ካሁን በኋላ ጦርነት ማቆም አትፈልግም። የዛሬ ሁለትና ሦስት ዓመት፣ አዎ። ዛሬ ግን ሌላ ቀን ነው ለዩክሬን። ውጊያው ተለውጧል።
ዩክሬን፣ የበላይነቱ ንፋስ ወደ እሷ እንዳዘነበለ፣ ሩሲያን ለምዕራባዊያን መያዝና ማንበርከክ፣ ታላቅ ታሪክ መፃፍ ሕልምን እያየች እንደሆነ ስለተረዳች፣ አሜሪካ መጥታ አቁሚ ብትላትም ካሁን በኋላ የምታቆም አይመስለኝም።
ጥያቄው፣ ፑቲን ይሄን ሁሉ ካወቀ፣ ምነው ሙሉ ጦርነት ለማወጅ እና ኃይሉን ለመጠቀም ሽባ ሆነ? ለምን ኪየቭን አይመታም? ለምን ዘለንስኪንና መንግሥቱን ዒላማ አያደርግም? ሕግ ማውጫውን፣ ማዘዣ ጣቢያውን፣ ማመላለሻ ባቡሩን፣ ወደቦቹን ለምን አይመታም? እንዲህ እንዳያደርግ የያዘው ምንድነው? ምን አስቧል? የሚቀርብለትን የውሸት 'እያሸነፍን ነው' ን ሪፖርት ምናልባት በየዋህነት አምኖ ነው? ወይስ አላማው ሩሲያን ማፍረስ ነው?
ከባድ ነው፣ በቅርበት ሁኔታውን ለሚከታተል ሰው።
4 312
🇺🇦🇷🇺⚡️ - የዩክሬን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ፡
ፑቲን ጦርነቱን እንዲያቆም ለማስገደድ እና በአጥቂው የክሬምሊን ስብስብ ላይ ተጽእኖ ለማሳደር በማለም፣ የዩክሬ የደህንነት ተቋማት በሩሲያ የሚያደርጉትን የ40 ቀናት ዘመቻ አጽድቄያለሁ። በሚቀጥሉት 40 ቀናት ውስጥ፣ ክሬምሊንን የሚያሳምም እና የሩሲያንን ሕዝብ የጦርነቱን ሕመም እንዲሰማው የሚያደርግን፣ ሰላም ከማውረድ ውጭም ሌላ ምንም ምርጫ እንደሌላቸው በማሳመን ላይ ለማስገደድ፣ በዩክሬን የደህንነት ኃይሎች ጥቃቶች ይደረጋሉ።
4 312
🇺🇦🇷🇺⚡️ - የዩክሬን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ፡
ፑቲን ጦርነቱን እንዲያቆም ለማስገደድ እና በአጥቂው የክሬምሊን ስብስብ ላይ ተጽእኖ ለማሳደር በማለም፣ የዩክሬን የደህንነት ተቋማትን የ40 ቀናት ዘመቻን አጽድቄያለሁ። በሚቀጥሉት 40 ቀናት ውስጥ፣ የሩሲያ መንግሥትን የሚያሳምም እና ሰላም ከማውረድ ውጭ ሌላ ምንም ምርጫ እንደሌላቸው በማሳመን ላይ ለማስገደድ፣ ጥቃቶችን አፅድቄአለሁ።
4 312
🇪🇹⚡️በመቶዎች የሚቆጠሩ የገዢው ፓርቲ፣ ብልፅግና፣ ሰራዊት አባላት፣ በዐማራ ክልል የሚንቀሳቀሰው ፋኖ፣ በጎጃም ክፍለ ሀገር ውስጥ፣ በሰነዘረው መጠነ-ሰፊ ጥቃት የተነሳ፣ እንደተማረኩ የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የገዢው ፖርቲ ሰራዊት አባላት፣ ሳይገደሉና ሳይቆስሉ እንዳልቀረም ተነግሯል።
4 312
🇮🇷 ⚡️🇺🇸🇮🇱 ኢራን በውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ በሰይድ አባስ አራግቺ በኩል፣ ለቀጠናው ሀገሮች ማስጠንቀቂያ ልካለች፡
አየራችሁን እና መሬታችሁን ለጠብ አጫሪዎች እና ለደም አፍሳሾች አትፍቀዱ። እምቢ ካላችሁ፣ ለሚመጣባችሁ ኢራን ተጠያቂ አትሆንም።
4 312
🇷🇺⚡️የፑቲን ሩሲያ ዛሬም በዩክሬን ድሮኖች በመንደድ ላይ ናት።
የዩክሬን ድሮኖች፣ የሩሲያን የአየር ክልል ሰባብረው እየገቡ የሚያደርሱት ጥቃት፣ የተለመደ እየሆነ መጥቷል።
የሚፈራው ያ የሩሲያ ሰማይ፣ ዛሬ የለም። ዛሬ በመቶዎች የሚቆጠሩ ድሮኖች፣ በየቀኑ፣ የፈለጉት ክፍለ ሀገር ሄደው፣ ተሽከርክረው፣ መምታት ጀምረዋል።
በአንድ ምሽት፣ የስንት ዘመናት ሥራ እና እውቀት የፈሰሰባቸውን፣ የኃይልና የወታደራዊ ኢንተርፕራይዘሮችን ነው፣ ዩክሬኖች አንድደው እየወጡ ያሉት።
ፑቲን ጦርነቱን መሃል ሩሲያ አምጥቶታል።
4 312
🇷🇺⚡️ፑቲን፡
ከአሁን በኋላ ናፍጣ ወደ ውጭ መላክ ለማቆም እየተነጋገርን እንገኛለን። በነዳጅ እና በዘይት ምርቶች ላይም ራሽን እና በውስን መጠን ለማከፋፈል በሚቻልበትም መንገድ ላይ እየሰራን ነው። ይህን የምናደርገው፣ 'በሽብርተኞች' ጥቃት የተነሳ የተፈጠረብንን እጥረት ለማቃለል እና ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚሆን በቂ ዘይት እንዲኖር ለማስቻል ነው። ባሁኑ ሰዓት፣ በየ ጋዝ ማደያው የሚገኘው ነዳጅ፣ ጥራቱን ያልጠበቀ እንደሆነ እየሰማሁ ነው፣ ምሬቶች እየበረከቱ እንደሆነ አያለሁ። የሩሲያ ሕዝብ እንዲታገስ ጥርዬን አቀርባለሁ። ከዚህም በተጨማሪ፣ ጋዝና ነዳጅ ከእስያ ሀገሮች ለመግዛት በንግግር ላይ ነን።ሩሲያ በፑቲን ሥር፣ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሳለች። ከጥቂት ወራቶች በፊት በዓለም ላይ ግዙፍ የነዳጅ ና ተያያዥ ዘይቶች አምራች እና አከፋፋይዋ ሩሲያ፣ በዚህ ሰው አመራር አፈር መጋጥ ጀምራለች። በሕልሜም በውኔም፣ በዚህ መጠን ሩሲያ ትሽመደመዳለች ብዬ አስቤ አላውቅም። ፑቲን በእንዝህላልነቱ ነው፣ ጦሩም ብሩም እያለው፣ 40 ፐርሰንቱን የሩሲያ የኃይል ኢንዱስትሪን በዩክሬን ያስወደመው።
4 312
+2
| 🇮🇱 🇦🇲 ሰበር ዜና - የእስራኤል መንግሥት በአርሜኒያ ላይ ለተፈፀመው የዘር ማጥፋት ወንጀል/ ጀኖሳይድ፣ ሙሉ እውቅና መስጠቱ ተሰማ።
የእስራኤል መንግሥት የአርሜኒያ ጀኖሳይድን በይፋ ለማረጋገጥ የወሰነው በሙሉ ድምፅ ነው።
የአርሜኒያ የዘር ማጥፋት ወንጀል፣ በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት፣ በኦቶማን ኢምፓየር ውስጥ ይኖሩ በነበሩ የአርሜኒያ ሕዝብ እና ማንነት ላይ የተፈፀመ፣ ስልታዊ ውድመት ነበር።
ጀኖሳይዱ በቱርክ መንግሥት የተፈፀመ ሲሆን፣ በ1915 እና 1923 መካከል በጅምላ ግድያ፣ በረሃብ እና በግዳጅ የሞት ሰልፎች ወደ 1.5 ሚሊዮን የሚጠጉ አርመኖች እንዲጠፉ ተደርጓል።
የአርሜኒያ ጀኖሳይድ ጉዳይ፣ ለቱርክ መንግሥት ስስ ብልቱ እና አንገብጋቢ ርዕስ ነው። ለዚህ የዘር ማጥፋትም በዓለም ላይ እውቅና ለመስጠት የሚያስቡን መንግሥታትን እና ተቋማትን ስትቃወምና ስታሸማቅቅ ኖራለች።
በአሁኑ ጊዜ፣ የአውሮፓ ሕብረትን ጨምሮ በርካታ ሀገሮች፣ ለአርሜኒያ ጀኖሳይድ ቱርክን በታሪክ ተወቃሽ በማድረግ፣ እውቅና ሰጥተው ይገኛሉ።
የእስራኤል ለዘር ማጥፋቱ እውቅና መስጠት፣ የቱርክ መንግሥትን በበለጠ እንደሚያስቆጣ ይገመታል።
4 312
+1
| 🇮🇱 🇦🇲 ሰበር ዜና - የእስራኤል መንግሥት በአርሜኒያ ላይ ለተፈፀመው የዘር ማጥፋት ወንጀል/ ጀኖሳይድ፣ ሙሉ እውቅና መስጠቱ ተሰማ።
የእስራኤል መንግሥት የአርሜኒያ ጀኖሳይድን በይፋ ለማረጋገጥ የወሰነው በሙሉ ድምፅ ነው።
የአርሜኒያ የዘር ማጥፋት ወንጀል፣ በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት፣ በኦቶማን ኢምፓየር ውስጥ ይኖሩ በነበሩ የአርሜኒያ ሕዝብ እና ማንነት ላይ የተፈፀመ፣ ስልታዊ ውድመት ነበር።
ጀኖሳይዱ በቱርክ መንግሥት የተፈፀመ ሲሆን፣ በ1915 እና 1923 መካከል በጅምላ ግድያ፣ በረሃብ እና በግዳጅ የሞት ሰልፎች ወደ 1.5 ሚሊዮን የሚጠጉ አርመኖች እንዲጠፉ ተደርጓል።
የአርሜኒያ ጀኖሳይድ ጉዳይ፣ ለቱርክ መንግሥት ስስ ብልቱ እና አንገብጋቢ ርዕስ ነው። ለዚህ የዘር ማጥፋትም በዓለም ላይ እውቅና ለመስጠት የሚያስቡን መንግሥታትን እና ተቋማትን ስትቃወምና ስታሸማቅቅ ኖራለች።
በአሁኑ ጊዜ፣ የአውሮፓ ሕብረትን ጨምሮ በርካታ ሀገሮች፣ ለአርሜኒያ ጀኖሳይድ ቱርክን በታሪክ ተወቃሽ በማድረግ፣ እውቅና ሰጥተው ይገኛሉ።
የእስራኤል ለዘር ማጥፋቱ እውቅና መስጠት፣ የቱርክ መንግሥትን በበለጠ እንደሚያስቆጣ ይገመታል።
4 312
+1
| 🇮🇱 🇦🇲 ሰበር ዜና - የእስራኤል መንግሥት በአርሜኒያ ላይ ለተፈፀመው የዘር ማጥፋት ጀኖሳይድ እውቅና ለመስጠት ወሰነ። የአርሜኒያ የዘር ማጥፋት ወንጀል፣ በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በኦቶማን ኢምፓየር ውስጥ የአርሜኒያ ሕዝብ እና ማንነት ስልታዊ ውድመት ነበር።
በቱርክ መንግሥት የተቀናበረ ሲሆን፣ በ1915 እና 1923 መካከል በጅምላ ግድያ፣ በረሃብ እና በግዳጅ የሞት ሰልፎች ወደ 1.5 ሚሊዮን የሚጠጉ አርመኖች እንዲጠፉ ተደርጓል።
የአርሜኒያ ጀኖሳይድ ለቱርክ ስስ ብልቷ ሲሆን፣ ለዚህ የዘር ማጥፋት በዓለም ላይ እውቅና የሚሰጡ መንግሥታትን እና ተቋማትን ስትቃወምና ስታሸማቅቅ ኖራለች።
የአውሮፓ ሕብረትን ጨምሮ በርካታ ሀገሮች፣ ለአርሜኒያ ጀኖሳይድ፣ ቱርክን በታሪክ ተወቃሽ በማድረግ፣ እውቅና ሰጥተዋል።
የእስራኤል ለዘር ማጥፋቱ እውቅና መስጠት፣ የቱርክ መንግሥትን በበለጠ እንደሚያስቆጣ ይገመታል።
4 312
🇹🇷🇮🇱⚡ "[የቱርክ ፕሬዝዳንት] ኤርዶጋን፣ የእስራኤል መንግስት እንዲጠፋ ጥሪ ሳያቀርብ አንድ ቀን አያልፍም። እነዚህን ቃላት በቁም ነገር እንመለከታቸዋለን። ምክንያቱም፣ በሕዝባችን ታሪክ ውስጥ አንድ ነገር ከተማርን፣ አንድ ሰው 'መጥፋት አለብህ' ሲል፣ ማስፈራራቱን በቁም ነገር እና በሙሉ ንቃት መውሰድ እንዳለብን ነው። እነዚህን ጉዳዮች እንዲሁ ንግግር ናቸው ብለን አናልፋቸውም እና የአሜሪካን ጓደኞቻችንን ትኩረት ወደ እነዚህ መግለጫዎች እንስባቸዋለን። እኛ ችላ አንልም!"
- የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ።
4 312
🇬🇧 የዩናይትድ ኪንግደም ተሰናባቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ስታርመር፣ የኔቶ ዋና ፀሃፊነትን ቦታ ለመያዝ አቅዷል። ይህ በብሪታንያ ዘ ኦብዘርቨር ጋዜጣ ላይ ተዘግቧል።
ቀደም ሲል፣ ስታርመር ለእሱ "ሩሲያን መጥላት መካከለኛው ምስራቅን ከመርዳት የበለጠ አስፈላጊ ነው" ብሏል። በ2030 ከሩሲያ ጋር ጦርነት ሊፈጠር እንደሚችል በማስጠንቀቅ የኔቶ የመከላከያ በጀት እንዲጨምርም ጥሪ አቅርቧል።
4 312
🇻🇪⚡️ተጨማሪ የአሜሪካ ወታደሮች ምስል በላጉዌራ ከተማ፣ ቬኔዝዌላ።
"አቤት ታድለ…ን" ይላሉ መቼስ ቬኔዝዌላዎች፣ እነዚህን ሲያዩ።
ሕዝቡ ተባሮ ነው እንጂ፣ ከበው ነበር እንደ ዕንቁ የሚያዩዋቸው ይሄን ጊዜ ቢፈቀድላቸው። የፈረንጅ ወታደሮች፣ ያውም የአሜሪካ ናቸው እኮ።
4 312
+2
🇮🇶⚡️ - በባግዳድ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ 15 ከፍ ብሏል። ሚኒስትሮች፣ አማካሪዎች፣ ዳይሬክተሮች እና የፓርላማ አባላት ናቸው፣ እንደ ኢራቅ ቻናሎች ዘገባ።
4 312
+2
🇮🇶⚡️በባግዳድ የጅምላ እስራት፡
በባግዳድ አረንጓዴ ዞን እና በሌሎች የዋና ከተማው ክፍሎች በርካታ የኢራቅ የፖለቲካ ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዘገባዎች ያመለክታሉ። ከታሰሩት መካከል፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር እና በርካታ የቅርብ ረዳቶቻቸው ይገኙበታል። በቁጥጥር ሥር የዋሉት፣ እንደ አንዳንድ ምንጮች፣ 'መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ ሙከራ አድርጋችኋል' በሚል ነው። ሌሎች፣ ከመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ጋር በተያያዘ ሳይሆን በአሸባሪው የኢራቅ የፍትህ አካላት በተሰጠ የውሸት ማዘዣ ተይዘዋል፣ ይላሉ። የታሳሪዎቹ ባለስልጣናት ቁጥር ብዙ ሲሆን፣ ሁሉም የሱኒ እስልምና እምነት ተከታይ ናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር አሊ ዛይዲ፣ ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተልኩኝ ነው፣ ብሏል።
4 312
🇮🇶⚡️ — የኢራቅ ፀረ ሽብር ኃይሎች፣ በባግዳድ ግሪን ዞን የሚገኘውን እና ባለስልጣናትንና ቤተሰቦቻቸውን የያዘውን Sikma መኖሪያ ህንፃን ሰብረው ገብተዋል።
በድጋሜ፣ ባይረጋገጥም፣ በአሁኑ ሰዓት በኢራቅ መፈንቅለ- መንግሥት እየተደረገ ይመስላል።
4 312
🇮🇶 ሰበር ዜና፡ በባግዳድ በሚገኘው የመንግሥቱ መቀመጫ፣ Green Zone፣ በአሁኑ ሰዓት መፈንቅለ መንግሥት እየተደረገ ይመስላል።
ቤተ መንግሥቱ በታንኮች ተከቧል፣ ወታደሮች ሰብረው በውስጡ በመግባት እስካሁን ማንነታቸው ያልተረጋገጠን ሁለት ባለስልጣናትን ወስደዋል። በከተማው ከፍተኛ ተኩስ ይሰማል፣ የወታደሮች እንቅስቃሴ በስፋት ይታያል።
ዜናው አልተረጋገጠም፣ ነገር ግን በኢራቅ፣ መፈንቅለ-መንግሥት በመደረግ ላይ ይመስላል።
4 312
🇮🇷⚡️🇺🇸 በዛሬው ሌሊት የአሜሪካ ጦር ኃይሎች፣ በኢራን ባንደር አባስ፣ ከሽም፣ እና ካሪግ ደሴቶችን ክፉኛ እንደደበደቡ ታውቋል።
ድብደባው፣ ዛሬ ጠዋት ኢራን በበርካታ የንግድ መርከቦች ላይ ተኩሳለች፣ የሆርሙዝ ወሽመጥ መተላለፊያንም አስተጓጉላለች በሚል የተወሰደ "አፀፋዊ እርምጃ" ነው፣ ብሏል CENTCOM።
በምላሹ፣ ኢራን በባሕሬንና በኩዌት በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች፣ በኢሳ አየር ኃይል እና በአሊ አል ሳሊም፣ ላይ በድሮንና ሚሳዬሎች የታገዘ ጥቃት ከፍታለች።
የኢራን ጥቃት አሁንም አላባራም። በተመሳሳይ አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን፣ የአሜሪካ የምሽቱ ድብደባ እንደተጠናቀቀ ለFOX NEWS ተናግሯል።
