የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
前往频道在 Telegram
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
显示更多未指定国家未指定类别
514
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
በኢትዮጵያ ንባብን የማስተዋወቅ ሥራ መሥራት ቅንጦት አይደለም፡፡ (የባህል ስፖርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ነፊሳ አልማህዲ)
የካቲት 22/2018 ዓ.ም
አርባ ምንጭ ከተማ
============
የንባብ ሳምንት፣ቡክፌር፣የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ ሥልጠና እና የፖናል ውይይት መርሐ ግብር በይፋ ተከፈተ።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት “የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!” በሚል መሪ ቃል ከደቡብ ኢትዮጵያ ባህል ቱሪዝም ቢሮ እና ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመተባበር ከየካቲት 22-25/2018 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ የተዘጋጀው የንባብ ሳምንት፣ ቡክፌር፣የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ ሥልጠና እና የፖናል ውይይት መርሐ ግብር በይፋ ተከፍቷል።
በመርሐ ግብሩ የባህል ስፖርት ሚኒስቴር ሚንሰትር ዴኤታ ክብርት ነፊሳ አልማህዲ፣የአገልግሎቱ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው፣የአገልግሎቱ ሥራ አመራር አቶ አብነት አበራ እና የሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣የአርባ ምንጭ ም/ከንቲባ ወ/ሮ ሊድያ ከንቲባ፣የደ/ኢ /ክልል ባ/ስ/ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ታሪኩ ኦይቻ፣ደራሲ ይታገሱ ጌትነት፣ ደራሲ ዮሐንስ ገ/መደህን እና ደራሲ ሃያሲ ገዛኸኝ ሀብቴ፣የሀገር ሽማግሌዎች፣ ተማሪዎች እና የሚድያ አካላት ተገኝተውበታል።
በመርሐ ግብሩ ንግግር ያደረጉት የባህልና ሰፖርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ነፊሳ አልማህዲ ኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ንባብ ባህል
እንዲሆን መሥራት እና የሀገርና ሕዝብ ባህል፣ ታሪክ፣ ጥቅም መዝግበው የያዙ የመረጃ ሀብቶችን በማሰባሰብ ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የአንድ ሀገር እድገትና ብልጽግና ከምንም በላይ ሀገሪቱ ባላት የሰብዓዊ ሀብት ጥራት ላይ መመስረቱን ገልጸዋል።
የሰብዓዊ ሀብት ጥራት ከሚሻሻልባቸው መንገዶች መካከል ንባብ አንዱ ነው፡፡ ንባብ የሰብዓዊ ሀብት ልማት መሰረት ለሆነው የትምህርት ሥራ መሰረታዊ ግብዓት ነው፡፡
ንባብ ሰዎች ከትምህርት ቤት ውጭ ራሳቸውን የሚያበለጽጉበት፣ እውቀታቸውን እና ክህሎታቸውን የሚያሻሽሉበት ቁልፍ መሳሪያም ነው፡፡
ሀገራችን ሕጻናትን፣ ወጣቶችን፣ ጎልማሶችን በአጠቃላይ ዜጎቸን በየደረጃው ለማስተማር እጅግ በጣም ከፍተኛ ወጪ የምታወጣ መሆኑ ለዚህ አንዱ ምክንያት ሊሆን እንደሚችል፤
በሚማሩበት የክፍል ደረጃ የሚጠበቅባቸውን ያህል የማንበብና የመጻፍ ክህሎት ሳይኖራቸው ክፍል እየቆጠሩ የሚሄዱ ተማሪዎች መኖራቸው በየትምህርት ቤቶቻችን የምናየው ሃቅ ነው፡፡
በአሁኑ ጊዜ ሀገራችንን የገጠሟት በርካታ ችግሮች ቢመረመሩ አሁን ካለን የንባብ ባህልና እውቀትን የመሻት ባህሪ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል መገመት ይቻላል።
የተለያዩ በንባብ ባህል ዙሪያ የሚዘጋጁ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ።
ከተቀናጀን የታመመ የንባብ ባህላችንን እና የትምህርት ሥርዓታችንን ማከም እንችላለን።
ንባብን እና የንባብ ባህልን የማስተዋወቅና የማስፋፋት ሥራ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት ሊከናወን እንደሚገባም ክብርት ሚኒሰትሯ ጠቁመዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በአርባ ምንጭ ከተማ ም/ከንቲባ በወ/ሮ ሊድያ ከንቲባ ሲደረግ ዘግጅቱን አስመለክቶ ገለጻ በአገልግሎቱ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው፤ መልዕክት በደቡ/ኢት/ያ ባህልና ስፖርት ቢሮ ም/ኃላፊ በአቶ ታሪኩ ኦይቻ ሲደረግ በደራሲ ይታገሱ ጌትነት እና በደራሲ ዮሐንስ ገ/መድህን ንባብን በተመለከተ አነቃቂ ንግግር ሲቀርብ በዞኑ የሰርከስ ቡድን ትርኢቶች ቀርቧል።
አገልግሎቱ በዞኑ ለሚገኙ ት/ት ቤቶች ቤተ መጻሕፍት ቤትና የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት ቤት በስጦታ ያበረከታቸውን በቁጥር አራት ሺህ ሰባሰባት /4077/ መጻሕፍት እና በበጀት ከአንድ ሚልየን ሦሥት መቶ አርባ ሁለት ሺህ ብር በላይ የፈጁ መጽሐፍትን ክብርት ሚኒስቴር ነፊሳ ለአርባ ምንጭ ት/ት መምሪያ ኃላፊ አበርክተው
በመጨረሻም አገልግሎቱ ለእይታ ያቀረባቸው የጋሞና አካባቢው የፎቶ እና መዛግብት መረጃ እንዲሁም የመጻሕፍት ሽያጭ ኤግዚቢሽን በባህልና ስፖርት ሚኒሰቴር ዴኤታ በክብርት ነፊሳ አልማህዲ፣ በክልልና በዞን አመራሮች በይፋ ተከፍቷል።
በከሰዓቱ የሥነ ጽሑፍ መድረክ ዝግጅት መርሐ ግብር በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ታተየኪነ ጥበብ ክፍል ተማሪዎች ትምህርት አዘል የሥነ ጥበብ ስራዎች ሲቀርቡ በደራሲና ሃያሲ ገዛኸኝ ሀብቴ፣በደራሲ ይታገሱ ጌትነት እና በደራሲ ዩሐንስ ገ/መድህን የንባብ ተምክሮ ለተማሪዎቹ ሲቀርብ ለዩኒቨርሲቲው የኪነ ጥበብ ክበብ ከአገልግሎቱ መጻሕፍት ተበርክቶ ዝግጅቱ ተጠናቋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት “የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!” በሚል መሪ ቃል ከደቡብ ኢትዮጵያ ባህል ቱሪዝም ቢሮ እንዲሁም ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከየካቲት 22-25/2018 ዓ.ም የንባብ ሳምንት፣ ኤግዚቢሽን፣ሥልጠና እና የፓናል ውይይት ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚቆይ መርሐ ግብር ለማዘጋጀት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
👉ተቋሙ በቆይታው የንባብ ሳምንት ያካሒዳል።
👉የጋሞ እና አካባቢውን የሚመለከቱ ምስሎች ከተቋሙ ክምችት የተመረጡትን ያስጎበኛል።
👉የንባብ ክበባት ምሥረታ ያካሂዳል።
👉የድራሲያን ተሞክሮና አነቃቂ ንግግር ይደረጋል፡፡
👉 የሥነ-ጽሑፍ ምሽት ያካዳል፡፡
👉 ለትምህርት ቤቶች የመጻሕፍት ስጦታ ያደረጋል፡፡
👉የፓናል ውይይት ያካሒዳል።
👉በጊዶሌ ማረሚያ ቤት የንባብ ቀን ያካሒዳል፡፡
👉የታራሚዎች የሥነ ጽሑፍ ውድድር ያካሒዳል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
+6
ታላላቅ የሙዚቃ ባለሙያዎች በተቋሙ ጉብኝት አደረጉ
በኢትዮጵያ የሙዚቃ እና የኪነጥበብ ዘርፍ አሻራቸው ጎልቶ ከሚጠቀሱት የኪነጥበብ ባለሙያዎች መሀል ስማቸው የሚጠቀሱት ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ፣ ጸጋዬ እሸቱ፣ አብርሃም ወልዴ እና ሸዋንዳኝ ኃይሉ የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር)ን ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸውም በታላቁ የጥበብ ሰው ያየህይራድ አላምረው ተሰባስበው በቤተሰቡ የተበረከቱ የጽሑፍ፣የድምፅ እና ምስል ክምችትን በማደራጀት በስሙ የተቋቋመውን ቤተመጻሕፍት እና የተቋሙን የቤተመጻሕፍትና የመዛግብት እንዲሁም የኦድዮ ቪዥዋል አገልግሎት ክፍሎችን ተመልክተዋል።
የኪነጥበብ ባለሙያዎቹ በተቋሙ ስብስብ፣አደረጃጀትና አገልግሎት አሰጣጥ አድናቆታቸውን ገልጸው እነሱም ያላቸውን የመረጃ ሀብቶች ወደ ተቋሙ በማምጣት ለትውልድ ለማሻገር ቃል ገብተዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
https://youtube.com/watch?v=p5Fe3fhBl7M&si=9sag8a68tuaIM-1R
የካቲት 12 89ኛው የሰማዕታት መታሰቢያ ቀን የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፣በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም እና ከዕዝራ ሱቱኤል የጥናትና ምርምር ማዕከል በጋራ የተዘጋጀ ሲምፖዚየምን በማስመልከት በፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን “ ሀገር አሳልፎ የሚሰጥ ኢትዮጵያዊ የለም” በሚል ከተዘገበው የተወሰደ……..
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ነፃነትን ተንከባከቧት እውነት ራሷን ትጠብቃለች፤ነፃነት በሌለበት የተገለጠች እውነት ራሷን ታጠፋለች (የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት)
የካቲት 13/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የካቲት 12 የሰማዕታት መታሰቢያ በዓል በፓናል ውይይት ተከበረ፡፡
እንደ ሀገር ለ89ኛው ጊዜ ታስቦ የዋለው የካቲት 12 የሰማዕታት መታሰቢያ በዓል የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፣በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም፣ከዕዝራ ሱቱኤል የጥናትና ምርምር ማዕከል እንዲሁም ከጥንታዊው የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በጋራ በተዘጋጀ መድረክ ቀኑን አስመልክቶ የፓናል ውይይት በማካሔድ አክብሯል፡፡
በፓናል ውይይቱ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ዳይሬክተር ዶ/ር ዮሐንስ አድገህ፣ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፣ የዕለቱ የክብር እንግዳ የጀግኖች አርበኞች ማኀበር ሊቀመንበር ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ተወካይ እና የማህበሩ ሥራ አመራር ጥላሁን ጣሰው፣ስለታሪኩ በርካታ መጻሕፍት የጻፉት ፕሮፌሰር ኢነ ካምፕቤል፣ የተከበሩ አምባሳደር ወ/ሮ ሙሉ ሰለሞን፣ የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች፣ የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊትና የፖሊስ አባላት፣ሚዲያና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ ተሳታፊዎች የተገኙበት ነበር፡፡
በዝግጅቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት ነፃነትን ተንከባከቧት እውነት ራሷን ትጠብቃለች፤ነፃነት በሌለበት የተገለጠች እውነት ራሷን ታጠፋለች በማለት ተናግረው ዛሬ በነፃነት አንገታችንን እንዳንደፋ ያደረጉ አባቶቻችን ያስረከቡንን ታላቅ ሀገር ለጠላት አሳልፈን ባለመስጠት የድርሻችንን መወጣት እንዳለብን ተናግረዋል፡፡
በዕለቱም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ዳይሬክተር ዶ/ር ዮሐንስ አድገህ እና የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ቀኑን በማስመልከት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የዕዝራ ስቱኤል የጥናትና ምርምር ማዕከል መሥራች አቶ ዕዝራ ንጋቱ የዕለቱን መርሐ ግብር በማስመልከት ንግግር ሲያደርጉ የአገር ነፃነት በወርቅ በብርና በዕንቁ የሚገበይ ሳይሆን በስራ በድካምና በደም የሚገዛ የከበረ ህይወት ነው ብለዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ የጀግኖች ማኀበር ሊቀመንበር ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ተወካይ እና የማህበሩ ሥራ አመራር ጥላሁን ጣሰው በዓሉ ለምን ታስቦ እንደሚውልና እንዴት እንደሚከበር ሲገልጹ ግፉ፦ የፋሺስት ወታደሮች እና ባንዳዎች የየካቲት 12 ተጎጂዎችን በጥይት፣በአካፋ እና በዶማ መጨፍጨፋቸው በታሪክ ተመዝግቧል፤መታሰቢያ፦ ይህ ቀን በየዓመቱ የካቲት 12 በአዲስ አበባ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የሰማእታት ሐውልት መታሰቢያ የአበባ ጉንጉን በማኖር እና የሐገር ፍቅር ጽናትን በማሰብ እንደሚከበር እና ዓላማ፦ ቀኑ አባቶቻችን ለሀገራቸው ነፃነት የከፈሉትን መስዋዕትነት ለመዘከር፣ የሰማእታቱን አልገዛም ባይነት ጽናት ለመዘከር እና አሁን ያለውን ትውልድ ሀገሩን እንዲጠብቅ ለማስተማር እንደሚውልም ተናግረዋል፡፡
የካቲት 12 ቀን በ1929 ዓ.ም የፋሺስት ኢጣሊያ ወታደሮች በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ላይ ያደረሱትን ዘግናኝ ጭፍጨፋ የምናስብበት የሰማእታት ቀን መሆኑን በወቅቱ የጣሊያን ምሥራቅ አፍሪቃ ገዢ የነበሩት ሮዶልፎ ግራዚያኒ ላይ በተፈጸመው የግድያ ሙከራ ተበቅለው፣ ለሦስት ቀናት ባካሄዱት የዘፈቀደ ጭፍጨፋ ከ30,000 በላይ ንጹሐን ኢትዮጵያውያን የተገደሉበትን የሚያሳይ የመነሻ ጽሑፍ በታሪክ ተመራማሪው ዲያቆን ተረፈ ወርቁ ለውይይት ቀርቦ ከተሳታፊዎች ሃሳብ አስተያየት ተሰጥቶበታል፡፡
በመጨረሻም ለእይታ የተዘጋጀ የሥዕል ኤግዚቢሽን ተጎብኝቶ ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
ዓለም አቀፍ የአረጋውያን ቀን እና አካቶ ትግበራን አስመልክቶ ለተቋሙ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ ።
የካቲት 5/ 2018ዓ.ም
ዓለም አቀፍ የአረጋውያን ቀን እና አካቶ ትግበራን አስመልክቶ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የአካል ጉዳተኞች ጉዳይ መሪ ስራ አስፈጻሚ በአቶ ሲሳይ ጥላሁን ለተቋሙ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ።
የአካል ጉዳት ምንነት፣ አካል ጉዳተኞችን ማካተትና በማካተት ሂደት ያሉ ተግዳሮቶች፣ እይታዎች /ሞዴሎች/ እንዲሁም የህግ ማዕቀፎች ስልጠናው ያተኮረባቸው ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው።
በአካል ጉዳተኞች ዙሪያ ካሉ እይታዎች /ሞዴሎች/ መካከል አካል ጉዳተኝነትን ከሀይማኖት፣ ከሀጢዓት፣ እርዳታ ፈላጊና ጥገኛ የሚያደርጉ እይታዎች በሰለጠነው አለም እስከ 18ኛው ክ.ዘ ድረስ የነበረ በሀገራችን በኢትዮጵያ ግን መሻሻሎች ቢኖሩም እስከ አሁን ድረስ ያለ የተሳሳተ እይታ እንደሆነ በቀረበው ጥናታዊ ፅሁፍ ላይ ተመላክቷል።
በተቋም ደረጃ የሚሰጡ አገልግሎቶችን አካታች ለማድረግ አካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያን፣ የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ተጋላጭ የኅብረተሰብ ክፍሎች የእኩል እድል ተጠቃሚና ተሳታፊ የሚሆኑበት ሁኔታ ማመቻቸት እንደሚገባ የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1263/ 2014 መሰረት በማድረግ ተገልጿል።
በመጨረሻም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሀገሬ መኮንን የአረጋውያን ቀንን አስመልክቶ ጌጦቻችን ስለሆኑ አረጋውያንን እናክብር ሲሉ፤
አካቶ ትግበራን አስመልክቶ ደግሞ በተቋም ደረጃ የተሰሩትንና አሁንም መሻሻል ያለባቸውን ጉዳዮች በመለየት ገለፃ አድርገዋል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
"መጽሐፍትን በማንበብ እንታረም!" በሚል መሪቃል በባሌ ዞን ማረሚይ ቤት የተካሔደ የንባብ ቀን ሥነሥርዓት በሀገሬ ቲቪ የተላለፈ:-
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!!
ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker
ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
Twitter:https//@wemezekr
በሮቤ ከተማ የተካሔደ የንባብ ሳምንት ዝግጅት መርሐ ግብር የመክፈቻ ሥነሥርዓት ከሀገሬ ሚድያ ከተላለፈ የተወሰደ፡፡
