Eotc Task Force
الذهاب إلى القناة على Telegram
7 369
المشتركون
-524 ساعات
+267 أيام
+35130 أيام
أرشيف المشاركات
7 372
የOMN ልጅ OBN ሞታችንን ለመሸፋፈን ከአዲስ አበባ ተነስቶ ሽርካ ድረስ ተጉዙአል። ሙስሊሞችን የባሕል ልብስ አልብሰው በእስታድዮም ሰብስበው " የፋሲካ በዓል አከበርን"የሚል ፕሮፖጋንዳ ሠርተዋል።መርሐግብሩ የተካሄደው መጋቢት 28/2018ዓ.ም ነው እነርሱ ግን በትንሳኤ ቀን እንደተካሄደ አድርገው ነው ያቀረቡት። ጭውውት አዘጋጅተው በኦርቶዶክሳውያን ላይ፣ልጆቼ ለምን ይገደላሉ ?ብለው የተናገሩ የሃገረ ስብከቱን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ኤልሳዕንም ወረኞች፣ወፈፌዎች፣ወሬ አናፋሾች፣አልቃሾች ብለው የስላቅ መልእክቶችን አስተላልፈዋል።ይኽ የኾነው የዞነ አስተዳዳሪ እነ ኢብራሂም ከድር በተገኙበት ነው።
https://t.me/Eyo21e
7 372
#አርሲ #አሰኮ
በምሥራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ዲማ አሰኮ ቀበሌ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ትናንት በ 05/08/2018ዓ.ም ሌሊት ከፍተኛ ተኩስ ተከፍቶባቸው ነው ያደሩት። ለጊዜው ግን የተገደለ ሰው የለም።እዚሁ ቀበሌ ላይ በሰሙነ ሕማማት በዕለተ ረቡዕ ማለትም በመጋቢት 30/2018ዓ.ም ይልማ ገብረ መስቀል የተባሉ የ80 ዓመት አዛውንት በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደለዋል አንድ ልጃቸውም የአካል ጉዳት ደርሶበታል ።አዛውንቱን ከገደሏቸው በኋላም አንገታቸውን ገዝግዘው ሆዳቸውን ቀዳደው ነው ጥሎአቸው የሄዱት።
7 372
#አርሲ_ዲገሉናጢጆ
በምሥራቅ አርሲ ዞን ዲገሉና ጢጆ ወረዳ ኦርቶዶክሳውያን የሚበዙባቸው ቀበሌዎች ላይ ወሀቢያዎች ጥቃት እየሰነዘሩ ነው። ኦርቶዶክሳውያን ከቤታቸው ማደር ብርቅ ሆኖባቸው በየጫካው እየተንከራተቱ ነው። እዚሁ ወረዳ ላይ ከሳምንት በፊት ሁለት ኦርቶዶክሳውያን ተገድለው ነበር።በዚህ ወረዳ በገጠሩ ክፍል ያለው ኦርቶዶክሳዊ 99% የሸዋ ኦሮሞ ኦርቶዶክስ ቢሆንም "አንተ ኦሮሞ ነህ "ብለው አልራሩለትም ዓላማቸው ኦርቶዶክስን ከኦሮሚያ ማጽዳትና ማጥፋት ነውና።
7 372
አስኳይ መረጃ #ሽርካ
[መረጃው ለሁሉም እንዲደርስ እናጋራው]
ከፌዴራል መንግሥትና ከክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተሰጠው ቀጭን ትእዛዝ ትናንት ማለትም በ28/07/2018ዓ.ም የምሥራቅ አርሲ ዞን ምክት አስተዳዳሪ አቶ ስንታየሁን ጨምሮ በ እምነታቸው ሙስሊምና ፕሮቴስታንት የሆኑ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከOBN ጋዜጠኞች ጋር የኦርቶዶክሳውያን መታረጃ ቄራ ወደሆነችው ሽርካ አቅንተው ነበር።ለወሀቢያ ትጥቅና ስንቅ አቅራቢው አቶ ጣሂር አሚኖ ደግሞ የወረዳውን ሕዝብ በጎቤሣ ከተማ ሰብስቦ ጠበቃቸው። ስብሰባው እንደ ተጀመረ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ መልእክቶች መተላለፍ ጀመሩ ።"ለምን በሃይማኖታችን ተገደልን አላችሁ? እናንተ የመንግሥታችን ጠላቶች ናችሁ የመንግሥታችንን ገጽታ አበላሻችሁት ይኽ መረጃ እንዲወጣ ያደረጉ ጽንፈኞች ላይ እርምጃ እንወስዳለን"እያሉ ቁጣቸውን ቀጠሉ።በመሐል እነርሱን ተከትሎ የመጣ አርቲስት ዘፈን ሲያቀርብ በሰብሰባው ላይ የተሳተፉ ሙስሊሞች አብረው ሲጨፍሩ ኦርቶዶክሳውያን ደግሞ እኛ ሀዘን ላይ ነን ብለው በዝምታ ይመለከቷቸው ነበር።ይኽን ያዩ ባለሥስጣናት ለምንድ ነው የማትጨፍሩት?ምን ሆናችሁ ነው የምታዝኑት? እያሉ ተቆጡ።እንዲያና እንዲህ እያሉ በመጨረሻም እነዚህን ውሳኔዎች አስተላልፈው ስብሰበው ተቋጨ።
1) "ኦርቶዶክሳውያን ተገደሉ"ተብሎ ሲሠራጭ የነበረው የሐሰት መረጃ መሆኑን እና እምነትን ከእምነት ለማጋጨት የታሰበ የጽንፈኞች ሴራ መሆኑን በOBN Tv እንዲተላለፍ እና ሌሎች የመንግሥት ሚዲያዎችም እንዲጋሩት የሚዲያ ሠራዊቶችም እንዲያስተጋቡት።
(ይኽን የሐሰት ዜና ለማቀነባበር፦
👉 ባለፈው 29 ኦርቶዶክሳውያን ከተገደሉበት ከጃዊ ዋጬ ቀበሌ ሙስሊሞች ቀበሌውን ለቀው እንዲወጡ ተደርጓል
👉 በተለያዩ ስፍራዎች ላይ ያሉ ኦርቶዶክሳውያን የመንግሥት ሠራተኞች እርዳታ ለማሰበሰብ ሲጀምሩ መረጃው የደረሳቸው የወረዳው ባልጣናት ሙስሊሞችም ተገድለዋል ተሰደዋልና እነርሱንም አካቱ የሚል ማስፈራሪያ አዘል መልእክት አስተላልፈዋል )
2) ኦርቶዶክሳውያን ላይ ጭፍጨፋ መፈጸሙን በቪድዮና በምስል መረጃዎችን አጋርተዋል ተብለው በሚጠረጠሩ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ
3) ለይስሙላ ጣል ጣል የተደረጉ በጸጥታ መዋቅር(ፖሊስና ሚሊሻ) ውስጥ ያሉ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ መረጃ የተገኘባቸው እርምጃ እንደሚወሰድባቸው
7 372
የዛሬው ለጉድ ነው
አንድ ቤተ መቅደስ ሰው ታፍኗል
********
በዛሬው ዕለት ክርስትና ሊያስነሱ የመጡ ቤተሰቦችን እና አገልጋዮችን በአርሲ እና ምስራቅ ሸዋ አዋሳኝ ላይ ከሚገኘው ኑራኤራ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ማንነታቸው የሚታወቁ መንግሥቱ ጡጦ የሚያጠባቸው የዋሃቢያ ታጣቂዎች አፍነው ወደየት እንደወሰዷቸው አይታወቅም።
7 372
ስምንት ዓመት ሙሉ በጅምላ ስንጨፈጨፈና ስንሰደድ እረኞቹ ምን ይሠሩ ነበር?
👉ገዳዮችን ይሸልሙ ነበር
👉ቀድመው የነቁ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን የሰንበት ትምህርት ቤት እና የማኅበራት ወጣቶችን እያደኑ ያሳስሩ ነበር
👉 የቤተ ክርስቲያንቱን ስደት የኦርቶዶክሳውያንን እልቂት ለማስቆም የተጀመሩ ንቅናቄዎችን ማኮላሸትና ፖለቲካዊ ቅርጽ ይሰጡ ነበር
👉የኦርቶዶክሳውያን እልቂት እንዳይቆም ኦርቶዶክሳውያንም ራሳቸውን እንዳይከላከሉ ከመንግሥት ጋር እየተወያየን ነው እየተነጋገርን ነው በውይይት እንፈተዋለን ወዘተ...እያሉ ሕዝቡን ያደነዝዙ ነበር
👉ስለ ደሞች ጭማሪ ፣ስለ ስውውር፣ስለ ህንጻ ግንባታ ያወሩ ነበር
👉 ኦርቶዶክሳውያንንን አፈናቅሎ ቤተ ክርስቲያን ብቻዋን እንድትቀር ያደረገውን ኮሪደር ልማት እየጎበኙ ያደንቁ ነበር
👉በሠንበተ ክርስቲያን ችግኝ ይተክሉ ነበር
👉ለአገዛዙ መሪ ዉዳሴ ያቀርቡ ነበር
👉የአገዛዙን ገጽታ ሲገነቡ ነበር
👉መናፈሻ ይጎበኙ ነበር
👉የዘር ሲኖዶስ መርስተው በኦርቶዶክሳውያን መካከል ልዩነትን ጥላቻችን መዝራት
የቀረውን እናንት ጨርሱበት
መልእክታችትን፦ወይ አባት ሆናችሁ ምሩን ወይ ደግሞ ዞር በሉልን ራሳችንን ከአጥፊዎች እንታደግ ዘንድ
https://t.me/Eyo21e
7 372
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
የአርሲ ዞን ካቢኔዎች እነ ኢብራሂም ከድር የሸዋ አማራ ኦርቶዶክሳውያንና የቱለማ ኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን እያስጨፈጨፉ በ ጭፈራና በዝላይ የአራት ኪሎ ጌቶቻቸውን በማስደት ላይ ናቸው።ከቤተ ክህነት ማንም ትንፍሽ እንዳይል አቡን ሳዊሮስ ቀጭን ትእዛዝ አውርደዋል።ለምን? የጌቶቻቸውን ገጽታ ያበላሽባቸዋልና።
7 372
◈ግፍን መላመድ ፍትሀዊ ህሊናን ያሳጣል።
◈በልምምድ ያለፍናቸው ነውሮች የወንጌልን እውነት ያጠፋሉ።
◈ኦርቶዶክሳዊ ልምምድ ክርስቶስን ወደ መምሰል ይወስደናል።
◈ኃጢአታዊ ልምምድ ደግሞ ዲያብሎስን ወደ መምሰል ያደርሰናል።
◈ክፋትን ጥፋትን እንደመለማመድ የሚያስፈራ ነገር የለም።
◈"ልማድ ከሰይጣን ይከፋል"የሚባለው ለዚህ ነው።
የኔታ ገብረ መድን እንየው
7 372
Repost from እምየ ተዋሕዶ ሚዲያ - Emye Tewahedo Media
በምስራቅ አርሲ ዞን የ80 ዓመት አዛውንትን ጨምሮ ሁለት ሰዎች በታጣቂዎች ተገደሉ
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን መርቲ እና ሮቤ ወረዳዎች ውስጥ መጋቢት 16 እና መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ባልታወቁ ታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት፣ የ80 ዓመት አዛውንትና የ67 ዓመት ጎልማሳ መገደላቸው ታውቋል።
በመርቲ ወረዳ ከቢሮ ኮኛ ቀበሌ ነዋሪ የነበሩትና ዕድሜያቸው ከ80 ዓመት በላይ የሆኑት አቶ በጋሻው ገብረ ህይወት፣ መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም አጥቢያ ላይ በታጣቂዎች ተገድለዋል።
እንደ መረጃዎች ገለጻ ከሆነ፣ በአካባቢው በሚኖሩ የክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ በተደጋጋሚ በሚደርስ ጥቃት ሳቢያ በርካታ ነዋሪዎች ቤትና ንብረታቸውን ጥለው ወደ አቦምሳ እና አጎራባች ከተሞች ተሰደዋል። ይሁን እንጂ ሟቹ አቶ በጋሻው "ከተማ ብሄድ የሚያስጠጋኝ የለም" በሚል በዚያው ለመቆየት በመገደዳቸው ለዚህ ጥቃት ሰለባ መሆናቸው ተገልጿል።
በተመሳሳይ ዜና፣ በሮቤ ወረዳ እንደቶ ቀበሌ አቶ ፍቅረ ገብረመድህን የተባሉ የ67 ዓመት ግለሰብ መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ.ም አጥቢያ ላይ በታጣቂዎች ተገድለዋል። ታጣቂዎቹ ግለሰቡን ከመገደላቸው ባለፈ፣ ከ6 በላይ ከብቶችን ነድተው መውሰዳቸው ታውቋል።
ከግድያውና ከንብረት ዘረፋው በተጨማሪ፣ በአካባቢው በታጣቂዎች ተይዘው ከነበሩ ሰዎች መካከል የተወሰኑት መለቀቃቸው ቢገለጽም፣ ሌሎች እስካሁን በታጣቂዎች እጅ እንደሚገኙ ተመልክቷል።
በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚከሰተው ይህ የጸጥታ ችግር ነዋሪዎችን ለከፍተኛ ስጋትና መፈናቀል እየዳረገ መሆኑን ከስፍራው የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።
መንግስት በበኩሉ በአካባቢው ያለውን የሰላም ሁኔታ ለማረጋጋትና ጥቃት አድራሾቹን ተጠያቂ ለማድረግ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አለማድረጉን እየተነገረ ነው።
ስምዐ ተዋሕዶ
7 372
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
ዐሥሩ የኦርቶዶክስ ኃጢአቶች፦
፩ኛ፦ በሃይማኖት ጸንታ ሀገርን ከነ ድንበሩ ታሪክን ከነ ምሥጢሩ ጠብቃ አስጠብቃ መኖሯ።
፪ኛ፦ፊደል ቀርጻ ቁጥር ወልጻ ብራና ዳምጻ ትውልድን እያስተማረች መምጣቷ።
፫ኛ፦እግዚአብሔርን ፈሪ ሰውን አክባሪ በመሆኗ
፬ኛ፦በአድዋ ጣልያንን ጦር ሰብቃ ጋሻ ነጥቃ በመመለሷ
፭ኛ፦በተቀደሰ እሤት እና ባህል የከበረ የዳበረ ትውልድ በመፍጠሯ
፮ኛ፦በአራሽ፣በቀዳሽ፣በተኳሽ፣በነጋሽ እሤት የተቃኘ ትውልድ በመፍጠሯ።
፯ኛ፦የሀገርን አንድነትን የትናንት ታሪክን አልጥልም አልጠላም በማለቷ።
፰ኛ፦በሀገር በቀል ዕውቀት የተቃኘ ባለ ቅኔ ባለዜማ ባለ ጥበብ በመሆኗ።
፱ኛ፦ሰው ሁሉ እኩል ነው ለማንም ፍትህ ያስፈልገዋል ብላ ፍትህ ርትዕን እንዲሰፍን በማስተማሯ የዳርዊን እሳቤን በማቃለሏ
፲ኛ፦እውነተኛ አንድነትን፣ክርስቶሳዊ ነጻነትን፣ተፈጥሯዊ እኩልነትን፣መስቀላዊ ታማኝነትን፣ወንጌላዊ ሥነምግባርን፣ልቡናዊሀቀኛነትን..ጠብቆ የሚኖር ሕዝብን በመፍጠሯበ።....የዚህ ተቃራናዎች ይጠሏታል።
https://t.me/Eyo21e
የኔታ ገብረመድኅን እንየው
