ar
Feedback
Legal Aid

Legal Aid

الذهاب إلى القناة على Telegram

⚖️ Legal Aid: Your essential hub for legal professionals and students! Stay updated on new laws, landmark judgments, vacancies, and key insights. Join us to empower your legal journey and connect with the community! 📚✨"

إظهار المزيد
1 636
المشتركون
+224 ساعات
+107 أيام
+1730 أيام
أرشيف المشاركات
የሴት አልባሳትን በመጠቀም ሲያጭበረብር የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ *** አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፡- ተጠርጣሪው ጀማል አነስ ይባላል፤ በቁጥጥር ስር የዋ
+1
የሴት አልባሳትን በመጠቀም ሲያጭበረብር የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ *** አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፡- ተጠርጣሪው ጀማል አነስ ይባላል፤ በቁጥጥር ስር የዋለው በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው አስኮ መናህሪያ አካባቢ ነው፡፡ ከማህበረሰቡ እሴትና ባህል ባፈነገጠ መልኩ የሴት ሂውማን ሄር፣ የጆሮ ጌጣ ጌጥ እና የመሳሰሉትን አለባበሶች በመጠቀም ሲንቀሳቀስ ነበር። ተጠርጣሪው ሴት መስሎ ከግለሰቦች ጋር ንግግር በሚያደርግበት ወቅት በመጠራጠር ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውልም ችሏል፡፡ በግለሰቡ ላይ በተደረገበት አካላዊ ፍተሻም ሴት ሳይሆን ወንድ ሆኖ መገኘቱን ከጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ተጠርጣሪ ጀማል አነስ ከዚህ ቀደምም ሴት መስሎ ሲያጭበረብር እንደነበር ከምስክሮች ቃል መረዳት የተቻለ ሲሆን ከተንቀሳቃሽ ስልኩ ላይም በተለያየ ጊዜ የተለያዩ የሴት አልባሳትንና ጌጣጌጦችን ለብሶ የተነሳቸው ፎቶ ግራፎች መገኘታቸውን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል፡፡ ከህብረተሰቡ እሴትና ባህል ባፈነገጠ መልኩ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች አንድም ለወንጀል ተግባር የሚደረጉ የማታለያ መንገዶች መሆናቸውን የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ህብረተሰቡ መሰል እንቅስቃሴዎችን ሲመለከት ለፖሊስ መረጃ መስጠት እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡ *

ወላጅ እናቱ በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተያ,ዘ ​ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር፣ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ፣ አየር ጤና ቀበሌ ውስጥ ወላጅ እናቱን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የተጠረጠረው ወጣት ዮሴፍ
+2
ወላጅ እናቱ በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተያ,ዘ ​ በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር፣ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ፣ አየር ጤና ቀበሌ ውስጥ ወላጅ እናቱን በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የተጠረጠረው ወጣት ዮሴፍ ከበደ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ። ​የክፍለ ከተማው ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ሟች ወ/ሮ ፍሬህይወት ገብረሚካኤል ተከራይታ ትኖርበት የነበረውን የተቆለፈ ቤት በር ሰብሮ በመግባት ባደረገው ፍተሻ፤ ሟች አንገቷ በቢላ ተቆርጦና ለብቻው በማዳበሪያ ተቋጥሮ መገኘቱን አስታውቋል። በፖሊስ የመጀመሪያ ደረጃ ማጣራት ግድያው የተፈፀመው ሰኔ 08 ቀን 2018 ዓ.ም አካባቢ ሲሆን፣ የቤቱ የውጭ በርም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ተቆልፎ ሰንብቷል። ​ፖሊስ አስከሬኑን ካነሳ በኋላ ባደረገው ፈጣን ክትትል፣ ወንጀሉን ፈፅሞ ወደ አዲስ አበባ የሸሸውና የ"666" አባል እንደሆነ የተነገረለት የሟች ልጅ ዮሴፍ ከበደ፤ ተመልሶ አክስቱ ቤት ተደብቆ ሳለ ወንጀሉን ከፈፀመበት ቢላ ጋር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል። ​የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ለሟች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን እየተመኘ፤ ይህ አሰቃቂ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ሌት ተቀን በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጧል። መረጃው የደብረብርሃን ፖሊስ መምሪያ ነው።

ክስ ቀርቦብኝ ከዚህ ቀደም ጉዳዩ በእርቅ ስምምነት መዝገቡ ተዘግቶ ነበር የሚለው መከራከሪያ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ባይነሳም በፍሬ ነገር ክርክር ላይ በእርቅ ስምምነት መዝገቡ ስለመዘጋቱ መከራከሪያ እስከተነሳ ድረስ ፍ/ቤቱ እንደ መጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ወስዶ በቅድሚያ እልባት ሊሰጠው የሚገባ እና ፍ/ቤቱ እንደመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አስቀድሞ ሊመለከተው የሚገባ ስለመሆኑ የፌደራል ሰበር ሰሚ ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 222041 ጥቅምት 15 ቀን 2015 የተሰጠ

>> የፍርድቤቶች አወቃቀር << ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች በሕገ-መንግሥቱ መሠረት በዋናነት በሁለት ማለትም #በፌደራል እና #በክልል መዋቅሮች የተደራጁ ሲሆኑ፣ እንደየስልጣን እርከናቸው እና እንደሚያዩት የጉዳይ አይነት ይከፈላሉ። >> የፌደራል ፍርድ ቤቶች << የፌደራል መንግሥትን ሕጎች፣ መብቶች እና ጥቅሞች የሚመለከቱ ጉዳዮችን የሚያዩ ፍርድ ቤቶች ናቸው።እነዚህም፦#በ_3_እርከኖች ይደራጃሉ፦ ፩ኛ #የፌደራል_መጀመሪያ_ደረጃ_ፍርድ_ቤት: አነስተኛ የይገባኛል ጥያቄዎችን እና የተወሰኑ የወንጀል ጉዳዮችን በመጀመሪያ ደረጃ የሚያይ። ፨፨ ፪ኛ #የፌደራል_ከፍተኛ_ፍርድ_ቤት: ከመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሚመጡ ይግባኞችን የሚያይ እንዲሁም በአንዳንድ ከባድ ጉዳዮች የመጀመሪያ ደረጃ ስልጣን ያለው። ፨፨ ፫ኛ #የፌደራል_ጠቅላይ_ፍርድ_ቤት: የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔዎችን በይግባኝ የሚያይ።በተጨማሪም የህግ ስህተት ያለባቸውን ጉዳዮች የሚያርም የሰበር ሰሚ ችሎት አለው። >> የክልል ፍርድ ቤቶች << በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የክልል መንግስታት (የከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ) የራሳቸው የፍርድ ቤት መዋቅር አላቸው። እነዚህ ፍርድ ቤቶች የክልሉን ህጎች እና ጉዳዮች ይመለከታሉ። እንደ ፌዴራሉ ሁሉ #በሦስት_እርከኖች_ይዋቀራሉ፦ ፩ኛ #የክልል_ወረዳ_ፍርድ_ቤት ፨፨ ፪ኛ #የክልል_ከፍተኛ_ፍርድ_ቤት ፨፨ ፫ኛ #የክልል_ጠቅላይ_ፍርድ_ቤት_የክልሉ_ከፍተኛ_የይግባኝ_እናየሰበር_ሰሚ_አካል >> ልዩ እና ሌሎች ፍርድ ቤቶች << ከተለመዱት መደበኛ ፍርድ ቤቶች በተጨማሪ እንደ አስፈላጊነቱ የሚቋቋሙ የፍርድ ቤት ዓይነቶች አሉ፦ ~ #የወታደር_ፍርድ_ቤቶች_ማርሻል፦በወታደራዊ ዲሲፕሊን እና ህግጋት ላይ የተመሰረቱ ጉዳዮችን የሚያዩ። ~ #የጉምሩክ_እና_የግብር_ይግባኝ_ሰሚ_ኮሚሽኖች_ችሎቶች፦ከታክስ እና ቀረጥ ጋር የተያያዙ ልዩ አቤቱታዎችን የሚያጣሩ።ከላይ በተዘረዘሩት ተቋማት ላይ የስልጣን ዘመን ገደብ የለም።የስልጣን ዘመን መገደቡ #ተቋማዊ_ነፃነትን_ለማረጋገጥ_ይረዳል። #ተጠያቂነትን_ለማስፈን_ይረዳል። #ከሙስናና_የጥቅም_ግጭት_ለመጠበቅ_ወሳኝ_ነው። ፨፨፨ >> #ገደቡ_በፍትህ_ሥርዓቱ_ላይ_የሚያመጣቸው_ጉልህ_ፋይዳዎች << ፩ኛ #ተቋማዊ_ነፃነት_Institutional_Independence የአመራሮች የስልጣን ዘመን በህግ ሲወሰን፣ ውሳኔዎቻቸው ከፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ እንዲሆኑና ፍትሕ ገለልተኛ በሆነ መንገድ እንዲሰጥ ያደርጋል። ፨፨፨ ፪ኛ #ተጠያቂነትን_ማስፈን_Accountability በአንድ አመራር ላይ የሚታዩ የአሰራር ክፍተቶችን ወይም የሙስና አደጋዎችን ለመቆጣጠር፣ የስልጣን ጊዜ ማብቂያ መኖሩ ያለአግባብ ስልጣንን ለራስ ጥቅም ማዋልን ይከላከላል። ፨፨፨ ፫ኛ #አዲስ_እይታና_ፈጠራ_Innovation የስልጣን ዘመን ገደብ ተቋማት በአዳዲስ ሀሳቦች እንዲታደሱ፣ የአሰራር ዘመናዊነት እንዲመጣ እና ቀጣይነት ያለው፦ #የፍትህ_ማሻሻያ_Justice_Sector_Reform እንዲኖር ያስችላል። ፨፨፨ ፬ኛ #የስልጣን_ሞኖፖሊን_ማስወገድ_Preventing_Concentration_of_Power ስልጣን በአንድ ግለሰብ እጅ ለረጅም ጊዜ እንዳይቆይ በማድረግ፣የስልጣን ሽግግር ሰላማዊና ጤናማ እንዲሆን አስተዋፅኦ ያደርጋል።

ያልተመዘገበ የጦር መሳሪያ እና የሰበር አቋም ✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅ በባልና ሚስት የንብረት ክፍፍል ክርክር ወቅት ድብቅ የጦር መሣሪያ መኖሩ እስከተረጋገጠ ድረስ በሕግ አግባብ ስልጣን ባለው አካል አለመመዝገቡ መሣሪያው የለም የሚያስብል ሳይሆን የኢኮኖሚ ጥቅም ያለው እና ባልና ሚስት በትዳር እያሉ የፈሩት እስከሆነ ድረስ ከሚመለከተው አካል ተመዝግቦ መሣሪያውን ለመያዝ ፈቃደኛ አለመሰጠቱ፣ የተጋቢዎች የጋራ ንብረት እንዳይሆን የማያደርገው ስለመሆኑ ​የአማራ ክልል የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 79/1995 አንቀጽ 73 (1) እና 101 መሠረት ተደርጎ በሰ/መ/ቁ፦ 179121 ቅፅ 25 ላይ የተሰጠ ዉሳኔ ነው ።

ኣዋጅ ቁፅሪ 366-2018_0001.pdf15.79 MB

ኣዋጅ ቁፅሪ 366-2018_0001.pdf15.79 MB

ዝፀደቀ ኣዋጅ 366/2018

የእቁብ/ሎቶሪ ህገወጥ ንግድ በኢትዮጵያ ንግድ ህግ ማእቀፍ መግቢያ #Ethiopia | ከትናንት ዛሬ እየተባባሰ የመጣው ከእለት እለት ስልክ በመደወል ቁጥሩ እየጨመረ የመጣው ለእቁብ ቁማር እና ለመሳሰሉት ገንዘቤን ተበላው አስመልስልኝ እባክህን እየተባለ የሚደወለው የስልክ ደውል አሁን ደግሞ በቅርብ የማውቃቻው ሰወች ይህን ያህል ገንዘብ ተበላው ያንተ መኖር ለእኛስ ካልሆነ ሙያህ ለሚቀርቡህ አይሆንም ወይ የሚል ተደጋጋሚ ጥያቄ እና ማሳሰቢያ የዚህ ጹሁፍ መነሻዬ ሲሆን አጠቃላይ በእንደዚህ አይነት ህገወጥ ተግባር ለተሳተፉ እና ለማህበረሰቡ ለግንዛቤ ይሆናል ከሚል መሠረታዊ ሀሳብ ይህንን እንድጽፍ አነሳስቶኛል። 1. እቁብ በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ ማንኛውም ስራዎች በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ ተካተው ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ ወይም ፖለቲካዊ ጥቅም ሊኖራቸው የሚገባ ስለመሆኑ የሚያጠራጥር አይደለም። ይሁን እንጂ አሁን አሁን እቁብ ሎተሪ እየተባለ እያማለሉ በደካማ ስለንቦናቸው በመግባት ገንዘባቸውን እየዘረፉ ቢከሱ እንኳን ለማግኘት አስቸጋሪ በሚሆነው ልክ ቅድሚያ ተዘጋጅተው በፍትህ ስረአት ውስጥ መተማመንን የሚያሳጡ የራስ አድር ባዮች በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ አለመተማመንን እያስነሱ ይገኛሉ። ይህንን ህገወጥ አካሄድ ለመግታት እና ለጥንቃቄ ያህል ይህ ጽሁፍ ለእናንተ ተዘጋጅቶ ቀርቧል። 2. እቁብ በኢትዮጵያ ንግድ ህግ እንዴት ይታያል? እቁብ አደራጆች በንግድ ስረአት ውስጥ ሆነው ተገቢውን የንግድ አሰራር እና ህግ ውስጥ በመግባት በአንዱ የንግድ ማህበር ውስጥ በንግድ አዋጅ ቁጥር 1156/11 አንቀጽ 495 መሠረት የሚመቸውን መርጦ የንግድህግ ባለሙያ አማክሮ በንግድ መዝገብ አስመዝግቦ ተገቢውን ግብር እና ክፍያ ለመንግስትና ለሚመለከተው አካል እየከፈለ በህግ ሊተዳደር ይገባል እንጂ ሰውን አለአግባብ በማታለል ወይም በማማለል በተለያየ ፕላትፎርም በአሳች ስም በመጠቀም ሰወች እንዲገቡ በማድረግ አላግባብ ገንዘባቸው እንዲዘረፍ እድል መክፈት፣ ማመቻቸት፣ መፈጸም ህገወጥ ተግባር ነው። ይህ ህገወጥድርጊት ስለመፈጸሙ የዚህ ድርጊት ሰለባ የሆኑ ሰወች በተደጋጋሚ መደወል ከጀመሩ ውለው ከርመዋል። ስለሆነም የንግድ እንቅስቃሴ ሊያደርጉ ፣ያደረጉ፣ወይም ሊያደርጉ በዝግጅት ላይ ያሉ በንግድ እና ሌሎች ህጎቻችን በሚደነግገው መሠረት በግል ንግድ ወይም በንግድ ማህበር በህጋዊ መንገድ ከመንቀሳቀስ በቀር ከዚህ ውጭ የሚያደርጉት ንግድ መሰል ድርጊት ህገወጥ ነው። 3. ተጠያቂነት 3.1 የወንጀል ተጠያቂነት ይህንን ድርጊት ያለ ህግ እውቅና ሎቶሪ ወይም እቁብ በማለት የሚያከናውኑ ሰወች በወንጀል በማታለል፣ በእምነት ማጉደል ወይም የህዝብን አደራ ገንዘብ ጋር በተያያዘ እንደ ወንጀል አፈጻጸሙ ክብደት የሚጠየቁበት ሲሆን ይህን በመረዳት ማህበረሰቡ ላይ ከሚያደርሱትም ጉዳት አንጻር ሊጠነቀቁ እና የሚመለከተው የፖሊስ እና የፍትህ አካላት ተገቢውን ክትትል እና እርምጃ ሊወስድ ያስፈልጋል። 3.2 የፍትሀብሄር ተጠያቂነት ይህን ህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ተጠያቂነት በወንጀል ብቻ ሳይሆን አላግባብ ህገወጥ አካሄድ በተከተለ መንገድ ከአባላት ገንዘብ በመሰብሰብ በተለያየ መንገድ ለብዝበዛ በመታለል የተዳረጉ ሰወች እነዚህ አታላዮች አላግባብ ገንዘባቸውን የወሰዱባቸውን በፍተሀብሔር ህግ ቁጥር 2162 መሠረት የተወሰደባቸውን ገንዘብ ለማስመለስ መጠየቅ ይችላሉ። 4. አጠቃላይ የዚህ ጽሁፍ አጠቃላይ ምክር እቁብ ወይም ሎተሪ በማለት ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ሳይኖራቸው ይህንንም ሳያጣሩ እዚህ ተግባር ውስጥ በመሳተፍ ለገንዘብ ብዝበዛ የምትዳረጉ በመጀመሪያ አስፈላጊ ህጋዊ ነጋዴ ወይም የንግድ ማህበር ስለመሆናቸው፣የንግድ ፍቃድ፣ምዘገባና እና ሌሎች ህጋዊ ስረአት ያሟሉ ስለመሆናቸው በደንብ ሊያጣሩ ይገባል። በዚህ ስራ መሠማራት የምትፈልጉም ህጋዊ የንግድ ፍቃድ እና ስረአቶችን በሟማላት ብትፈጽሙ ለእናንተም ሆነ ለማህበረሰቡ አስተማማኝ ዋስትና ሲሆን የሚመለከተው የፍትህ አካላትም ከዚህ አንጻር አስፈላጊውን የህግ ግንዛቤ መስጠትና ቁጥጥር ሊያደርግ ያስፈልጋል።

የ2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የህግ ትምህርት መውጫ ፈተና ላይ 98/100 ውጤት በማምጣት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ Tsegay Araya ከአዲግራት ዩንቨርስቲ ህግ ትምህርት
+1
የ2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ የህግ ትምህርት መውጫ ፈተና ላይ 98/100 ውጤት በማምጣት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው ተማሪ Tsegay Araya ከአዲግራት ዩንቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት Congratulations 🎉👏👏 https://t.me/Aid432

አንድ አሽከርካሪ ግልጽ የትራፊክ ደንብን በመተላለፍ ለእግረኛ ቅድሚያ ባለመስጠት በቸልተኝነት ሰው ገድሏል በሚል በወንጀል ህግ አንቀጽ 543(3)ስር ጥፋተኛ ሊባል የሚችለው ግልፅ የሆነ የእግረኛ መተላለፊያ ምልክት ሲኖር ነው። ግልፅ የሆነ የእግረኛ መተላለፊያ ምልክት ከሌለ የሚጠየቀው በአንቀፅ 543(2) ነው:: # የሰበር መዝገብ መ/ቁ 230508 # ነሀሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም

ስለ ዐቃቤያነ ህግ የደመወዝ ጭማሬ (ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም =======///======= በአማራ ክልል የሚገኙ ዓቃቢያነ ህግ የፌደራል መንግስት ያደረገው ሀገራዊ የደመወዝ ማሻሻያ እስካሁን ተግባራዊ አልተደረገልንም ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል። " በአንድ የፍትህ ሥርአት ውስጥ ለዳኞች የደሞዝ ማሻሻያው ተተግብሮ ለዓቃቢያነ ህግ መቅረቱ አግባብ ያልሆነና በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጫና የሚያሳድር ጉዳይ ነው " - የክልሉ ፍትሕ ቢሮ በአማራ ክልል ውስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙ ዓቃቢያነ ህግ፣ የፌደራል መንግስት ያደረገው ሀገራዊ የደመወዝ ማሻሻያ እስካሁን ተግባራዊ እንዳልተደረገላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን ገልጸዋል። ዓቃቢያነ ህጉ፥ የ2018 በጀት ዓመት የደመወዝ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 1110/2018 እነሱንም የሚያካትት ቢሆንም፣ የበጀት ዓመቱ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ እስኪቀሩት ድረስ ምንም ዓይነት ጭማሪ እንዳልተደረገላቸው ገልጸዋል። የፌደራል ዓቃቢያነ ህግ የማሻሻያው ተጠቃሚ በሆኑበት ሁኔታ፣ የክልሉ ባለሙያዎች ተነጥለው መቅረታቸው አግባብ እንዳልሆነና አሳሳቢ የህልውና ጥያቄ በመሆኑ በአስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የባለሙያዎቹን ቅሬታ ይዞ የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ዋና ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽምን በስልክ አነጋግሯል። የክልሉ ፍትህ ቢሮ ዋና ኃላፊ በዝርዝር ምን አሉ ? የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ ሀገራዊ የደሞዝ ጭማሪው ከመታወጁ በፊት በክልሉ የዓቃቢያነ ህግ የደረጃ ማሻሻያ ተደርጎ እንደነበር አንስተዋል። " ከፌደራል የደሞዝ ጭማሪ መጥቷል ሲባል የክልሉ መንግስት ያደረገውን የደረጃ እድገት ማስተካከያን መነሻ ያደረገ ሪፖርት ለፌደራል መንግስት ልከናህ። ይሁን እንጂ ሀገራዊው የደሞዝ ስኬል ማሻሻያ ግን ለክልሉ ዓቃቢያነ ህግ እስካሁን አልተላከም። ለምንድነው እስካሁን ያልመጣው? የሚለው የኛም ጥያቄ ነው። የፌደራል ፍትህ ሚኒስቴሯን ሰብሳቢ ያደረገ ኮሚቴ ተቋቁሟል። የገንዘብ ሚኒስቴር እና ለሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለጉዳዩ መፍትሄ እንዲሰጡም ጥረት እየተደረገ ነው። የዳኞች የደሞዝ ማሻሻያ በቅርቡ በዚህ አንድ ወር ውስጥ ተግባራዊ ተደርጓል። በአንድ የፍትህ ስርዓት ውስጥ ለዳኞች የደሞዝ ማሻሻያው ተተግብሮ ለዓቃቢያነ ህግ መቅረቱ አግባብ ያልሆነና በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጫና የሚያሳድር ጉዳይ ነው። የእኛም አቋም ሀገራዊ ጭማሪው ለዓቃቤ ህግም መምጣት አለበት የሚል ነው " ሲሉ ነግረውናል። የዐቃቢያነ ህግ ጥያቄ የደሞዝ ጭማሪው እስከ ውዝፍ ክፍያው ይከፈለን የሚል መሆኑን ለኃላፊው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሀገራዊ የደሞዝ ማሸሻያው መመሪያ መስከረም ላይ እንደወጣ አስታውሰው እንደ አማራ ክልል ከመስከረም ጀምሮ ውዝፉም አብሮ ይሰጠን የሚል ጥያቄ ለፌደራል መቅረቡን አሳውቀዋል። በመጨረሻም የፌደራል መንግስት ውሳኔውን አሳልፎ በጀቱን ሲለቅ፣ የክልሉ ፍትህ ቢሮ የዚህን በጀት ዓመት ውዝፍ ክፍያ በቀጥታ ለባለሙያዎቹ ተደራሽ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን አቶ ብርሃኑ ጠቁመዋል። የጊዜ ጉዳይ እንጂ መፍትሄ ማግኘቱ የማይቀር መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፣ የፍትህ ሚኒስቴር ማኔጅመንትም በትናንትናው እለት በጉዳዩ ላይ ውይይት ማድረጉንና በቀጣይም ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር የሚደረገውን ንግግር ኮሚቴው አጥብቆ እንደሚከታተለው ተናግረዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም

የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ ወታደራዊ ፍትሕ ዳኞች ሥልጠና መስጠት ጀመረ አዲስ አበባ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓመቱ የአቅም ማጎልበ
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ ወታደራዊ ፍትሕ ዳኞች ሥልጠና መስጠት ጀመረ አዲስ አበባ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓመቱ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለመስጠት በያዘው ዕቅድ መሰረት፣ ለመከላከያ ወታደራዊ ፍትሕ ዳኞች በጥብቅና እና የክርክር ክህሎት፣ በዳኞች ሥነ-ምግባር፣ ከውል ውጭ ኃላፊነት እና በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁ. 3/2017 ላይ ያተኮረ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል። በስልጠናው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ዶ/ር ዘካርያስ ኤርኮላ ፣ ከመከላከያ ሰራዊት ጋር መስራት ሀገርን የማገልገል ትልቅ ክብር እንደሚሰጥ ገልጸው፣ ሰልጣኝ ዳኞች ሥልጠናውን በአግባቡ ወስደው ወደ ተግባር እንዲቀይሩት አሳስበዋል። ይህ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለ4 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ይሆናል። ================================= ምንጭ፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

እስካሁን ባለው የሐገር አቀፍ የሕግ መውጫ ፈተና ከፍተኛ ውጤቶች ✔️ Mustefa 97 Jigjiga University School of Law ✔️Habtamu Dibu  95 -Woldia University, Law school ✔️ Yonas 93 Woldia University School of Law ✔️ Meira Aliye 93 Haramaya University, Law School ✔️Mabrat mihale 93 Salale University School of Law ✔️ Ghion Molla 92 Woldia University School of Law ✔️ Amanu Raja 92 -Wolkite University, Law School በዩኒቨርስቲያቹ ከፍተኛ የሆነው ውጤት ስንት ነው? Inbox via @Hope2be1live እዚሁ post ላይ update የምናደርግ ይሆናል:

የጅማ ዩንቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ከፍተኛ ውጤት 96/100 ተማሪ Wada Dejene 👏👏👏

📢 Job Opportunity: Associate Attorney (Part-Time | Remote)
JOIN ABOUT-LAW Telegram- t.me/ethiolawblog Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-law
An internationally oriented legal and business advisory practice based in Addis Ababa, Ethiopia is seeking two qualified and analytical professionals for the position of Associate Attorney. Key Responsibilities • Legal research and drafting • Corporate and commercial advisory support • Regulatory and compliance analysis • Support in dispute resolution and documentation Requirements ✔️ LLB degree in Law from a recognized institution ✔️ Minimum CGPA of 3.4 or above ✔️ Excellent English language and research skills ✔️ Strong analytical, communication, and teamwork abilities ✔️ Ability to work independently in a fast-paced environment ✔️ Strong technology and business aptitude Position Details 📍 Remote (Part-Time) 📈 Potential for increased engagement based on performance and organizational needs Application Documents • Updated CV • Cover Letter • Academic Transcript (if available) • Portfolio or sample work (if applicable) 📧 Apply to: lexeuver.careers@gmail.com 📅 Deadline: 25 June 2026 Apply: https://ethiojobs.net/job/yYVwgeukHk-associate-attorney

📢 Job Opportunity: Associate Attorney (Part-Time | Remote)
JOIN ABOUT-LAW Telegram- t.me/ethiolawblog Facebook- https://m.facebook.com/aboutlawlegalservice LinkedIn- https://www.linkedin.com/company/aboutethiopian-law
An internationally oriented legal and business advisory practice based in Addis Ababa, Ethiopia is seeking two qualified and analytical professionals for the position of Associate Attorney. Key Responsibilities • Legal research and drafting • Corporate and commercial advisory support • Regulatory and compliance analysis • Support in dispute resolution and documentation Requirements ✔️ LLB degree in Law from a recognized institution ✔️ Minimum CGPA of 3.4 or above ✔️ Excellent English language and research skills ✔️ Strong analytical, communication, and teamwork abilities ✔️ Ability to work independently in a fast-paced environment ✔️ Strong technology and business aptitude Position Details 📍 Remote (Part-Time) 📈 Potential for increased engagement based on performance and organizational needs Application Documents • Updated CV • Cover Letter • Academic Transcript (if available) • Portfolio or sample work (if applicable) 📧 Apply to: lexeuver.careers@gmail.com 📅 Deadline: 25 June 2026 Apply: https://ethiojobs.net/job/yYVwgeukHk-associate-attorne

የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለማቋቋም ያስችላል *********** በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ይፋዊ የሕዝብ ውይይት እያካሄደ ነው። ይህ የማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ በፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ውስጥ በስፋት የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር እና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል። የአጥኚ ቡድኑ እና የሕጉ አርቃቂ ኮሚቴ ሰብሳቢ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ መሐመድ አህመድ አዋጁን ለማሻሻል ሰፊ ጥናት መደረጉን ጠቁመው፣ በጥናት ሂደቱም የበርካታ ሀገራትን ተሞክሮ በመነሻነት መመልከታቸውን በዝርዝር አብራርተዋል። ይህ አዲስ የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለማቋቋም፣ የፍርድ ቤቶችን የሥራ ተደራሽነት ይበልጥ ለማስፋት እና ራሱን የቻለ የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ እንዲኖር ለማድረግ እንደሚያስችል ተመላክቷል። በተጨማሪም በሪፖርቱ አቀራረብ ወቅት እንደተመለከተው፤ የጋብቻ፣ የፍቺ፣ የውርስ ማጣራትና የሀብት ክፍፍል ጉዳዮች በማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ውስጥ በግልጽ የተካተቱ ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወ/ሮ እፀገነት መንግሥቱ በበኩላቸው የማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ የኢትዮጵያን የፍትህ ሥርዓት በማሻሻል ረገድ እጅግ የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸው፣ አሁን እየተካሄደ ያለው የሕዝብ ውይይት መድረክም በረቂቅ አዋጁ ላይ ተጨማሪ ጠቃሚ ግብዓቶችን በስፋት ለማሰባሰብ እንደሚያግዝ አስታውቀዋል። በዚሁ የሕዝብ ውይይት መድረክ ላይ የተገኙ ልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ላይ ሊካተቱና ሊስተካከሉ ይገባል ያሏቸውን ገንቢ ሐሳቦች ለቋሚ ኮሚቴው አቅርበዋል። አሁን ለውይይት የቀረበው ይህ የማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ፣ ከ25 ዓመታት በላይ ረጅም ጊዜ ሳይሻሻል የቆየውን ነባሩን የፌደራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ሙሉ በሙሉ የሚተካ ይሆናል። በሞላ ዓለማየሁ

በጦርነት ጊዜ ዓለም ዓቀፍ ሕጎችንና የሰብአዊነት አጠባበቅ ስምምነቶችን ተቃዋሚ በሆነ መንገድ፡- • የተማረከውን፣ መሳሪያውን ለምርኮ ያስረከበውን ወይም በማናቸውም ዓይነት ለመከላከል የተነሳውን ወይም የመከላከል ተግባሩን የተወውን ጠላት መግደል ወይም ማቁሰል ወይም • የሙት አካል ያጎደለ ማጉደል ወይም • በጦር ሜዳ ላይ በአንድ የጠላት ቁስለኛ፣ በሽተኛ፣ ወይም ሬሳ ላይ ስርቆት መፈፀም ወይም ኃይልን ተጠቅሞ ገፈፋ መፈፀም ወይም ከነዚህ ተግባሮች አንዱን ለመፈፀም በማሰብ ቁስለኛውን፣ በሽተኛውን ወይም ሬሳውን መበርበር፣ መያዝ ወይም የኃይል ተግባር መፈፀም ወይም • ከእነዚህ ተግባራት አንዱ እንዲፈፀም ማዘዝ በጽኑ እስራት ወይም ወንጀሉ በጣም ከባድ በሆነ ጊዜ እድሜ ልክ ጽኑ እስራት ወይም በሞት ያስቀጣል (አንቀጽ 275)፡፡ በዓለም አቀፍ ሰብአዊ ድርጅቶች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች በዓለም ዓቀፍ ደረጃ እውቅና አግኝቶ ተግባራዊ እንዲደረግ ጥረት እየተደረገ ያለው ዓለም ዓቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነት ጥበቃ ከሚደረግላቸው መካከል ሰብአዊ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ይገኙበታል፡፡ የቀይ መስቀል፣ የቀይ ጨረቃ እና የመሳሰሉ ድርጅቶች በተለይም በጦርነትና በተፈጥሯዊ ክስተቶች ለሚደርሱ በሰብአዊነት ላይ የሚደርሱ ቀውሶችን ለመታደግ የሚሰሩ ዓለም ዓቀፍ ዕውቅና ያላቸው ድርጅቶች ናቸው፡፡ በመሆኑም አገራት በእነዚህ ድርጅቶችም ሆነ ሠራተኞቻቸው ተገቢውን የሕግ ጥበቃ እንዲያገኙ የሚያደርጉ ሲሆን የወንጀል ሕጋችንም ይህን ተልዕኮ ግምት ውስጥ ያስገባ ክልከላን አስቀምጧል፡፡ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 281 መሠረት በሰላም ጊዜ አስቦ በቀይ መስቀል ወይም እነዚህን በመሳሰሉ ሌሎች ሰብዓዊ ድርጅቶች ሠራተኞች፣ ወኪሎች ወይም ባልደረቦች ወይም በነዚሁ ድርጅቶች ጥበቃ ሥር በሚገኙ ሰዎች ላይ የፀብ ሥራ ወይም የኃይል ድርጊት መፈፀም፣ መዛት ወይም ማዋረድ ወይም የነዚህን ድርጅቶች ዕቃዎች፣ ግዙፍ ሥራዎች ወይም ማከማቸዎች ማፍረስ ወይም ጉዳት ማድረስ በቀላል እስራት፣ የተፈጸመው ወንጀል ከባድ በሆነ ጊዜ ከአምስት ዓመት ባልበለጠ ጽኑ እስራት ያስቀጣል፡፡ ወንጀሉ የተፈፀመው በጦርነት ጊዜ እንደሆነ ቅጣቱ ከአንድ ዓመት እስከ አምስት ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እስራት ይሆናል፡፡ ማጠቃለያ ከአስከፊነታቸው የተነሳ ዓለም ዓቀፍ ማሕበረሰብ ተስማምቶ ክልከላ ያደረገባቸው ዋና ዋና የወንጀል ድርጊቶች ከላይ የተመለከትናቸው ሲሆኑ እነዚህን ዓለም ዓቀፍ ሕጎች በመጣስ የሚፈፀሙ ወንጀሎች በብሔራዊ ሕጎችም ተጠያቂነት ሊያስከትሉ የሚችሉ በመሆኑ ይህን ማወቅና የወንጀል ደርጊቱን ከመፈፀም መቆጠብ ይገባል፡፡