Legal Aid
الذهاب إلى القناة على Telegram
⚖️ Legal Aid: Your essential hub for legal professionals and students! Stay updated on new laws, landmark judgments, vacancies, and key insights. Join us to empower your legal journey and connect with the community! 📚✨"
إظهار المزيد1 707
المشتركون
+324 ساعات
+297 أيام
+7130 أيام
أرشيف المشاركات
1 707
የNGAT ምዝገባ ዛሬ ቅዳሜ ሀምሌ 25/2018 ዓም ይጠናቀቃል።
የመመዝገቢያ Link https://ngat.ethernet.edu.et
ለምዝገባ የሚያስፈልጉ ነገሮች
👉ብሔራዊ የድጅታል መታወቂያ
👉የመመዝገቢያ 750 ብር
👉የሚሰራ(የምትጠቀሙበት) የEmail አካውንት
1 707
ሕጉን መፈለግና መተርጎም የፍርድ ቤት እንጂ የባለጉዳዩ ኃላፊነት አይደለም (Jura Novit Curia)
Written by Jura Legal Update
በሥነ-ሥርዓት ሕግ ውስጥ የክርክር ሂደቶችን ውጤታማና ፍትሐዊ የሚያደርገው ዋናው መሠረት በፍርድ ቤቱ እና በተከራካሪ ወገኖች መካከል ያለው ግልጽ የሥራ ክፍፍል ነው። አንዳንድ ጊዜ በክርክር ወቅት ተከራካሪ ወገኖች ያቀረቡትን አቤቱታ ወይም መከራከሪያ የሚደግፍ ሕግ አልጠቀሱም ወይም የተሳሳተ የሕግ ድንጋጌ አቅርበዋል በሚል ምክንያቶች የክርክሩ ይዘት በአግባቡ ሳይመረመር ውድቅ ሲደረግ ይስተዋላል።
ሆኖም ግን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው የሚሠራበትና በሕግ ሥርዓታችን ውስጥም መሠረት ያለው "ፍርድ ቤቱ ሕጉን ያውቃል" (Jura Novit Curia) የሚለው መርህ ይኸንን አሰራር በጽኑ ይሞግታል። በዚህ መርህ መሠረት፣ ባለጉዳዮች ለፍርድ ቤቱ የማቅረብ ግዴታ ያለባቸው ፍሬ-ነገር (Facts) እና ማስረጃዎችን ብቻ ሲሆን፣ አግባብነት ያለው ሕግ መኖሩን መፈለግ፣ መተርጎም እና መተግበር ግን የፍርድ ቤቱ የራሱ ኃላፊነት ነው።
የፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ቁጥር 222 (1) ከሀ እስከ ቀ ባሉት ንዑሳን አንቀጾች በክስ አቤቱታ ላይ መካተት ያለባቸውን ዝርዝር ነገሮች ይደነግጋል። ከነዚህም መካከል የፍርድ ቤቱ ሥልጣን፣ የከሳሽና የተከሳሽ ማንነትና አድራሻ፣ የክሱ ምክንያት የሆኑት ነገሮችና የተፈጠሩበት ጊዜና ቦታ (የፍሬ-ነገር ዝርዝር)፣ እንዲሁም ለክሱ ምክንያት በሆነው ነገር ውስጥ የተከሳሽ አግባብነት ይገኙበታል።
በዚህ የሕግ አንቀጽ ውስጥ ትልቅ ትኩረት የሚሰጠው ነጥብ ከሳሽ ክሱን በሚያቀርብበት ጊዜ ክሱን የሚደግፍ የሕግ አንቀጽ ወይም የሕግ መከራከሪያ የማቅረብ ግዴታ እንዳልተጣለበት ነው። ሕጉ ባለጉዳዩ የክርክሩን መሠረት ወይም ፍሬ-ነገር (Facts) ብቻ እንዲያቀርብ ያስገድዳል፤ እንጂ አግባብነት ያለውን ሕግ ጠቅሶ እንዲከራከር አይጠይቅም። ይህ ድንጋጌ የJura Novit Curia (ፍርድ ቤቱ ሕጉን ያውቃል) መርህ ቀጥተኛ መገለጫ ነው። ባለጉዳዩ ፍሬ-ነገሩን የማቅረብ ኃላፊነት እንዳለበት ሁሉ፣ በቁጥር 222 መሠረት የቀረበውን ፍሬ-ነገር አይቶ አግባብነት ያለውን ሕግ ፈልጎ የማዛመድ እና የመተግበር ድርሻ የፍርድ ቤቱ ነው።
ይህ መርህ በከሳሽ ላይ ብቻ ሳይሆን በተከሳሽ የመከላከያ መልስ ላይም በተመሳሳይ ደረጃ ይተገበራል። በፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ቁጥር 234 (1) መሠረት፣ ተከሳሽ በመከላከል መልሱ ውስጥ ሊያካተታቸው የሚገቡት የክሱን ፍሬ-ነገሮች ማስተባበያ፣ የመቃወሚያ መሠረቶችን (ለምሳሌ የዕርቅ፣ የይርጋ ወይም የችሎት ማጣት መከራከሪያዎችን) እና ለመከላከያው መሠረት የሆኑትን የፍሬ-ነገር ዝርዝሮች እንጂ መከላከያውን የሚደግፉ የሕግ አንቀጾችን መጥቀስ ግዴታ አይደለም።
ተከሳሹ የቀረበበትን ክስ የሚከላከልበትን ፍሬ-ነገር እና ማስረጃ ማቅረብ እንጂ፣ የመከላከያ መከራከሪያውን የሚደግፍ የሕግ አንቀፅ የመጥቀስ ግዴታ የለበትም። ተከሳሹ የሕግ ድንጋጌዎችን ባይጠቅስ እንኳ፣ ባቀረበው የመከላከል ፍሬ-ነገር መሠረት አግባብነት ያለውና ተከሳሹን ሊታደግ የሚችል ሕግ የመፈለግ፣ የመተርጎም እና የመተግበር ኃላፊነቱ አሁንም የፍርድ ቤቱ የራሱ ነው። ተከሳሽ "መከላከያውን የሚደግፍ የሕግ አንቀጽ አልጠቀሰም" በሚል ብቻ መከላከያው ውድቅ ሊደረግበት አይገባም።
ከዚህም በላይ፣ የፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 3/1987 አንቀጽ 2 ንዑስ ቁጥር 3 በግልጽ እንደሚያስቀምጠው "ማንኛውም የፌዴራል ወይም የክልል ሕግ አውጪ፣ አስፈጻሚ እና ተርጓሚ እንዲሁም ማንኛውም የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ የወጣውን ሕግ የመቀበል ግዴታ አለበት" ይላል። የእንግሊዝኛው ትርጉም ደግሞ በግልጽ "shall take judicial notice of Laws published in the Federal Negarit Gazeta" በማለት ይገልጸዋል።
ይህ ድንጋጌ በነጋሪት ጋዜጣ ታትመው የወጡ ሕጎች በሙሉ በሕግ ተርጓሚው አካል (በፍርድ ቤቱ) ዘንድ አስቀድመው እንደሚታወቁ (Judicial Notice) ይገመታል። በመሆኑም ተከራካሪ ወገኖች በነጋሪት ጋዜጣ የታወጀን ሕግ በማስረጃነት ማቅረብ ወይም "ሕጉ አለ" ብለው ማስረዳት አይጠበቅባቸውም። ፍርድ ቤቱ በራሱ ተነሳሽነት በነጋሪት ጋዜጣ የወጡትን ሕጎች አውቆና ተረድቶ በክርክሩ ላይ የመተግበር ግዴታ አለበት።
ሲጠቃለል፣ የፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ቁጥር 222 እና 234 ተከራካሪ ወገኖች ፍሬ-ነገሩን እና ማስረጃ ብቻ የማቅረብ ኃላፊነት እንዳለባቸው ሲደነግጉ፣ የአዋጅ ቁጥር 3/1987 አንቀጽ 2 (3) ደግሞ ፍርድ ቤቱ በነጋሪት ጋዜጣ የወጡ ሕጎችን በJudicial Notice ደረጃ አውቆ የመተግበር ግዴታ እንዳለበት ያረጋግጣል። እነዚህ ድንጋጌዎች ተጣጥመው ሲተገበሩ ተከራካሪ ወገኖች "የሕግ አንቀጽ አልጠቀሱም" ወይም "ክርክሩን የሚደግፍ ሕግ አላቀረቡም" በሚል ምክንያት አቤቱታን ወይም ክርክርን ውድቅ ማድረግ ሕጋዊ መሠረት የሌለው እና የሕጉን ዓላማ የሚቃረን መሆኑን በግልጽ ያሳያሉ።
1 707
እንሆ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አዲስ ዉሳኔ !
በወንጀል የተከሰሰ ማንኛውም ሰው ድርጊቱን ስለመፈጸሙ በዐቃቤ ሕግ በኩል "ከምክንያታዊ ጥርጣሬ በላይ" (beyond reasonable doubt) ካልተረጋገጠ በቀር ጥፋተኛ ተብሎ የቅጣት ውሳኔ ሊሰጥበት የማይገባ መሆኑን እና ይህ ሳይረጋገጥ የሚሰጥ የጥፋተኝነትና የቅጣት ውሳኔ ሕገ-መንግሥታዊ እንዳልሆነ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 20 (3) ሥር ከተረጋገጠው "ንጹህ ሆኖ የመገመት መብት" አንጻር የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስገዳጅ የሕገ-መንግሥት ትርጉም ውሳኔ ሰጥቷል። በተጨማሪም ተከሳሽ ጥፋተኛ አለመሆኑን በተራው ለማስረዳት በዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ላይ ምክንያታዊ ጥርጣሬን (reasonable doubt) መፍጠር በቂው እንደሆነ ተወስኗል።
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ፣ መዝገብ ቁጥር 151፣ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. የተሰጠ ውሳኔ
1 707
For Fresh graduates🎴Transsion Manufacturing PLC🎴
▪️Job Position-Junior Lawyer
Education:Bachelor’s Degree (LL.B) in Law from a recognized university.
▪️Find More Details here
💧💧💧💧💧
https://elelanajobs.com/2026/07/30/transsion-manufacturing-plc-9/?utm_source=telegram&utm_medium=mobile_app
1 707
ጃንቦ Vs ጀንቦሮ
#Ethiopia | "ጀንቦሮ ራል እስቴት" (Jenboro Realestate) የንግድ ስሙን በሕጋዊ መንገድ ለማስመዝገብ ለኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን ማመልከቻ አቀረበ።
ከጃምቦ ሪል እስቴት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል!
የጃምቦ ሪል እስቴት የድርጅቱ ኃላፊዎች እንደገለጹት፤ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የንግድና ኢንቨስትመንት ችሎት ተይዞ በነበረው ክስ ላይ ገና ውሳኔ ባልተሰጠበት ሁኔታ፣ "ጀንቦሮ ራል እስቴት" በሚል ተመሳሳይ ስም ድርጅቱን ለመመዝገብ ጥረት ማድረጉን ተክትሎ፣ በ03/07/2018 ዓ.ም ለባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ጥያቄ በማቅረብ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል።
የብራንድ ጥበቃ እና የሕግ አውድ
በዓለም አቀፍ የአእምሯዊ ንብረት ሕግ (WIPO - World Intellectual Property Organization) እና በኢትዮጵያ የንግድ ምልክት ምዝገባና ጥበቃ አዋጅ መሠረት፣ የአንድ ንግድ ስም ወይም የብራንድ መለያ ተመሳሳይነት ያላቸውን ስሞች በመጠቀም ደንበኞችን ማደናገር (Consumer Confusion) እና አላስፈላጊ ውድድር መፍጠር የተከለከለ ነው።
የጃንቦ ራል ስቴት የሥራ ኃላፊዎች እንደሚሉት ከሆነ፡
* ድርጅቱ ስሙን በሕጋዊ መንገድ ያስመዘገበውና የመጠቀሚያ ፈቃድ ያገኘው በ2007 ዓ.ም እና በ 2011 ዓ.ም ባደረጋቸው ተከታታይ ምዝገባዎች መሆኑን፤
* የአሁኑ የስም መመሳሰልና ያልተፈቀደ አጠቃቀም በደንበኞችና በማህበረሰቡ ዘንድ ሰፊ ብዥታን በመፍጠሩ ምክንያት የሕግ ጥበቃው አስፈላጊ መሆኑን፤
* የንግድ ስማቸው ያለአግባብ ተመሳሳይ ስም ባላቸው አካላት እንዳይወሰድና የንግድ ስማቸውን ለማስጠበቅ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
ተመሳሳይ አሰራሮችና የዓለም አቀፍ የንግድ ውድድር ደንቦች እንደሚያስረዱት፣ የንግድ ምልክቶች መመሳሰል (Trade Name Infringement) በገበያው ላይ የሚፈጥረውን ብዥታ ለማስቀረት ተቋማት የፈጠራና የብራንድ መብቶቻቸውን በሕግ ማስከበር እንዳለባቸው ያሳስባሉ።
ውሳኔ በተሰጠበት ሁኔታ ተከሳሽ ድርጅት በተመሳሳይ አቋም ድርጅቱን ጀምቦሮ ሪል እስቴት በሚል ስያሜ ለማስመዝገብ ጥያቄ ማቅረቡን ጉዳዩን የበለጠ ለማወሳሰብ የሚደረግ ጥረት በመሆኑ ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ተቋውሟቸውን በማሰማት ዝርዝር ማስረጃዎችን ለማቅረብ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን አሳውቀዋል።
የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣንም የቀረበውን የተቃውሞ አቤቱታ እና የስም ምዝገባ ጥያቄ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
1 707
ሪ ሕገ መንግሥት ቀዳሚው ሲሆን በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 28(1) መሠረት ኢትዮጵያ ባፀደቀቻቸው ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶችና በሌሎች የአገራችን ሕጎች የሰው ልጅ ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች ተብለው የተወሰኑ ወንጀሎች፣ የሰው ዘር የማጥፋት፣ ያለፍርድ የሞት ቅጣት እርምጃ የመውሰድ፣ በአስገዳጅ ሰውን የመሰወር ወይም የኢሰብዓዊ ድብደባ ድርጊቶችን በፈፀሙ ሰዎች ላይ ክስ ማቅረብ በይርጋ አይታገድም።
ማጠቃለያ
የወንጀል ክስ በአንድ በኩል ተጎጂዎች ፍትሕ የሚያገኙበት የሕግ ሂደት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በወንጀል የተጠረጠሩ ወይንም የተከሰሱ ግለሰቦች ነፃነት በሕግ የሚገደብበት ነው። በዚሁ መሠረት የወንጀል ክስ መመስረቻ ጊዜ ገደብ በሕግ ወስኖ ማስቀመት በሁለቱ ተፃራሪ መብቶች መካከል ሚዛን ለመጠበቅ የሚያስችል ነው። ስለሆነም ማንኛውም ክስ በሕግ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ሊቀርብ ይገባል፡፡
በንቃተ ሕግና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
1 707
የወንጀል ክስ ይርጋ በኢትዮጵያ
********************
መግቢያ
ወንጀል ፈፃሚዎች ለፈፀሙት ጥፋት በሕግ ፊት መጠየቃቸውና ተገቢውን ቅጣት መቀበላቸው ተገቢና አስፈላጊም ነው፡፡ ይህም በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ አንድ እንደተመለከተው በወንጀል ሕጉ መሰረት ወንጀል የተደረጉ ድርጊቶች እና የሚያስከትሉትን ቅጣት በመደንገግ ሰዎች ወንጀል ከመፈፀም እንዲቆጠቡ አሰቀድሞ ቅድመ-ማስጠንቀቂያ የሚሰጥ ቢሆንም ቅድመ-ማስጠንቀቂዎች በቂ ባልሆኑ ጊዜ ወንጀል ፈፃሚዎች ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ከመፈፀም እንዲታቀቡና ለሌሎችም ማስተማሪያ እንዲሆኑ ማድረግን ግቡ ያደረገ ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ግን በወንጀል ሕጉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ክስ ሊመሠረት እና አጥፊዎችን ለሕግ ማቅረብ የሚገባ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን ክሱ በይርጋ የሚታገድ ይሆናል፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ የወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት፣ በሕግ የተመለከተውን የክስ ይርጋ ዘመን እናአቆጣጠር እንዲሁም የክስ ይርጋ ዘመን መቋረጥና መታገድ በአጭሩ እንመለከታለን፡፡
የወንጀል ክስ ይርጋ ምንነት
የወንጀል ሕጉ የወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት በተመለከተ ቀጥተኛ ትርጓሜ ባይሰጥም ከወንጀል ሕግ አንቀጽ 217 በመነሳት የወንጀል ክስ ይርጋ ማለት በማናቸውም ወንጀል ጉዳይ በግል አቤቱታ ወይም በወንጀል ክስ አቅራቢነት ጉዳዩ በዳኝነት ከመታየት የሚታገድበት በሕግ የተመለከተ ጊዜ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
የመደበኛ ክስ ይርጋ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 217 መደበኛ የክስ ማቅረቢያ ጊዜን የደነገገ ሲሆን
• የሞት ፍርድ ወይም የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አምስት ዓመት
• ከአስር ዓመት በላይ እስከ ሃያ አምስት ዓመት ለመድረስ የሚችሉ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አመት
• ከአምስት ዓመት በላይ እስከ አስር ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስራ አምስት አመት
• ከአምስት አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስር ዓመት
• ከአንድ ዓመት በላይ በቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአምስት ዓመት
• እስከ አንድ ዓመት ቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወይም በመቀጮ ብቻ ለሚያስቀጣ ወንጀል በሦስት ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ ክሱ በይርጋ ይታገዳል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ ተደራራቢ ወንጀሎች ተፈጽመው ሲገኙ የወንጀሎቹ ከፍተኛ ቅጣቶች ተመሳሳይ በሚሆኑበት ጊዜ የአንዱ ወንጀል የክስ ማቅረብያ የይርጋ ዘመን በሁለቱም ወንጀሎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆንና የወንጀሎቹ ከፍተኛ ቅጣቶች የተለያዩ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ከሁሉም ከባድ የሆነው ወንጀል የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን በሌሎች ወንጀሎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 217(2) ይደነግጋል፡፡
በግል አቤቱታ አቅራቢነት የሚያስቀጡ ወንጀሎች ይርጋ
በወንጀል ሕጉ ልዩ ክፍል ወይም በሌላ ማሟያ የወንጀል ሕግ በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ እንደሚያስቀጡ የተደነገጉ ወንጀሎች የግል ተበዳዩ ወይም ሕጋዊ ወኪሉ የግል አቤቱታ ካላቀረበ በስተቀር ክስ እንደማይመሰረት በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 212 ተደንግጓል ፡፡ ለአንብነትም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 560 የእጅ እልፊት ወንጀል በግል አቤቱታ ሲቀርብ የሚስቀጣ ወንጀል መሆኑ ተደንግጓል፡፡ መሰል በግል አቤቱታ የሚቀርቡ ወንጀሎች የተፈፀመበት የግል ተበዳይ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 213 መሠረት አቤቱታውን ማቅረብ የሚጠበቅበት ሲሆን የእነዚህ በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ የሚያስቀጡ ወንጀሎች የክስ ይርጋ ዘመን ሁለት አመት እንደሆነ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 218 ተደንግጓል፡፡
ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን
በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 222 ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን የተደነገገ ሲሆን በማናቸውም ምክንያት ከላይ የተመለከትነው መደበኛ የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን እጥፍ ጊዜ ካለፈ ወይም በግል አቤቱታ የሚያስቀጡ ወንጀሎች ሲሆኑ ደግሞ ከላይ ከተመለከትነው በግል አቤቱታ የሚያስቀጡ ወንጀሎችን የይርጋ ዘመን በግማሽ የሚበልጥ ጊዜ ካለፈ በወንጀሎቹ ላይ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ቀሪ ይሆናል፡፡
የክስ ይርጋ አቆጣጠር
በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 219 መሠረት የክስ የይርጋ ዘመን የሚታሰበው የቅጣት ማክበጃ ወይም ማቅለያ ሁኔታዎች ግምት ውስጥ ሳይገቡ በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሠረት በማድረግ ሲሆን የተፈፀመው ወንጀል በተለዋጭ ወይም በተደራራቢ ተፈፃሚነት በሚኖራቸውም ቅጣቶች የሚያስቀጣ ሲሆን የይርጋ ዘመኑ የሚታሰበው ከሁሉም ከባድ ለሆነው ወንጀል በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሠረት በማድረግ ይሆናል፡፡
የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረውም ጥፋተኛው የወንጀል ድርጊቱን ከፈጸመበት ቀን አንስቶ ሲሆን የወንጀል ድርጊቱ እየተደጋገመ የተፈፀመ ከሆነም የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የመጨረሻው የወንጀል ድርጊት ከተፈፀመበት ቀን አንስቶ ነው፡፡ የወንጀል ድርጊቱ ለረጅም ጊዜ ሲፈፀም የቆየ ከሆነ ደግሞ የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የወንጀል ድርጊቱ ካቆመበት ቀን ጀምሮ ይሆናል፡፡
የክስ ይርጋ መታገድ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 220 የወንጀል ክስ ይርጋ የሚታገድበትን ሁኔታ የደነገገ ሲሆን ይኸውም
በሕግ ወይም በፍሬ ነገር ክሱ እንዳይጀመር ወይም እንዳይቀጥል የሚያግድ መሰናክል ካለ መሰናክሉ እስካለ ድረስ
ክስ ቀርቦ ነገሩ በዳኝነት በመታየት ላይ ከሆነ ወይም በሌላ ችሎት የቀረበ ክስ ሳይፈፀም ተከሳሹ በተከሰሰበት የወንጀል ክስ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ የማይገባ በሆነ ጊዜ
የይርጋ ዘመኑ ታግዶ ይቆያል፡፡ መታገዱን ያስከተለው መሰናክል ሲወገድ ግን የይርጋ ዘመኑ ወዲያውኑ መቆጠር ይጀምራል፡፡
የይርጋ ዘመን መቋረጥ
የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 221 እንደሚያመለክተው ከወንጀሉ ወይም ከወንጀለኞቹ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ምርመራ እንዲካሄድ፣ ብርበራ እንዲደረግ፣ መጥሪያ እንዲሰጥ ወይም ክስ እንዲቀርብ የሚሰጥ ትዕዛዝ፣ የሚፈፀም ድርጊት ወይም የሚሰጥ ውሳኔ የይርጋ ዘመኑን መቆጠር ያቋርጣል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ የይርጋ ዘመን እንደገና እንደ አዲስ መቆጠር ይጀምራል፡፡ በድንጋጌው መሠረት የይርጋ ዘመኑ መቋረጥ ፍፁም የሆነ ውጤት የሚኖረው ሲሆን በወንጀሉ ተካፋይ መሆናቸው ለታወቀውም ሆነ ላልታወቀው ሁሉ መቋረጡ ይፀናባቸዋል፡፡ ይህ ማለት የወንጀል ተካፋይ መሆናቸው ወንጀሉ በተከሰተበት ጊዜ ያልታወቁ ሰዎች ያኔ ባለመታወቃቸው ምክንያት የይረጋ መቋረጥ አስመልክቶ ሊኖር የሚችል ልዩነት እንደሌለ መረዳት ይቻላል፡፡
በይርጋ የማይታገዱ ጉዳዮች
በመርህ ደረጃ የወንጀል ድርጊቶች ከተፈፀሙ በኋላ ክስ ለማቅረብ የሚቻልበት የጊዜ ገደብ በግልፅ ሰፍሮ ያለ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ በሌላ ሕግ ከተደነገገ በይርጋ የማይታገዱ ወንጀሎች እንዳሉ ከወንጀል ሕጉ እንቀጽ 216(1) መገንዘብ ይቻላል፡፡ ከዚህ አንፃር የኢ.ፌ.ድ.
1 707
አዲስ ኮንዶሚኒየም ተከራይቼአለሁ መጥተሽ እይልኝ በማለት በምቀኝነትና በአደገኛ ጓደኛዋ ሴራ ህይወቷን የተነጠቀችው ነፍስ
የቅዱሳን ይርጋለም አሰቃቂ የግድያ ሴራና የፖሊስ የምርመራ ውጤት፦
የ2026 ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ተወዳዳሪ የሩታ ይርጋለም ታላቅ እህት ቅዱሳን ይርጋለም በተፈጸመባት እጅግ አሰቃቂ የእገታና የግድያ ወንጀል ሕይወቷ ማለፉ የመላውን ህዝብና የማህበረሰብ ልብ የሰበረ ክስተት ሆኗል።
በሞደሊንግ ዓለም ስኬትን ለማስመዝገብ በምትተጋው ቅዱሳን ይርጋለም እና ከትምህርት ቤት ጀምሮ በቅርብ የምታውቃት ጓደኛዋ ቅድስት ሙሉቀን መካከል የጠነከረ ወዳጅነት የነበረ ቢሆንም፣ ከጀርባው ግን ምቀኝነትና አደገኛ ሴራ ተሸሽጎ ነበር።
አርብ ዕለት ቅድስት ሙሉቀን ላለፉት ጥቂት ጊዜያት ያልተገናኘችውን ቅዱሳንን በስልክ በመደወል "አዲስ ኮንዶሚኒየም ተከራይቼአለሁ፤ መጥተሽ ቤቴን እዪልኝ፤ ደግሞም የሚያገናኝሽ አዲስ የሥራ ዕድል አለ" በማለት የደስታና የጽኑ ወዳጅነት በሚመስል መንፈስ ጥሪ አቀረበችላት።
ቅዱሳን በጓደኛዋ ላይ አንዳችም ክፋት ሳትጠረጥር ሜክሲኮ አካባቢ ተገናኝተው አብረው ወደ ኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም አመሩ።
ኮዬ ፈጬ በሚገኘው አዲስ ኮንዶሚኒየም ደጃፍ ደርሰው ወደ ቤት እንደገቡ፣ ቀድሞ ተደብቆ ይኖር የነበረው የቅድስት ፍቅረኛ ደስአለኝ፣ ቅዱሳን ድምፅ እንኳ አውጥታ እንዳትጮህ አፍኖ በማሰር እገታውን ፈጸመ።
አጋቾቹ ወዲያውኑ ለሟች ቤተሰቦች በመደወል የ2 ሚሊዮን ብር ቤዛ እንዲከፈላቸው ጠየቁ። የቤተሰብ ልብ በጭንቀትና በድንጋጤ ተሞልቶ....
የገንዘብ ድርድርና ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት፣ አጋቾቹ ቅዱሳን በቅርብ የምታውቃቸው በመሆኑ ነፃ ብትወጣ የፈጸሙትን ምስጢር አሳልፋ እንደምትሰጣቸው ተገነዘቡ። በዚህም ፍርሃትና ጭካኔ በተሞላበት ውሳኔ፣ በዚያው አርብ ዕለት የቅዱሳንን ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ አጠፉት።
አስክሬኗንም ማንም እንዳያገኘው በማሰብ እዚያው አካባቢ በተከራዩት ሌላ ተጨማሪ ኮንዶሚኒየም ውስጥ ደበቁት።ሆኖም አጋቾቹ የፈጸሙት ግፍ በጨለማ ሊቀበር አልቻለም። የፖሊስ አባላት ባደረገው ፈጣንና የተቀናጀ ክትትል፡
1. ዋናኛዋ ተጠርጣሪ ቅድስት ሙሉቀን በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በቁጥጥር ስር ዋለች።
2.ተባባሪው ደስ አለኝ ደግሞ ሁኔታዎች ሲከፉበት ለማምለጥ ሞክሮ በአዳማ ከተማ ተደብቆ እያለ በፖሊስ ተያዘ።
በአጠቃላይ ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ 8 ሰዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ ዋና ዋናዎቹ ተጠርጣሪዎች ወንጀሉን መፈጸማቸውን አምነው ድርጊቱን እንዴት እንደፈጸሙት በቦታው ተገኝተው ለፖሊስ አሳይተዋል።
ይህ አሰቃቂ ድርጊት መላውን ማህበረሰብ ያስቆጣና ያስዘነዘነ ሲሆን፣ እህቷ ሩታ ይርጋለም በልብ ስብራት ሆና፡
"እግዚአብሔር የወደደውን አደረገ፤ ከጠላቴ እኔ እጠነቀቃለሁ ከወዳጄ አንተ ጠብቀኝ..." በማለት ያስፈረመችው መልእክት የዚህን አሳዛኝ ሁኔታ ጥልቀት የሚያሳይ ሆኗል።
ለቤተሰቦቿ ለወዳጅ ዘመዶቿ መፅናናትን እንመኛለን ። ነብሷን ይማርልን ! #RIP
ዘገባው የዘሀበሻ ነው::
1 707
በወንጀል ሕጋችን፦ ስርቆት፣ ከባድ ስርቆት፣ ውንብድና፣ ዝርፊያ እና መሸሸግ ልዩነታቸው ምንድን ነው?
ብዙዎቻችን እነዚህን የንብረት ወንጀሎች በማደባለቅ እንጠቀማቸዋለን። ነገር ግን በኢትዮጵያ ወንጀል ሕግ መሠረት እያንዳንዳቸው የተለያየ የድርጊት ዓይነት፣ የቅጣት መጠን እና ሕጋዊ መለኪያ አላቸው።
ልዩነታቸውን በጥቅሉና በግልጽ እንደሚከተለው እንመልከት፦
1️⃣ ስርቆት (Simple Theft)
የሌላውን ሰው የሚንቀሳቀስ ንብረት ባለቤቱ ሳይያውቅ ወይም ሳይፈቅድ፣ ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ለማድረግ በማሰብ በደባ ወይም በስርቆት መውሰድ ነው።
ምንም ዓይነት ኃይል/ዛቻ (Violence) የሌለበት፣ በስውርና በደባ የሚፈጸም ነው።
2️⃣ ከባድ ስርቆት (Aggravated Theft)
ሕጋዊ ትርጉም፦ ስርቆቱ የተፈጸመበት ሁኔታ፣ ቦታ፣ ወይም መንገድ ወንጀሉን ከባድ የሚያደርገው ሲሆን ነው።
ዋና መለያዎች፦
# በሌሊት፣ በቡድን፣ ወይም መሣሪያ/መሳሪያ መሰል ነገሮችን በመያዝ ከተፈጸመ፤
# መቆለፊያ በመስበር፣ በር/መስኮት በመስበር ወይም የመግቢያ ቁልፍ አስመስሎ በመስራት ከተፈጸመ፤
# በእምነት ማጉደል ወይም በሥራ አጋጣሚ (ለምሳሌ፦ ዘበኛ፣ አጋዥ) ከተፈጸመ።
3️⃣ ዝርፊያ (Robbery)
የሌላውን ሰው ንብረት ለመውሰድ ሲባል ኃይልን (Force) መጠቀም ወይም በሕይወትና አካል ላይ አደጋ ለማድረስ ማስፈራራት/መዛተት ነው።
ከስርቆት የሚለየው ቀጥተኛ ኃይል፣ ጥቃት ወይም የዛቻ ድርጊት (Violence or Threat) የሚታከልበት በመሆኑ ነው።
4️⃣ ውንብድና (Brigandage / Banditry)
በቡድን በመደራጀት ወይም መሣሪያ በመታጠቅ መንገድ በመዝጋት፣ በሕዝብ ወይም በግል ንብረት ላይ ጥቃት በማድረስ የሚፈጸም እጅግ ከባድ የዝርፊያና የሽብር ድርጊት ነው።
በታጠቀ ቡድን የሚፈጸም፣ የህዝብን ሰላምና ጸጥታ በከፍተኛ ደረጃ የሚያናጋ እና ከግል ንብረት አልፎ የማኅበረሰብ ደህንነት ላይ አደጋ የሚደቅን ነው።
5️⃣ የስርቆት ዕቃ መሸሸግ (Receiving or Storing Stolen Property)
አንድ ንብረት በስርቆት፣ በዝርፊያ ወይም በወንጀል የተገኘ መሆኑን እያወቁ ወይም መጠራጠር ሲገባው ንብረቱን መግዛት፣ መረከብ፣ ማስቀመጥ ወይም መሸሸግ ነው።
ግለሰቡ በስርቆቱ ድርጊት ላይ ቀጥታ ባይሳተፍም፣ በወንጀል የተገኘውን ንብረት በስውር በመያዙ ወይም በመግዛቱ ተጠያቂ ይሆናል።
6️⃣ ከባድ መሸሸግ (Aggravated Storing/Concealment)
የሌላውን ሰው ወንጀል መሸሸግ ወይም የተሰረቀ ንብረት መረከብ በከባድ ሁኔታ ሲፈጸም ነው።
ዋና መለያዎች፦
#ድርጊቱን የተለመደ ሙያ ወይም ንግድ (Habitual Business) አድርጎ ሲይዘው፤
# በከባድ ወንጀል (ለምሳሌ፦ በዝርፊያ ወይም በውንብድና) የተገኘ ንብረት መሆኑን እያወቁ ሲሸሽጉ፤
# በስፋትና በከፍተኛ ደረጃ የተደራጀ የመሸሸግ ድርጊት ሲሆን።
“ህግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም!”
የወንጀል ሕጋችን የንብረት መብትን ለማስከበርና የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ለእያንዳንዱ ድርጊት እንደ ከባድነቱ መጠን የተለያየ የሕግ ተጠያቂነትና የቅጣት እርከን አስቀምጧል።
👉 ይህን የሕግ ግንዛቤ ላይክ፣ ሼር (Share) በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ ያዳርሱ
1 707
የጎንደር ዩኒቨርስቲ የህግ ተማሪዎች በ በጀርመን ሀገር በሚካሄደው አለምአቀፉ የኑረምበርግ ምስለ ችሎት ውድድር (Nuremburg Moot Court) ኢትዮጵያን በመወከል በመወዳደር ላይ ይገኛሉ።
መልካም ዕድል እንመኛለን!
1 707
በክረምት ለ2 ወራት በከፊል የሚዘጉና ፈጽሞ የማይዘጉ ፍ/ቤቶች ዝርዝር
I) በከፊል የሚዘጉ:-
1. የፌደራል ፍ/ቤቶች:-
-ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም - መስከረም 30/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ::
[በፌደራል ፍ/ቤቶች ዐዋጅ ቁጥር 1234/2012 አንቀጽ 38(2) መሠረት]
2. የኦሮሚያ ክልል:-
-ከሐምሌ 21/2018 ዓ.ም - መስከረም 20/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ::
[በክልሉ ፍ/ቤቶች ዐዋጅ ቁ.216/2011 አ. 44(1)+በደንብ ቁ.7/2012 አ. 80(1) መሠረት]
3. የአማራ ክልል:-
-ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም - መስከረም 30/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ::
[በክልሉ ፍ/ቤቶች ዐዋጅ ቁ. 282/2014 አ.41 መሠረት]
4. የትግራይ ክልል:-
-ከሐምሌ 7/2018-መስከረም 7/2019
5. የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል:-
-ከሐምሌ 21/2018 ዓ.ም - መስከረም 20/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ::
6. የሲዳማ ክልል:-
-ከሐምሌ 21/2018 ዓ.ም - መስከረም 21/2019 ኦዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ::]
[በክልሉ ዐዋጅ ቁ.40/2016 አ.52(2)]
7. የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል:-
-ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም -መስከረም 30/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ::
[በዐዋጅ ቁ.6/2016 አ. 59]
8. የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል:-
-ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም - መስከረም 30/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ::
[በክልሉ የፍ/ቤቶች ዐዋጅ ቁ. 1/2016 አ. 59(2)]
9. የሸሪዓ ፍ/ቤቶች:-
-ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም - መስከረም 30/2019 ዓ.ም
(የኒካ፣ “ጋብቻ” እና ቀለብ ጉዳዮችን ከማስተናገድ በስተቀር) ዝግ ናቸው::
10. የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል:-
-ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም - መስከረም 30/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ::
Il) የማይዘጉ
1. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍ/ቤቶች:-
-አይዘጉም—መደበኛ ሥራቸውን ይቀጥላሉ!😁
IIl) መረጃ ያልተገኘ
1. የአፋር ክልል :-NA
2. የሐረሪ ክልልል :-NA
3. የሱማሌ ክልል :-NA
4. የጋምቤላ ክልል:- NA
5. የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፍ/ቤት
6. የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን: NA
7. የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ ይግባኝ ሰሚ አስተዳደራዊ ፍ/ቤት: NA
Via: Ethiopian Law
1 707
ቅሬታ ❗️❗️ ቅሬታ ❗️
ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- ፍትሐዊ ያልሆነውን የህግ ባለሙያዎች የቅጥር መስፈርት ማስተካከያ እንዲደረግበት ስለመጠየቅ
በአሁኑ ሰዓት ሚኒስቴር መስሪያቤታችሁ ያወጣው የህግ ባለሙያዎች የቅጥር ማስታወቂያ የያዘው መስፈርት እጅግ አግላይ እና በብዙ የሚቆጠሩ ብቁ ተማሪዎችን ከውድድር ውጭ የሚያደርግ በመሆኑ ከፍተኛ ቅሬታ ፈጥሯል። ከዚህ ቀደም በነበሩ የቅጥር ሂደቶች (ለምሳሌ ባለፈው ዓመት የነበረው የ CGPA 3.25 እና ከዚያ በላይ እንዲሁም የ Exit Exam 85% ፐርሰንታይል መስፈርት) የተሻለ ተደራሽነት እና ሚዛናዊነት የነበረው ቢሆንም፣ የዘንድሮው አሰራር ግን የሚከተሉት መሠረታዊ የፍትሐዊነት ችግሮች አሉበት፦
የመጀመሪያ ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች (First Generation Universities) ነባራዊ ሁኔታ አለመታሰቡ፦
1. እንደ ባህር ዳር፣ አዲስ አበባ እና ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ያሉ የመጀመሪያ ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች እጅግ ጥብቅ የሆነ የትምህርት አሰጣጥ እና የውጤት አሰጣጥ ስርዓት የሚከተሉ፣ ውጤት በግዴለሽነት የማይሰራባቸው ነገር ግን ከፍተኛ አቅም እና እውቀት ያላቸው ተማሪዎችን ያፈሩ ተቋማት ናቸው። እነዚህ ተማሪዎች በብሔራዊ የማጠቃለያ ፈተና (Exit Exam) ላይ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ቢሆንም፣ በነበረው ጥብቅ የምዘና ስርዓት ምክንያት በ CGPA በትንሽ ነጥብ መቀራረብ ብቻ ከውድድር ውጭ መደረጋቸው እጅግ አድሎአዊ እና እውነተኛ ብቃትን ያላገናዘበ ነው።
የሁለቱ መለኪያዎች አለመጣጣም እና አግላይነት፦
በ CGPA የተሻለ ውጤት ያላቸው ነገር ግን በ Exit Exam ውጤታቸው መጠነኛ ዝቅ ያለባቸው ብቁ ተማሪዎችም ሆኑ፣ በ Exit Exam ከፍተኛ ብቃት አሳይተው በ CGPA በትንሽ ነጥብ ዝቅ ያሉት ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ከጨዋታው ውጭ እንዲሆኑ ተደርጓል። ይህ ደግሞ የመጫወቻ ሜዳውን ፍትሐዊ እንዳላደረገው እና ብዙ አቅም ያላቸውን ወጣት የህግ ባለሙያዎች ያገለለ አሰራር ነው።
ስለሆነም፣ የፌደራል ተቋማት የስራ ቅጥር በተቻለ መጠን ሁሉንም የሀገሪቱን የትምህርት ተቋማት ነባራዊ ሁኔታ ያማከለ፣ ሚዛናዊ እና አካታች መሆን ስላለበት፤ ሚኒስቴር መስሪያቤታችሁ አሁን የተዘረጋውን ጥብቅ የማጣሪያ መስፈርት እንደገና እንዲመረምረው እና ብቁ ተማሪዎችን ባካተተ መልኩ ማስተካከያ እንዲያደርግልን በአክብሮት እንጠይቃለን።
ከሰላምታ ጋር፣
የ 2018 የሕግ ተመራቂዎች.
1 707
# አስደሳች የሕግ ውሳኔ! የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያስተላለፈው ታሪካዊ ውሳኔ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰጠው ውሳኔ፣ የወንጀል ምርመራ ሳይጠናቀቅ ወይም ክስ ሳይመሰረት ተጠርጣሪዎች በእስር እንዲቆዩ ትዕዛዝ መስጠት ሕገ-ወጥ መሆኑን አብራርቷል።
# ዋና ዋና ነጥቦች፦
የጉዳዩ አመጣጥ፡ አመልካች (አቶ አበበ ዳሙሳ) በተጠረጠሩበት የኃይማኖት ማጥፋት እና የቴሌኮም የገንዘብ ማጭበርበር ወንጀል ምርመራ ሳይጠናቀቅ፣ ኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ15 ቀን ጊዜ በመስጠት ክስ እንዲመሰረት አዟል።
የቀረበው ክርክር፡ "የምርመራ ጊዜ ተሰጥቶ ክስ ሳይመሰረት እና ከእስር ሳይፈቱ እንደገና ለሁተኛ ጊዜ የምርመራ ጊዜ መጠየቅ ሕገ-ወጥ ነው፤ የሰዎች የነፃነት መብት ሊከበር ይገባል" የሚል የሰበር ቅሬታ ቀርቧል።
የሰበር ችሎት ትንተና፡
በሕገ መንግሥቱ አንደ 17/2 እና 19/6 መሠረት ማንኛውም ሰው በሕግ ካልተደነገገው ሥርዓት ውጪ ነፃነቱ ሊነፈግ እንደማይችል ተደንግጓል።
የወንጀል ምርመራ ሳይጠናቀቅ እና ክስ ሳይመሰረት ተጠርጣሪውን ከእስር ሳይፈቱ በተደጋጋሚ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ማራዘም መሠረታዊ የሕግ ስህተት መሆኑ ተረጋግጧል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ፡
የታችኛው ፍርድ ቤቶች የሰጡዋቸው የምርመራ ጊዜ ማራዘሚያ ትዕዛዞች መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለባቸው በመሆኑ ተሻሽለዋል።
አመልካች 50,000 (አምሳ ሺህ) ብር ዋስትና በማስያዝ ወይም በቂ ዋስትና ቀርቦ ከእስር እንዲፈቱ ተወስኗል።
ይህ የሰበር ውሳኔ ለጥናት እና ምርምር እንጂ ለፍርድ አፈፃፀም አያገለግልም
1 707
የፍርድ ቤቶች ዓመታዊ የዕረፍት ጊዜ
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 በአንቀጽ 38 ላይ እንደተደነገገው፤ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች (ጠቅላይ፣ ከፍተኛ እና የመጀመሪያ ደረጃ) በየዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ መስከረም 30 በከፊል ዝግ ሆነው ይቆያሉ።
ይህ የዕረፍት ጊዜ እየቀረበ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ፣ ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ በሚሆኑበት ወቅት የዳኝነት አገልግሎቱ ሙሉ በሙሉ እንደማይቋረጥ እና የትኞቹ ጉዳዮች እንደሚስተናገዱ ማወቅ አስፈላጊ ነው።
ፍርድ ቤቶች የዜጎችን መብትና ጥቅም የሚያስክብሩ ተቋማት በመሆናቸው፣ ሙሉ በሙሉ ዝግ አይሆኑም። ይልቁንም አጣዳፊ ምላሽ የሚሹ ጉዳዮችን ለማስተናገድ በተረኛ ችሎቶች በከፊል ክፍት ሆነው አገልግሎት ይሰጣሉ።
የክልል ፍርድ ቤቶችም በየራሳቸው ሕጎች በተደነገገው መሠረት የዕረፍት ጊዜያት የሚኖራቸው ሲሆን፣ በዚህም ወቅት አጣዳፊ ጉዳዮችን በተረኛ ችሎት በማስተናገድ በከፊል ዝግ ሆነው እንደደሚቆዩ ይታወቃል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያስተላለፈው ማስታወቂያ ከዚህ ጋር ተያይዟል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከሐምሌ 21/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም ድረስ በክረምት እረፍት ምክንያት መደበኛ የመዝገብ ሥራ ዝግ ይሆናል።
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ሆነ የሌሎች ክልሎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የዓመቱን የዕረፍት ጊዜ ዝርዝር አፈፃፀም አስመልክተው ይፋዊ መግለጫ በቅርቡ እንደሚያወጡ ይጠበቃል።
J
