🔥የወንጌል ስርጭት revival🔥🔥
الذهاب إلى القناة على Telegram
እነሆ፥እኔ እላችኋለሁ፥ዓይናችሁን አንሱና እርሻው አሁን እንደ ነጣ እዩ።" — ዮሐንስ 4፥35 🔥 missional መነቃቃትን ማምጣት (Revival) 📢 የወንጌል ስምሪትን መፍጠር (Mobilization) 📖 አገልጋዮችን ለታላቁ ተልዕኮ ማብቃት (Mission) 👉 እርስዎም ባለራዕይ ከሆኑ ተቀላቅለው አብረውን ያገልግሉ!⚠️I'm missionary and mission mobilizer.
إظهار المزيد1 747
المشتركون
+5024 ساعات
+2697 أيام
+68730 أيام
أرشيف المشاركات
Meditate missioner's thought
"አንዳንዶች በቤተክርስቲያን ደወል ድምፅ ስር መኖርን ይመኛሉ፤እኔ ግን ከገሃነም ደጃፍ ላይ ሰዎችን ማዳኛ ጣቢያ (Rescue shop) መክፈት እፈልጋለሁ።"(Some wish to live within the sound of a church or chapel bell; I want to run a rescue shop within a yard of hell.)
ሲ.ቲ. ስተድ (C.T. Studd) - የእንግሊዝ ሚሲዮናዊ
ሰላም እንዴት ናችሁ ቤተሰብ! 😊
ዛሬ አንድ ደስ የሚል ቻናል ላስተዋውቃችሁ። በዚሁ ቻናል ላይ አብረን የምንወያይበት Live Stream ይኖረናል! 🎙️✨
በውይይታችን የምናነሳቸው አርእስቶች፦ • ስለ ህይወት •ስለ ትምህርት እና ስለ ወደፊት ግቦቻችን • ስለ ፍቅር ህይወት እና ክርስቲያናዊ ትዳር • አብረን የምንማማርበት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት (Bible Study)
አልፎ አልፎም ጥሩ እይታ ያላቸውን እንግዶች እየጋበዝን ልምድ እንወስዳለን። አብረን እንብስል አብረን እንደግ!
ገብታችሁ ተቀላቀሉን👇 🔗 https://t.me/Ethiobirtuset
2019 እግዚአብሔር በእውነተኛ የተልዕኮ መነቃቃት የሚባርከን ዓመት ይሁንልን!
እስኪ let me challenge you ወንድሞቼ፣የ2018 ዓመተ ምሕረት እንደ ጌታ ፈቃድ እያለቀ ነው። ሁለት ቀን ብቻ ቀረው፤እና ዛሬ ቆም ብላችሁ እንድታስቡ ላሳስባችሁ ነው።
በ2018 ዓ.ም ስለ እግዚአብሔር ታላቅ ተልዕኮ ምን አስተዋጽዖ አደረግን? በእውነት ተልዕኮውን አሳክተን ነበር? ወይስ እንዴት ነው ለተልዕኮው ማሰናከያ ሆናን ነበር? ያለፈው ዓመት አዎ፣አንዳንዶቻችን ስብከታችን ራሱ ምናልባት ሕንፃ ስለመገንባትና ስለ ቁሳቁስ ብቻ ሆኖ ሊሆን ይችላል፤ግን ሕንፃ መስራትን እኔ እየተቃወምኩ አይደለም።ግን እንዴት ነው ለተልዕኮ ጉዳይ አንድ ሺህ ብር የማይሰጡ ሰዎች በሚሊዮኖች ሲሰጡ እንዴት አልነቃንም? ለምን ደስ ብሎን ዝም አልን? ልንጠይቅ ይገባል።ሰዎች ለተልዕኮ ሲባል ነው ወይስ ለሌሎች ጉዳዮች ነው ብር ለመስጠት የሚሮጡት? ለተልዕኮ የማያደርጉትን ለሌላ ለውስጥ ጉዳይ ብቻ የሚያደርጉ ከሆነ ምናልባት ሰዎችን ልናሰለጥናቸው ይገባል።
ለነገሩ አይወቀሱም፤እኛ ከፊት የምናገለግል ሰዎች ራሱ ለቁሳቁስ ጊዥ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ጠቅሰን እንደምንሰብከው ልክ እና ከዚያ በላይ ስለ ተልዕኮ አንገበጋቢነት የማስተማር ልማዱ የለንም። ስለዚህ ሕዝቡን ሞቢላይዝ ልናደርግ ይገባል። አሁን ቁሳቁስ ላይ ብቻ ብዙ የምንቆይበት ጊዜ ላይ አይደለንም፤ወንጌል ሊሮጥ ይገባል በፍጥነት፣ሌላው ሁሉ ትርፍ ነው ወዳጆቼ። ስለዚህ ስለልተደረሱት ግድ ሊለን ይገባናል።
እና ጳውሎስ ቢኖሩ በቁጥር በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ የጌታን ወንጌል ያልሰሙ ሰዎች በሚኖሩበት ዓለም በእኛ ልክ ሌላ ነገር ላይ የሚቆዩ ይመስላችኋል? በፍጹም! ነፍሳቸው በእነርሱ ዘንድ እንደማትከብር ከማቆጠርና ለእስርም ለሞትም ተላልፈው ከመሳጠት በቀር ወደኋላ አይሉም።እንዲያውም በጣም የሚያዝነኝ አሁን የቤተክርስቲያን ስብሰባው ራሱ ሌላ ሌላ ጉዳይ መሆኑ ነው፤አሁን ለይዘታዊ ጉዳዮች እና ለአንዳንድ ሥርዓት ጉዳዮች በምንሰበሰብበትና ከላይ መመሪያዎችን በምናወርድበት ልክ ስለ ተልዕኮ ጉዳይ መመሪያዎች ቢወርዱ፣ተልዕኮን መፈጸምና በዚህ ጉዳይ መሳተፍ የሁሉም አማኝ ድርሻ መሆኑን ማስገንዘብ ቢቻል ምን ያህል ጥሩ ነበር! ሲደረግ ግን እያየነው አይደለም።
ዋና ሃሳቤ ትችት ሳይሆን በሁሉም ነገር የተልዕኮ ጉዳይ ሊጠቃለል ይገባል ማለቴ ነው እንጂ እግዚአብሔር ይመልሰን! አሁንም ያለፈውን እንተወው፤በእውነት ወንጌልን እንሥራ።እግዚአብሔር ዕድል ሰጥቶኝ ሚሽን በሚሄድበት አካባቢዎች አብዛኞቹ የምሰማቸው ሪፖርቶች ልክ እንደልሆኑና እንደገና ወደ ተልዕኮ መመለስ እንዳለብን በጣም ውስጤ እርግጠኛ ነው።ስለዚህ እውነተኛ የተልዕኮ መነቃቃት እግዚአብሔር ያስነሳልን።
በእውነት ያሳዝናል፤በዚህ ሁሉ ግን ለተልዕኮ ትልቅ ዋጋ የምትከፍሉ ቡሩካን እንደ ቤተክርስቲያንም እንደ ግለሰብም ጸጋ ይብዛላችሁ፤ተባረኩ፣ቀጥሉበት፣በርቱ! 2019 ደግሞ ዋና የእቅዳችሁ እምብርት የተልዕኮው ጉዳይ ይሁን።ከዚህ በፊት ብዙ ጊዜ የጻፍኩትን ላሳስባችሁ ነው! 2019 እግዚአብሔር በእውነተኛ የተልዕኮ መነቃቃት የሚባርከን ዓመት ይሁንልን!
ምናልባት ዳምቦያ ወረዳ የምትኖሩ ሰዎች፣ዛሬ እስከ ማታ 12፡00 ሰዓት ቶሎ ኢንቦክስ ለሚያደርጉልኝ የተልዕኮ ስልጠና ስፖንሰር የማድረግ ሃሳብ አለኝ ምናልበት ለ አንድ ወይም ለሁለት ቤተክርስቲያን፤ቶሎ ኢንቦክስ አድርጉልኝ።በሌላም አካባቢ የምትኖሩ፣እድሉ ከሌላችሁ ኢንቦክስ አውሩኝ!
@Trinitarian_Aman
የሚስዮን አቅጣጫን ማስተካከል
አብዛኛው የሰው ኃይል፣ጸሎት እና የበጀት ድጋፍ ወንጌል በደረሰባቸው አካባቢዎች ላይ ብቻ ከሚደጋገም፣ትኩረታችንን በዓለም ዙሪያ ወንጌል ወደ አልደረሰባቸው የሩቅ ስፍራዎችና ህዝቦች (Unreached People Groups) ማዞር አለብን፤ ይህም ማለት ወንጌል በተደጋጋሚ በተሰበከባቸውና በርካታ አብያተ ክርስቲያናት ባሉባቸው ቦታዎች ላይ ብቻ ተጨማሪ ጊዜና ሀብት ከማፍሰስ ይልቅ፣አንድም ጊዜ ስለ ክርስቶስ ሰምተው የማያውቁ ሰዎችን ማስቀደም ፍትሃዊ ነው። ምክንያቱም ወንጌልን በፍጹም ያልሰሙ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች እያሉ፣በሚያውቁትና በሰሙት ላይ ብቻ ማተኮር የተሰጠንን ታላቅ ተልዕኮ ዘንጊ ያደርገናል። ስለዚህ የቤተክርስቲያንና የአማኞች ዋና ትኩረት ወንጌል ጭራሽ ባልደረሰባቸው አካባቢዎች ላይ መሆን አለበት ለ 2019 ዓ.ም እንደ ቤተክርስቲያንም እንደ ግለሰብም ለሊተደራሱት ቅድሚያ መስጠት ይኖርብናል።
ለመሆኑ ሚስዮናውያንን 2018 ዓ.ም የት አከባቢ ነው የለክናው እናም ምን አይነት አከባቢ ይሁን ሚሽን የወጣነው ? ወደ ሊተደራሱት አቅንተን ማዬት አለብን!
Meditate missioner's thought
"ማንም ሰው ወንጌልን አንድ ጊዜ ሳይሰማ፣ ሌላው ሰው ሁለት ጊዜ የመስማት መብት የለውም።"(No one has the right to hear the gospel twice, while there remains someone who has not heard it once.)
ኦስዋልድ ስሚዝ (Oswald J. Smith)
ቅድሚያ ለሊተደራሱት
Meditate missioner's thought
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
"የማቃጥላት አንዲት የህይወት ጧፍ ብቻ አለችኝ፤ እርሷንም በብርሃን በተሞላች ሀገር ከማበራት ይልቅ በጨለማ በተዋጠች ሀገር ባበራት እመርጣለሁ።"(I have but one candle of life to burn, and I would rather burn it out in a land filled with darkness than in a land flooded with light.)
ጆን ኪዝ ፋልኮነር (Ion Keith-Falconer)
ቅድሚያ ለሊተደራሱት
ወዳጆቼ እግዜር በኃይል እየተጠቀመንና ታላቅ ክብሩን በእኛ
እየገለጠ፣በምናገለግለው አገልግሎትም ብዙዎችን እያጽናና ከሆነ፤እኛ በጣም ከሌሎቹ የተሻለ አቅም፣እውቀት፣ብቃትና ችሎታ ወይም በጣም ሊያስመሰግነን የሚገባ ጠንካራ ጎን ኖሮን አይደለም።እንደ ባለጠግነቱና ምሕረቱ እርሱ ብቻውን በእኛ እየሠራ እንደሆነ ለመግለጥ ነው እንጂ።
ስለዚህ በድካማችን አልፎ ለሚሠራ፣ለክብሩ ሁሉ ባለቤት ክብር ይሁንለት! እንዳው ይሄንን ሀሳብ ካነሳሁ ላይቀር አንድ ነጭ ሰው የተናገረውን ነገር ነግሬያችሁ ልሰናበታችሁ። እንዲህ ብሏል፦'ሳገለግል በጣም ከተሳካልኝ እኔ አይደለሁም፣እግዜር ኃይሉን ገልጧል ማለት ነው ወይም የኔ እጅ የለበትም። ካበላሸው ግን የኔ እጅ አለበት' ብሏል።
ወዳጆቼ በአገልግሎታችን ብዙ ፍሬ እያየን ከሆነ እርሱ ሠርቶ ነው፤እርሱ ሊመሰገን ይገባል።እግዜር በክብሩ ድርድር አያውቅምና።ነገ ደግሞ ቸርች መሄድ እንዳትረሱ፤በዛውም ላልተደረሱትም ጸልዩ። መልካም አዳር ይሁንላችሁ!
+4
የእግዚአብሔር ተልእኮ ስልጠና የጠዋቱ ፈረቃ፣ለዚህ ስልጠና የማይረሳ ድጋፍ ያደረጋችሁልን ቅዱሳን በእውነት ተባረኩልኝ! ከሰዓትም ይቀጥላል🙏
🎯ማሳሰቢያ ለዳምቦያ አካባቢ ወጣቶች!
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ወዳጆቼ የእግዜር መልካም ፈቃድ ከሆነ ስልጠናችን ነገ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ጀምሮ ነው የሚሆነው MKC ቸርች ግቢ። አሰልጣኙ እንደ እግዜር ፈቃድ ዛሬ ገብቶ ያድራል፤ ስለዚህ እንዳታረፍዱ። ጸጋ ይብዛላችሁ!
ወዳጆቼ ሰላምና ጸጋ ይብዛላችሁ። እንግዲህ ማታ ለኤን ቪዥን/N Vision (የእግዜር ተልእኮ) ስልጠና ድጋፍ (support) እንድታደርጉ ጠይቄያችሁ ነበር። እናም በቶሎ ምላሽ የሰጣችሁኝ ሰዎች በእውነት ምንም ማለት አልችልም፤ተባረኩ እንደልላችሁ፣በሰማያዊ ስፍራ በክርስቶስ ኢየሱስ ተባርካችኋል በበረከት ሁሉ። እንግዲህ [ጌታ] እግዜር በእናንተ ዘመን ኢየሱስን ይግለጥ። ነገራችሁ እየጨመረ ሲመጣ ኢየሱስ ይብዛላችሁ።አሁን ምናልባት አንድ ሦስት ሰው ብቻ የተወሰነ ነገር ከጨመራችሁልን ይበቃናል፤ተባረኩልኝ ውዶቼ!
ወዳጆቼ ሰላምና ጸጋ ይብዛላችሁ። ዛሬ ትንሽ የከበደኝን ነገር ልነግራችሁ ነው የመጣሁት። ለእኔ ብር መጠየቅ በጣም ከባድ ነው፣ በእውነት ግን ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ። አንድ የሚሽን ስልጠና፣ የእግዜር ተልእኮ የምለውን፣ ለወንጌል ካደረብኝ ቅናት የተነሳ አዘጋጅቼ ነበር። ግን ምንም ብር ሳላገኝ ጊዜው ቅዳሜ ደረሰ። ሰልጣኞቹ ለምሳቸው የሚሆን አንድ መቶ ብር ይዘው ነው የሚመጡት፣ ነገር ግን አሰልጣኙ ከወላይታ ሶዶ ነው የሚመጣው። ዛሬ የቢሮ ፕሮጀክተር እሱ ጋር እንደሌለ ነገረኝ፤ እና እሱን ለመከራየትና አገልጋዩንም ለመሸኛት የተወሰነ ድጋፍ እንድተረጉልን በትህና እጣይቃለው።
እኔ ደግሞ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ነኝ፣ያለፈውን ሳምንት ደግሞ ሚሽን ኮንሶ ዳራሼ አካባቢ ስለነበርኩኝ ምንም አማራጭ ለመፈለግ አቻኩም ነበር ፤ስለዚህ እስኪ የተወሰነ ነገር ድጋፍ (support) አድርጉልን። ለዚህ ስልጠና ስልጠናው ሲካሄድ ፎቶ አስቀምጥላችኋለሁ። በእውነት ፈቃደኛ ለሆነ ሰው አካውንቴን አስቀምጣለሁ!
Account 1000268433247
Amanuel Addise
በድካም ጊዜ የሚጮኽ ብርቱ ጩኸት━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ወዳጆቼ በዚህ ምድር ላይ እያላችሁ በልዩ ልዩ ፈተና ማለፋችሁ ግድ ነው። ምንም እያንዳንዳችን የምንፈተንበት የፈተና ዓይነት ቢለያይም፤በዚህ የፈተና መንገድ ስታልፉ በመንፈሳዊ ሕይወታችሁ ዝቅታና መወዥቅ በእርግጠኝነት ታልፉበታላችሁ።ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ብርቱ ዐውሎ ነፋስ ነፍሶባችሁ፣ባሕሩ ሊያሰጥማችሁ ደርሶ «እደርስበታለሁ» ብላችሁ ያሰባችሁበትን ጉዳይ መና ሲሆንባችሁ ታዩና «በቃ» ልትሉ ትችላላችሁ።በእርግጥ አልተሳሳታችሁም።
ነገር ግን በዚህ ሁሉ ውስጥ የምታስመስሉ ከሆነ፣እየተዋጣችሁ እንደሆነ ልባችሁ እያወቀ፣በመጮህ ፈንታ «አይ ብርቱ ነኝ፣ደኅና ነኝ» የምትሉ ከሆነ ከባድ ነው።በእንደዚህ ዓይነቱ ሰዓት ግልጽ መሆን ነው ያለባችሁ።ልክ እንደ ጴጥሮስ፤ጴጥሮስ ኢየሱስን በባሕር ሲሄድ አይቶ «ልምጣ» ባለው ጊዜ ኢየሱስ «ና» አለው።
ነገር ግን ጴጥሮስ ጉዞውን ምንም በድፍረት ቢጀምርም እንዳሰበው አልሆነለትም፤መስጠም ጀመረ።ይህም ሲሆን ግን ጴጥሮስ «ቆይ እየዋኘሁ ነው፣እችላለሁ፤መጣሁ ጠብቀኝ» አላለም።«ጌታ ሆይ እየተዋጥኩ ነው፤እኔ መምጣት ባልችልም አንተ ግን ወደ እኔ መጥተህ ታድነኛለህና ና አድነኝ» አለ።
ታዲያ እኔና እናንተም መዋጥ ስንጀምር ምክንያት ከማዘርዘር ይልቅ «ወደ አንተ መቅረብ እየፈለግኩ አቅቶኛል፤አረሙ በዝቶ እየዋጠኝ ነው፤እኔ መምጣት ቢያቅተኝም አንተ ግን ወደ እኔ መምጣት ትችላለህና መጥተህ አድነኝ» ብለን በድካም ሰዓት ብርቱ ጩኸት ስንጮኽ፣በእርግጠኝነት እርሱ በድካማችን ሊራራልን የሚችል ታላቅ ሊቀ ካህናት ነውና መጥቶ ያወጣናል። ከተያዝንበት ነገር በድካም ብርቱ ጩኸት ለሚጮኹ መጥቶ የሚያድን አምላክ አለና።
ምናልባት ከእግዚአብሔር ጋር የለመዳችሁት የጓዳ ቆይታችሁ እየሄደባችሁ ከሆነ፣መዝሙርና ጸሎታችሁ፣እግዚአብሔር እንድትነግዱበት የሰጣችሁ ጸጋ እየሄደባችሁና በሌላ ነገር እየተዋጣችሁ ከሆነ ብርቱ ጩኸት ጩኹ! ልክ እንደዚያኛው ምሳር በባሕር ወድቆበት «ወዮ ጠፋሁ፣ተበድሬ ያመጣሁት ነበረ» ብሎ ብርቱ ጩኸት እንደጮኸው ሰው ጩኹ እንጂ! በእውነት እናንተ እርሱ ጋር መምጣት ባትችሉ እንኳ እርሱ ወደ እናንተ ይመጣል።
አይዟችሁ፤አምላካችን በድካም ለሚደረግ ብርቱ ጩኸት አይዘገይም!
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ሮሜ 13:11-12
11 ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።
12 ሌሊቱ አልፎአል፥ ቀኑም ቀርቦአል። እንግዲህ የጨለማውን ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ።
መልካም ቀን
•••••••••••••••••••••••••••••
🎯ማሳሰቢያ
ሰላም ይብዛላችሁ! ዳምቦያ አካባቢ የምትገኙ ወጣቶች፣ ባለፈው እንዳልኳችሁም ቅዳሜ የሚኖረን የሚሽን ( የ 'ኤን ቪዥን' (N Vision) ወይም የእግዚአብሔር ተልዕኮ) ስልጠና የሚሆነው በዳምቦያ ከተማ በሚገኘው MKC ቤተክርስቲያን ግቢ ነው፡፡ ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ስልጠናችንን የምንጀምርበት ነው፡፡ ጸጋ ይብዛላችሁ!
👉Mobilized by የወንጌል ስርጭት ሪቫይቫል ቲም
ኒኮላስ ሉድቪግ ቮን ዚንዘንዶርፍ
በ1700 በጀርመን የተወለደው ካውንት ኒኮላስ ሉድቪግ ቮን ዚንዘንዶርፍ የህግ ትምህርት ለማጥናት በዊተንበርግ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ ነበር።በ19 ዓመቱ በመስቀል ላይ በከፍተኛ ስቃይ ላይ ያለውን የክርስቶስን ስዕል እና "ይህን ሁሉ ያደረግኩት ላንተ ነው። አንተስ ለእኔ ምን ልታደርግልኝ ነው?" የሚል ጽሑፍ ይመለከት ነበር። እነዚህ ቃላት ልቡን ሰርስረው ገቡ፣እርሱም ተለወጠ።ከዚያን ጊዜ ጀምሮ፣ዚንዘንዶርፍ ወንጌልን በዓለም ዙሪያ ለማዳረስ ራሱን ሰጠ።ስለ ዓለም በመማለድ ላይ ያተኮረና ለአንድ መቶ ዓመታት ያለማቋረጥ የዘለቀ የ24 ሰዓት የጸሎት ትጋት ጀመረ።
በውጤቱም፣'ሞራቪያውያን' (the Moravians) የተባለው የሚሲዮን ማኅበሩ፣በቀጣዮቹ ሃያ ዓመታት ውስጥ፣ባለፉት ሁለት መቶ ዓመታት ውስጥ ማንም ከላከው በላይ እጅግ ብዙ ሚሲዮናውያንን ልኳል! ይህ ለኢየሱስ ያለው ንጹህ ቅንዓት እና ሠራተኞችን እስከ ምድር ዳርቻ የማሰማራት ተነሳሽነት ወደ ሌሎችም በቀላሉ የሚጋባ (ተላላፊ) ነበር።በእርሱ አገላለጽ፣"አለኝ የምለው አንድ ቅንዓት ብቻ ነው፡ እርሱ ነው፣እርሱ ብቻ። ዓለም ማሳ ነው፣ማሳውም ዓለም ነው፤ከእንግዲህ ወዲህም ነፍሳትን ለክርስቶስ በማትረፍ ስራ በበለጠ ልጠቅም የምችልበት አገር ሁሉ መኖሪያ ቤቴ ይሆናል።
🙏ጌታ ሆይ የ ሞራቪያውያን' (the Moravians) ታሪክ በእኛም ይደረግ!
"በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤" — ኤፌሶን 6:18
I was deeply moved and convicted after reading a brother's post on his channel concerning this photo of Evangelist Reinhard Bonnke. It honestly makes me reflect: as for us, who have we committed to reaching with the message?
መንፈስ ቅዱስ በቤተክርስቲያን_3
•••••••••••••••••••••••••••••••••
አንድ ትልቅ የሸራ መርከብ ነፋስ በሌለበት ባህር ላይ ምንም ያህል ውብ ቢሆንና አቅጣጫውና መሪው ቢስተካከልም መንቀሳቀስ አይችልም። በጰንጠቆስጤ ዕለት የወረደው መንፈስ ቅዱስ ግን እንደ ኃይለኛ ነፋስ በመምጣት (የቤተክርስቲያንን) የሐዋርያትን ልብ ሞላ፤ በዚያም ጊዜ ጀምሮ ቤተክርስቲያን ወደ ዓለም ሁሉ የመንቀሳቀስ ኃይል አገኘች። ዛሬም የወንጌል ስርጭት ወይም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መመስከር በመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚደረግ የሰዎችን አዕምሮ ለክርስቶስ የመመራክ ሥራ ነው። ሚሽኑ ከመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተለይቶ ሊሳከ የማይችል አገልግሎት ነው።
መልካም ቀን
•••••••••••••••••••••••••••••
