Ethiopian Health Insurance Service
الذهاب إلى القناة على Telegram
This is the official Telegram channel of the Ethiopian Health Insurance Service
إظهار المزيد2 477
المشتركون
-324 ساعات
-97 أيام
-1530 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮጵያ የጤና መድኅን አገልግሎት የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን የወረዳ ሽፋኑ 96 በመቶ መድረሱን አስታወቀ
መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢጤመአ)
የኢትዮጵያ የጤና መድኅን አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት የማህበረሰብ ዓቀፍ የጤና መድኅን (CBHI) ተደራሽነትን በማስፋፋት ረገድ ጉልህ ስኬት መመዝገቡን ገለጸ። ተቋሙ ሀገር አቀፍ የወረዳ ሽፋኑን ወደ 96 በመቶ ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የአባላቱን ቁጥር 15 ሚሊዮን በማድረስ አጠቃላይ ተጠቃሚዎችን ወደ 69 ሚሊዮን ማሳደግ መቻሉን ይፋ አድርጓል።
ይህንን መረጃ የሰጡት የኢትዮጵያ የጤና መድኅን አገልግሎት የአባላት አስተዳደርና የሀብት አሰባሰብ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጉደታ አበበ ናቸው። እንደ መሪ ስራ አስፈጻሚው ገለጻ፣ ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው ህብረተሰቡ ስለ ማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን ያለው ግንዛቤ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ በመምጣቱ ነው።
አቶ ጉደታ አበበ እንደገለጹት፣ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ የህክምና አገልግሎት ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረና የዋጋ ንረትም የታየበት ቢሆንም፣ ህብረተሰቡ "በመደጋገፍና ወጪን በመጋራት" መርህ ላይ የተመሰረተውን የጤና መድኅን ስርዓት እንደ መፍትሔ በመውሰዱ ውጤት ታይቷል። "ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቀውን የህክምና አገልግሎት በጋራ የማካካስ ባህል እያደገ መምጣቱ ለአባላት ቁጥር መጨመር ትልቁን ድርሻ ይይዛል" ብለዋል።
ምንም እንኳን ስራው ሰፊና ፈታኝ ቢሆንም፣ ከክልል እስከ ቀበሌ ያለው የመንግስት መዋቅር በቁርጠኝነት መስራቱ ለውጤቱ መገኘት ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። የመንግስት አካላት ህብረተሰቡን በማስረዳትና በማሳመን፣ አባላቱም እንደየመክፈል አቅማቸው መዋጮአቸውን እንዲያዋጡ በማድረጋቸው ሽፋኑ 96 በመቶ ሊደርስ መቻሉን አቶ ጉደታ አብራርተዋል።
የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን ስርዓቱ ማህበራዊ ፍትሃዊነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን የጠቆሙት መሪ ስራ አስፈጻሚው፣ በተለይም ሴቶች፣ ህጻናት፣ አካል ጉዳተኞች እና አዛውንቶች ቅድሚያ ተሰጥቷቸው የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙና መዋጮ መክፈል የማይችሉ 4.4 ሚሊዮን የሚሆኑ አባወራዎችና እማወራዎች በመንግስት ሙሉ ድጎማ ተደርጎላቸው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ የጤና መድኅን አገልግሎት በቀጣይ ቀሪ የሆኑ ወረዳዎችን ወደ ስርዓቱ በማስገባት እና አሰራርን በማዘመን ዲጂታላይዝ በማድረግ አንዳንድ ግድፈቶች ለመቅረፍ አተኩሮ እንደሚሰራ የአባላት አስተዳደርና ሀብት አሰባሰብ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጉደታ አበበ አሳስበዋ።
"Youtube: https://www.youtube.com/@Ethiopian-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram
በአዳማ ቅርንጫፍ የጤና መድኅን ተጠቃሚዎች መጨመሩን አስታወቀ
24/07/2018 ዓ.ም ኢጤመአ
የኢትዮጵያ የጤና መድኅን አገልግሎት የአዳማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት፣ የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን አባላት ቁጥር ባለፉት 13 ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ ዕድገት በማሳየት በአሁኑ ወቅት ከ1.5 ሚሊዮን በላይ አባወራዎችና እማወራዎችን መድረሱን አስታወቀ።
የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ እድሪስ አህመድ እንደገለጹት፣ ፕሮግራሙ በ 2005 ዓ.ም ሲጀመር የአባላቱ ቁጥር ከ4 ሺህ የማይበልጥ ነበረ። ሆኖም ግን ህብረተሰቡ የጤና መድኅን ያለውን ፋይዳ በመረዳቱና እርስ በእርስ የመደጋገፍ እና የጤና ወጪን የመጋራት ባህልን በማጠናከሩ፣ በ2018 ዓ.ም በአባወራ እና እማወራ ደረጃ የተጠቃሚዎች ቁጥር 1.5 ሚሊዮን ደርሷል።
ይህ ስኬት በቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ሥር የሚገኙትን ምስራቅ ሸዋ ዞን ፣ምዕራብ ሐረርጌ ዞን፣ አርሲ ዞን እንዲሁም አዳማ፣ ባቱ እና አሰላ ከተሞችን ጨምሮ በጠቅላላው 65 ወረዳዎችን ሙሉ በሙሉ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉ ተመልክቷል።
ከጠቅላላው የአባላት ቁጥር ውስጥ ከ92 ሺህ በላይ የሚሆኑት እማወራዎች መሆናቸውን የጠቀሱት አቶ እድሪስ፣ ይህም ሴቶች በቤተሰብ ጤና አጠባበቅ ላይ ያላቸውን ሚና ከማሳደጉም በላይ፣ የእናቶችና የህጻናትን ጤና ለመጠበቅ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን ገልጸዋል።
አገልግሎቱን ፍትሐዊና ጥራት ያለው ለማድረግ የተለያዩ ስልቶች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛሉ። የፋይናንስ ዘላቂነትን ለማረጋገጥ የአባላት መዋጮ እንደየመክፈል አቅማቸው እንዲሆን የሚያደርግ አሠራር ሙሉ በሙሉ ተተግብሯል። የወረዳዎችን የፋይናንስ አቅም ለማሳደግ በምዕራብ ሐረርጌ 20 ወረዳዎች እና በአርሲ ዞን 28 ወረዳዎች ከፍተኛ የፋይናንስ ቋት እንዲመሰረት ተደርጓል። ይህም አገልግሎት አሰጣጡ የተሳለጠና አስተማማኝ እንዲሆን ይረዳል። ቀሪዎቹ ወረዳዎችም በተመሳሳይ መልኩ በቀጣይ ወደዚህ ሥርዓት እንደሚገቡ አቶ እድሪስ ገልጸዋል።
የጤና መድኅን አገልግሎቱ ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን እያስመዘገበ ቢሆንም፣ አሁንም ድረስ አሰራርን የሚያደናቅፉ ክፍተቶች እንዳሉ አቶ እድሪስ አልሸሸጉም። ለሥራው እንቅፋት የሆኑ ዋና ዋና ጉዳዮች ተብለው የተጠቀሱት፣ የማህበራዊ ጤና መድኅንን ለማስጀመር በጀት አለመመደቡ፣ የሰዎች ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ ሁኔታ፣ የሥራ መሣሪያዎች ማለትም የላፕቶፕና ተያያዥ የቴክኖሎጂ ግብዓቶች እጥረት፣ እንዲሁም ለመስክ ሥራ የሚሆኑ ተሽከርካሪዎች እጥረት መኖራቸው ተጠቁሟል።
የአዳማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት እነዚህን ተግዳሮቶች በመቋቋም፣ በቀጣይም ተደራሽነቱን በማስፋት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለሁሉም ዜጋ ለማድረስ በትኩረት እንደሚሠራ የቅርንጫፍ ጽቤቱ ኃላፊ አቶ እድሪስ አህመድ አስታውቀዋል። "Youtube: https://www.youtube.com/@Ethiopian-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram
የጤና መድህን አገልግሎት ከሶማሌ ህዝብ የመደጋገፍ ባህል ጋር የተሳሰረ ነው” - ወይዘሪት አሚና አህመድ
02/07/2018 ዓም ኢጤመአ
በካራማራ አጠቃላይ ሆስፒታል የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አስተባባሪ ወይዘሪት አሚና አህመድ፤ የጤና መድህን አገልግሎት ከሶማሌ ህዝብ የአኗኗር ዘይቤና የመረዳዳት ባህል ጋር በእጅጉ የሚቀራረብ መሆኑን ገለጹ።
አስተባባሪዋ ጨምረው እንደገለጹት፣ የአካባቢውን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ የቅስቀሳ ስራ ከተሰራና ማህበረሰቡ በቂ ግንዛቤ ካገኘ፣ አገልግሎቱ ካለው ጠቀሜታ አንጻር ህዝቡ በደስታና ያለማቋረጥ እንደሚጠቀምበት ያላቸውን እምነት ተናግረዋል።
ቀደም ሲል አብዛኛው የክልሉ ነዋሪ አርብቶ አደር በመሆኑ፣ ለድንገተኛ የህክምና ወጪ ሲባል ከብቶቹን ለመሸጥ ይገደድ እንደነበር ያስታወሱት ወይዘሪት አሚና፤ ይህም ሆኖ ህክምናው የሚያስፈልገውን ያህል ወጪ የማይሸፍንበት አጋጣሚ ሰፊ እንደነበር ጠቁመዋል።
"አሁን ግን የሶማሌን የመደጋገፍ ባህል መሰረት ያደረገው የጤና መድህን፤ ነዋሪዎች ንብረታቸውን ሳይሸጡና ሳይሳቀቁ ተገቢውን የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ አስችሏቸዋል" ብለዋል።
ካራማራ አጠቃላይ ሆስፒታል የክልሉን የህክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት በማሳደግ ረገድ የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን የገለጹት አስተባባሪዋ፤ በአሁኑ ወቅት ከጅግጅጋ ከተማ አልፎ ከተለያዩ ወረዳዎች የሚመጡ የጤና መድህን አገልሎት ተጠቃሚዎችን እንደማንኛውም ዜጋ ፍትሃዊና ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት እያገኙ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም አገልግሎቱ ማህበረሰቡ መብቱን እንዲጠይቅ እያደረገው መሆኑን በመጥቀስ፣ ይህንን ታሳቢ ያደረገ የማሻሻያ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሲሆን፣የመድኃኒት አቅርቦት በእጅጉ እንዲሻሻል መደረጉ፣አስፈላጊ የሕክምና ግብዓቶች እየተሟሉ መሆናቸውና አጠቃላይ የህክምና ስርዓቱን የማዘመን ስራ በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በክልሉ ያለው የግንዛቤ ደረጃ ከወትሮው የተሻለ ቢሆንም፣ አሁንም ቀሪ ስራዎች እንዳሉ አስተባባሪዋ አልሸሸጉም። በቀጣይ የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት ማህበራዊ ሚዲያዎችን በስፋት መጠቀም፣የሃይማኖት አባቶችና የጎሳ መሪዎችን ግንዛቤ በመፍጠሩ ረገድ ማሳተፍ እንደሚገባ ጠቁመዋል፦
በአመት አንድ ጊዜ በሚከፈል አነስተኛ መዋጮ አመቱን ሙሉ ጥራት ያለው ህክምና ማግኘት የሚያስችለው ይህ አገልግሎት፤ ዜጎች በህመም ወቅት ከሚገጥማቸው ከፍተኛ ወጪ እየታደጋቸው መሆኑን በመግለጽ፣ የጤና አገልግሎቱን ይበልጥ በማሻሻል ተጠቃሚዎችን ቁጥር ለማሳደግ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
Youtube: https://www.youtube.com/@Ethiopian-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu
የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች የጋራ የኢፍጣር መርሃ-ግብር አከናወኑ
መጋቢት 01 ቀን 2018 ዓ.ም ኢጤመአ
የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት የማኔጅመንት አባላት ከተቋሙ የእስልምና እምነት ተከታይ ሰራተኞች ጋር በመሆን የጋራ የኢፍጣር መርሃ-ግብር አካሄዱ።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ወርቁ እንደገለጹት፤ በጋራ ማዕድ መቋደስ በሰዎች መካከል ያለውን ማህበራዊ ግንኙነት የሚያጠብቅና ትስስርን የሚያጠናክር ተግባር ነው። በተለይም በረመዳን ወቅት የሚከናወኑ እንዲህ ያሉ የጋራ የኢፍጣር ስነስርዓቶች በስራ ባልደረቦች፣ በጎረቤታማቾችና በወዳጆች መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግሩት ገልጸዋል። ይህ አይነቱ አብሮነትም በደስታም ሆነ በችግር ጊዜ እጅ ለእጅ ተያይዞ ለመቆም ጽኑ መሰረት እንደሚሆን ዋና ዳይሬክተሩ አስገንዝበዋል።
በኢፍጣር ስነስርዓቱ ላይ የታደሙት የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች፣ መሪ ስራ አስፈጻሚዎችና ስራ አስፈጻሚዎች በበኩላቸው፤ መርሃ-ግብሩ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት ያዳበሩትን የመከባበር፣ የፍቅር እና የአንድነት እሴት የሚያጸና መሆኑን ገልጸዋል። ይህንኑ ጥልቅ የሆነ አብሮ የመኖር ባህል ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባም አመራሮቹ በንግግራቸው ጠቅሰዋል።
በዕለቱ የተገኙ የእስልምና እምነት ተከታይ ሰራተኞችና አመራሮች በሰጡት አስተያየት፤ የረመዳን ወር የጾም፣ የጸሎትና የልግስና ወቅት መሆኑን ጠቁመው፣ እምነቱ የማይከተሉ ወገኖች በማዕዱ ላይ መሳተፋቸው "መስጠት መቀበል ነው" የሚለውን ሁለንተናዊ እሴት በተግባር የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም መካፈል ያለውን መንፈሳዊ እርካታ ከማሳየቱም በላይ ለተቸገሩ ወገኖች የሚሰጠውን ትኩረት ይበልጥ እንደሚያጠናክር አስረድተዋል።
መርሃ-ግብሩ በተቋሙ ሰራተኞች መካከል የቤተሰባዊነት ስሜት በመፍጠርና የስራ ተነሳሽነትን በማሳደግ በታላቅ የፍቅር ድባብ ተጠናቋል።
ለተሻለ የጤና አገልግሎት እና ለተሟላ ጤና ፣የጤና መድኅን።
27/06/2018 ዓ. ም ኢጤመአ
በአዲስ አበባ ደቡባዊ ክፍል፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 — በተለምዶ ሳሪስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ — የወ/ሮ ለይላ ሁሴን ሕይወት እንደ ንጋት ፀሐይ በብሩህ ተስፋ የተሞላ ነበር። ሆኖም ግን፣ ከአራት ወራት በፊት አንድ ቀን ያ ፈገግታ በድንገት ደመና ጋርዶት ቀረ።
በግራ ጡቷ ላይ የተሰማት እብጠት መጀመሪያ ላይ "ምናልባት የድካም ሊሆን ይችላል" ብላ አልፋው ነበር። ነገር ግን ህመሙና እብጠቱ እየጨመረ ሲመጣ ወደ ወረዳ 9 መጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ አመራች።
ከጤና ጣቢያው ወደ ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል በሪፈር በተላከችበት ወቅት፣ በለይላ አእምሮ ውስጥ ከህመሙ በላይ የገንዘብ እጥረት ጭንቀት ተደቅኖ ነበር። "እንዴት አድርጌ ነው ይህን ሁሉ ወጪ የምችለው?" የሚለው ጥያቄ በውስጧ ይመላለሳል። ሆኖም ግን፣ ለይላና ባለቤቷ አቶ ኢብራሒም ነጋሽ ቀደም ብለው የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን አባል መሆናቸው በዚያ ፈታኝ ወቅት እንደ ትልቅ ዋስትና ሆኖ ቀረበላቸው።
ለይላ ወደ ዘውዲቱ ሆስፒታል እንደመጣች ለስምንት ቀናት ተኝታ እንድትታከም ተደረገ። በነዚህ ቀናት ቆይታዋ የማህበረሰብ ጤና መድኅን ባይኖር ኖሮ፣ ዛሬ እዚህ አልጋ ላይ ሳይሆን ሜዳ ላይ እንወድቅ ነበር። የሰው ልጅ መረዳዳት ትርጉሙ የገባኝ ዛሬ ነው።" አለች ወ/ሮ ለይላ ፡፡
አቶ ኢብራሒምም በፈገግታ ራሱን ነቀነቀ። እሱም ቢሆን በተለያዩ ጊዜያት ወደ ህክምና ሲመጣ የመድኅኑ ተጠቃሚ መሆኑንና የተደገፈው ገንዘብ እያሰበ ተጽናና። በገንዘብ እጥረት ምክንያት ህክምናቸውን አቋርጠው የአልጋ ቁራኛ የሆኑ፣ ሞታቸውን በዝምታ የሚጠባበቁ ምስኪኖችን ታሪክ ሰምተዋል። ይህ ደግሞ በውስጣቸው የቆጫቸው ትልቅ ጉዳይ ሆነ።
ይሁን እንጂ የለይላ ጉዞ አልጋ በአልጋ አልነበረም። ህክምናዋ እየቀጠለ ሲመጣ፣ የመድኅን አገልግሎቱ ያልሸፈናቸው ወይም በሆስፒታሉ ውስጥ የማይገኙ አስፈላጊ ነገሮች መከሰት ጀመሩ። አንድ ቀን ሐኪሙ በጣም ወሳኝ የሆነ በሆስፒታሉ የሌለ የመድኃኒት ስም በወረቀት ላይ ጽፎ ሰጣት።
"መደጋገፉ ጥሩ ነው፣" ትላለች ለይላ ለሆስፒታሉ አስተዳዳሪዎችና ለሚመለከታቸው አካላት በምሬት። "ነገር ግን ውድ የሆኑና ለሕይወታችን ወሳኝ የሆኑ መድኃኒቶችን ሳናገኝ ስንቀር፣ ድጋፉ ጎደሎ ይሆናል።"
የለይላ ታሪክ የብዙ ኢትዮጵያውያን እናቶች ታሪክ ነው። በመረዳዳት ውስጥ ያለውን ተስፋ፣ ነገር ግን በሥርዓቱ ውስጥ ያለውን ክፍተት የሚያሳይ መስተዋት ነው። ለይላ ዛሬም ትመክራለች፣ ዛሬም ትሞግታለች — ለተሻለ የጤና አገልግሎት እና ለተሟላ የጤና መድኅን። ምክንያቱም ህይወት በመድኃኒት እጥረት ልትቀጠፍ የማይገባት ውድ ስጦታ መሆኗን ጠንቅቃ ታውቃለች። "Youtube: https://www.youtube.com/@Ethiopian-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
