ኢት-መጽሐፍት | ETHIO-BOOKS
الذهاب إلى القناة على Telegram
👉 "የምታነበው መጽሐፍ ለአንተ የሚያስብልህ ሳይሆን አንተ እንድታስብ የሚያደርግ ነው።" ሃርፐር ሊ Fiction (ልቦለድ), History (ታሪክ), Politics (ፖለቲካ), Psychology (ስነልቦና), Biography (ግለ-ታሪክ), Self-help(ራስ አገዝ),& Philosophy(ፍልስፍና) የሀገር ውስጥ & የውጪ ሀገር መጽሐፎችን ያገኛሉ!አስተያየትዎን እዚህ @Desutech_bot ያድርሱን
إظهار المزيد1 991
المشتركون
-124 ساعات
-47 أيام
-5230 أيام
أرشيف المشاركات
የወንጀል ህግ መጽሐፍ ተጋበዙልኝ!
መጽሐፏ ስለህግና ተያያዥ ጉዳዮች ጠለቀ ያለ ማብራሪያ ትሰጣለች።
በተለይ የህግ ተማሪ የሆናችሁና መሆን የምትፈልጉ ይሄ መጽሐፍ የግድ ያስፈልጋችኋል።
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
“ተጓዝ ግን ለማንም አትንገር ፥ የምር አፍቅር ግን ዝም በል፥ በደስታ ኑር ግን ደግሞ ለማንም ትንፍሽ እንዳትል፡ ለማንም ምንም አትበል በቃ ዝምበል"...
ሰዎች ቆንጆውን ነገር ያጠፉብሀል
[ካህሊል ጂብራን]
ሀዲስ/በበዓሉ ግርማ፥
በዓሉ ውብ ጭንቅላትን የተሸከመ የደራሲያን ቁንጮ ነበር ብል ለራሴ ትክክል ነኝ፣ ድርሰቶቹ ሁሉ በጥሩ ቋንቋ የተዋቡና ትምህርት ሰጪ ናቸው። በዓሉ የአንባቢን የልብ ትርታ የተረዳና በአንባቢዎች ተወዳጅ የሆነ፣ የደራሲነትን መመዘኛ ሙሉ ለሙሉ ያሟላ ከአለም ድንቅ ደራሲዎች ሥፍራ የሚመደብ ፣ ሀገሩን ይወድ የነበረ ችግር ከማራገብ መፍትሔን ለማዝነም የተገኘ መልካም ሠው ነበር።
ሀዲስ የመፅሐፉ ርዕስም፣ መሪ ገፀ ባኅርይም ነው። ገፀባኅሪዩ ሀዲስ የበዓሉ ተመራማሪ፣ ዕውቀትን አሰራጭ፣ መልካምነትን አስተማሪ፣ ሥራን ከህይወት አጣማሪ፣ አዛኝና ሠውን አክባሪ፣ ሠውን ለመርዳትና ሕፃናትን ለማውጣት ታታሪ ነው፣ በዓሉ በጥሩ ሁኔታ ሀዲስን ቀርፆታል፣ የዓለምን በጎነቶች ሁሉ አሸክሞታል፣ እንዲህ ያለ ሠው በውን ይገኛልን እስኪያሰኘን ድረስ።
በገፀ ባኅርያት አቀራረፅና፣ በሕይወት ጉዞ መነሻ የሀዲስ አለማየሁ ከፍቅር እስከ መቃብርና የበዓሉ ሀዲስ በብዙ መልኩ ይመሳሰላሉ፣ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል።
የሀዲስ አለማየሁ የገፀ ባኅሪያት የሕይወት ጉዞ መነሻ በጎጃም የምትገኝ ብቸና የምትባል የገጠር መንድር ስትሆን፣ የበዓሉ በኢሉባቦር የምትገኝ ሱጴ የተሰኘች መንደር ናት። ገፀ ባኅሪያትን ስናይ የሀዲስ ፊታውራሪ መሸሻና የበዓሉ ፊታውራሪ ተካ በአቻነት የተመደቡ ናቸው፣ የሀዲሱ የቆሎ ተማሪ በዛብህ በበጎ አመለካከትና በዐዕምሮ ብሩኅነት የበዓሉን ሀዲስ ተፎካካሪ ነው። የሀዲስ አለማየሁ ቆንጆዋ፣ ጨዋዋና ቁምነገረኛዋ ሠብለ ወንጌል ከሌላዋ ቆንጆ፣ ጨዋና ቁምነገረኛ የበዓሉ ዓይናለም ተፎካካሪ ናት፣ ሀዲስ አለማየሁ ጨዋ ለጨዋ የሆኑትን መሪ ተዋንያን ሰብለ ወንገልንና በዛብህን በፍቅር እንዳጣመርዋቸው ሁሉ በዓሉም ገፀ ባኅሪዩን ሀዲስንና የቆንጆዎች ቁንጮ የሆነችውን ዓይናለምን በፍቅር አጣምሯቸዋል።
በዓሉ ሀዲስ አለማየሁን በጣም ከማድነቁም በላይ ደራሲ ሀዲስ በፍቅር እስከ መቃብር የሚጠቅሷቸውን ሃሳቦች ለማዋዣነት ተጠቅሟል፣ ስማቸውንም የመፅሐፉ ርዕስና ዋና ገፀ ባኅርይም አድርጓል።
በዓሉ ሀዲስ መፅሐፉ ላይ፣ ሀዲስና ዓይናለም ተጋብተው አብረው እንዲኖሩ ሲያደርግ ሀዲስ አለማየሁ ግን፣ ሰብለንና በዛብህን ሳያገናኟቸው እንደተዋደዱ ወደ መቃብር እንዲወርዱ ነው ያደረጉት። በእኔ አስተሳሰብ እነዚህን ሁለት መጻሕፍት ማንበብ የቻለ ሁሉ ያነበበ ይመስለኛል።
በአሉ በሀዲስ ድርሰቱ ክስተቶችን እንዲህ ይገልፃል፦
ስለ ሀዲስ እናት ኅልፈት፥
"ከባድ ዝምታ ቤቱን ዋጠው። የእናቱን መሞት ማመን አቃተው። ጭካኔ የተሞላበት ፍቺ የሌለው የእግዜር ዕንቆቅልሽ ጨዋታ ከቶ ሊገባው አልቻለም። አንድ ደቂቃ ሕይወት__ተስፋ። በሚቀጥለው ደቂቃ ሞትመቃብር። የሕይወት እስትንፋስን ለማቆየት የታሰበ ገንዘብ ለከፈንለቃሬዛ። ተዝካር የሌለው ተዝካር አልባየድሃ ሞት። ኑሮው አይሰምር፣ ሞቱ አያምር__የድሃ ሕይወት፣ የድሃ መቃብር።"
ስለ ፊታውራሪ ቀጠሮ አክባሪነት፣ የማያከብሩትን ወቀሳና ትምህርት በተመለከተ፥
"ፊታውራሪ በቀጠሮ ቀልድ አያውቁም። ባለፈው ግዜ ለምሳ ቀርበው ባብዛኛው የጎረሰው የቀረበለትን ፍትፍት ሳይሆን ፊታውራሪ ስለግዜ ያላቸውን ፍልስፍና ነበር።ከማቲዎስ ወንጌል ውስጥ ከምዕራፍ 25 ቁጥር 1 ያለውን የብልሆችና የሰነፎች ቆነጃጅት ታሪክ እየጠቀሱ ------ግዜና ቀጠሮ መከበር አለባቸው። ከግዜና ቀጠሮ ውጭ የሚሆን ነገር የለም። ወቅትና ዘመናት ግዜና ቀጠሮን ጠብቀው ነው የሚፈራረቁት። እህል አለግዜው አይዘራም፣ አለግዜውም አይታጨድም። ሠውም ከቀነ ቀጠሮው አያልፍም። ግዜና ቀጠሮን የማያከብር ሰነፍ ነው፣ አውሬ ነው እንጂ ሠው አይደለም።" " ይሉ ነበር።
ስለ ተስፋ፥
" የመጨረሻ ትንፋሽ_ለመኖር የሚደረግ የመጨረሻ ትግል የማይበገር የሠው ልጅ መንፈስማን ነው እንደ ሞተ መቅረት የሚፈልገው፣ ዘለዓልም የመኖር ተስፋ የሠው ልጅ ርሃብና ጥማት አይደለምን፣ ተስፋ ቆርጦ እጅ ከመስጠት መታገል ይሻላል_በዚህ ዓለም የሠው ልጅ ፈፅሞ ተስፋ መቁረጥ የለበትም_ትግል የሠው ልጅ ዕጣ ፈንታ ነውእንኖራለን የሠው ልጅ ይኖራል።"
ከመፅሐፉ የሚወድቅ የለም፣ ባማሩ ቃላት የተቀነባበረ ነው፣ የተዋዛ ነው፣ የደራሲውን የመቀመምና የማዋዛት ክህሎት የሚገልፅ ነው፣ አንብቡኝ አንብቡኝ የሚል፣ የማንበብ ተስፋን የሚጭር፣ እንደዚህ ያለም ሠው ይሞታል፣ ጣሊያን ሲጨንቀው ሞት ፓፓን ኩሎ እንዳለ። አንብቡ በአማርኛው ትካናላችሁ፣ ትወዱትማላችሁ____ቸር እንሠንብት።
መአዛ:- "ያለንባብ ሕይወት ምንድነው?
ዓለማየሁ:- "ያው መብላት፣ መጠጣት፣ መዋሰብ ሊሆን ነው እንግዲ…"
መአዛ:- "ይሄንንማ እንሰሳትም ያደርጉታልኮ"
---
የትግራይ አቡነ ዮሐንስ ናቸው አሉ። አንዱ ወጣት ሊሳለም ይመጣል። ሲመለከቱት አይማርም።
አቡኑ:- "አትማርም?"
ወጣቱ:- "አልማርም"
አቡኑ:- "ለምን አትማርም?"
ወጣቱ:- "ምን በልቼ ልማር…?"
አቡኑ:- "ምን በልተኸ ደደብክ" አሉት ይባላል።
•
"ዓለማየሁ ገላጋይ ሸገር ካፌ ላይ ስለንባብ ከተናገረው"
"ማወቅ ስለምሻው ነገር ነው መማር የምፈልገው። ነገር ግን መምህራኖቹ ለፈተና ብቻ እንድማር ይፈልጋሉ ። በጣም የጠላሁት ነገር ደግሞ የምዘና ስርዓቱን ነው። በዚህ ምክንያት ምንም ነገር ውኃ አልቋጥርልህ አለኝ። መምህራኖቼ የዕውቀት ጥማቴን አጨነገፉብኝ። ውጤት ብቸኛ መለኪያቸው ነው። ታዲያ እንዴት መምህራን በዚህ በዘቀጠ ስርዓት ተማሪዎችን ይመዝናሉ?"
•
አልበርት አንስታይን
ስውሩና ያልተነገረው የአይሁዳውያን እና የኢትዮጵያውያን ታሪክ - ፍቅሬ ቶሎሳ
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
👉 እያሳለፍከዉ ያለሀዉን አስጀጋሪ ግዜ የምታሸንፍባቸዉ ወርቃማ ንግግሮች!!
1 ችግሩ ችግሩ አይደለም አንተ ለችግሩ የሰጠሀዉ ቦታ ነዉ።
2 አንተ ከችግሮችህ በላይ ነህ።
3 የትኛዉንም ችግር ፈጣሪ ወደአንተ ስልከዉ ልጥልህ ሳይሆን ሊያበረታህ ነዉ።
4 ማንም ሰዉ ለችግር አልተፈጠረም ፣ ማንም ሰዉ ለድህነት አልተፈጠረም።
5 ለመቻል እንጂ ችሎ የተፈጠረ የለም።
6 ዛሬ ላይ ከባድ ግዜን እያሳለፍክ ከሆነ እመነኝ ነገ በጣም ይቀልሃል።
7 ሁሉም ነገር መፍትሄ አለዉ፣ ሁሉም ጥያቄ መልስ አለዉ።
8 አሁን ማይ ያለብህን ችግር ተጋፍጠህ ማለፍ ከቻልክ እመነኝ ማንም የማይደርስበት ሰዉ ትሁናለህ።
9 ለኔ ስለመረጥክልኝ ተመስገን በል።
10 ተስፋ አትቁረጥ ነገ የተሻለ ቀን ይሆናል።
11 አንተ ጠንካራ ነህ አንተ ጋር ብዙ አቅም አለ ምንም አይነት ችግር በህይወት ቢፈጠር እመነኝ የማሸነፍ አቅም አለህ። አቅምህን ተጠቀምበት።
12 ነገ የተሻለ ቀን ይሆናል።
13 ሁሉም ነገር ግዜያዊ ነው ችግሮቻችንን ሁሉ ያልፋሉ።
Join_us;
👉 @et_books1
👉 @et_books1
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
