cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ነፍጠኛው አማራ

አማራ ያሸንፋል !

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
574
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

104 ሚሊየን ብር የተበጀተለት አዲስ አማራን የማተራመስ ሴራ/ሼር ይደረግ!! አስቸኳይ መረጃ የአማራ ህዝብ ለአፅፋው ከወዲሁ ይዘጋጅ ...! ኦህዴድ ከቅዳሜ ጀምሮ በአዳማ (ናዝሬት) ከትግራይ የሄዱ አክቲቪስቶችና የኦሮሞ አክቴቪስቶች እንዲሁም ከአማራ ክልል ደግሞ ክልሉን ከውስጥ ሆነው ይበጠብጡልኛል ያላቸውን የኬሚሴ፣ የቅማንትና የአገው ሸንጎ አክቲቪስቶችን ሰብስቦ ሲመክር ውሏል። የስብሰባው አጀንዳ ክልሉን (አማራን) እንዴት እንበትነው በሚል ሲዶለትበት እንደዋለ አረጋግጫለሁ። ይሄን ሰይጣናዊ ተልዕኮ ለማስፈፀም ለእነዚህ አክቲቪስቶች የስራ ማስኬጃ በጀት 104 ሚሊዮን ብር ተመድቦላቸዋል ተብሏል። ጦርነቱ ከውጭ ወደ ውስጥ በመከላከያ በኩል፣ ከውስጥ ደግሞ ጠባብ የፖለቲካ ፍላጎት ባላቸው አካላት እንዲዘወር ታቅዷል። ከአማራ ክልል ከተሳተፉ ተሳታፊዎች መካከል ▪ከአገው ሸንጎ መለሰ እንግዳን ጨምሮ 18 ተሳታፊዎች ▪ከቅማንት ኮሚቴ 8 ተሳታፊዎች ▪ከከሚሴ ኦነግ 9 ተሳታፊዎች ▪ከወሎ ህብረት ተስፋዬ ከበደ እና ብሩክ አበጋዝን ጨምሮ 9 ተሳታፊዎች ▪ከራያ ራዩማ ፓርቲ አገዘው ህዳሩ ሀጎስን ጨምሮ 5 በጠቅላላ ከአማራ ክልል ከ49 ፀረ-አማራ ተሳታፊዎች በላይ ተሳትፈዋል። (ከወግደረስ ጤናው ) ድል ለአማራ ህዝብ!!
إظهار الكل...
የስራ ማቆም አድማዋን ገዥዎቹ ይፈልጓታል! ብዙ ጊዜ የስራ ማቆም አድማ ወዘተ ጥሪ ወረቀት ፌስቡክ ላይ አያለሁ። ገዥዎቹ ለይምሰል ይቃወሙት ይሆናል እንጅ የሚፈልጉት ነው። በተለይ ያልተደራጀና ያልተጠና ከሆነ። 1) ገዥዎቹ ራሳቸው ህዝብ ስራ እያስፈቱ ነው። ጉዳያቸው አይደለም ባይሰራ። መንገድ ዘግተው ወደስራ እንዳይሄድ ሲከለክሉ ከርመዋል። ማዳበሪያ አያቀርቡ፣ ሲሚንቶ ከነጋዴ ጋር ተመሳጥረው በህገወጥ እየሸጡ ሌላውን ስራ አጥ አድርገውታል። በሶስት አመት ያልቃል የተባለ ግድብ 12 አመት የሞላው አለ። ፋብሪካዎቹ ስራ አቁመዋል። በሚቀጥለው አመት ደግሞ ተመራቂ አንቀጥርም ብለዋል። መስርያ ቤት ስራ የለም። ሄደህ ማየት ነው።ገዥዎቹ በኢትዮጵያ ላይ የስራ ማቆም አድማ ካወጁ ቆይተዋል። ብትሰራ ባትሰራ ጉዳያቸው አይደለም። 2) ወደ አገር ቤት የምትላከውን ትንሽ ዶላር ለራሳቸው አድርገዋል። ገንዘብ ጠፍቷል። አቅርቦት የለም። ነዳጅ በለው ስኳር ማቅረብ እየቻሉ አይደለም። ዘይት በለው ዱቄት ከቀን ቀን እየተወደደ ነው። ሱቅ ብትዘጋላቸው፣ ሳምንትና ወር ፀጥ ረጭ ብትል እረፍት የሰጠሃቸው ነው የሚመስላቸው። ችግሩ አንተ ባወጅከው የመጣ አድርገው፣ የአቅርቦት ጉዳይ ሳያስጨንቃቸው እረፍት ነው የሚወስዱበት። 3) የስራ ማቆም አድማ ስታደርግ ከአደባባይ ትጠፋለህ። ገዥዎቹ የሚፈሩት አደባባይ መውጣትን እንጅ ቤት ከተቀመጥክማ ደስታቸው ነው። ህዝብ የቤት ቁልፍ ቢሰጣቸው ዘግተውበት ቢጠፉ በወደዱ። 4) የስራ ማቆም አድማ የሚጎዳው ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ኑሮ ውስጥ ያለውን ነው። አብዛኛውን ህዝብ ማለት ነው። ይህ ማለት ደግሞ ህዝብ የስራ ማቆም አድማ የጠራውን ያማርራል ማለት ነው። አሊያም ገዥዎቹ አድማ የጠሩት እንዲጠሉ ያደርጋሉ። ለኢኮኖሚ ምስቅልቅል የዳረገው ገዥው ሆኖ ህዝብን ያስራበው የሶስት ቀን አድማ አድርገው ያቀርቡልሃል። በጅራፍህ ትገረፋለህ ማለት ነው። ነፃ አወጣዋለሁ ባልከው ህዝብ ዘንድ ፖለታካ ይሰሩብሃል። 5) በተለይ ባልተቀናጀ መልኩ ሲደረግ ሌላ ቀን አዋጭና አስፈላጊ ሲሆን ቢጠራ ህዝብ ከቁም ነገር እንዳያየው፣ ስልቱን እንዲሰለቸው፣ ትግሉን እንዲርቀው ያደርጋል። 6) ዋናዎቹ ገዥዎቹ አማራ ክልል በኢኮኖሚ ድቅቅ እንዲል ይፈልጋሉ። ስራ አቁሞ ቢከርም አድማ የጠራውን አካል ያመሰግኑታል። ህዝብ ትግሉን ሊያግዝ የሚችለው ደግሞ ገንዘብ ሲኖረው ነው። ሌላው በህገወጥ መንገድ ስራ እየሰጠ፤ አማራው ባለችውም ዘግቶ ከዋለ ለጠላቶቹ አዋጭ ነው። 7) ትግል ጊዜን ይጠይቃል። ተማሪዎች ለአመታት የደከሙበት ፈተና የሚፈተኑበት ወቅት ላይ "የትምህርት ማቆም" ተብሎ ስልት ከታጋይ ይሁን ከገዥዎች የመጣው ግራ የሚያጋባ ነው። ከዚህ ይልቅ የተቃውሞ ምንጩ ግራ እስኪገባቸው ድረስ ሊደረጉ የሚችሉ ስልቶች አሉ። በርካቶች ናቸው። ትግል የሚመራ አካል ስልቶቹን በደንብ አይቶ መርጦ፣ ጉዳትና ጥቅማቸውን አይቶ መሆን አለበት። ህዝብ በቀላሉ የሚቀባበለው፣ ለሚዲያ ግቡ የሆነ፣ ሰው አይቶት ምልክት የሚያደርገው፣ ፋሽን የሚያደርገው፣ የፀጥታ ኃይሉ ህገወጥ ነው አይደለም ብሎ የሚወዛገብበት፣ ቢከለክል ከህዝብ ጋር የሚጣላበት ስልት ሞልቷል። ከዚህ ላይ ልፃፈው? አልፅፈውም! እንደዛ አይደረግም! Getachew Shiferaw
إظهار الكل...
ከዚህ በታች ስማቸው የተዘረዘሩት ከሰሜን ሽዋ ዞን በአብይ ሰራዊትና የፌደራል ደህንነት ታፍነው ተወስደው በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከፍተኛ ግፍ በምርመራ ስም ሲፈፀምባቸው ቆይቶ ትናት ለፌደራል ፓሊስ ተላልፈው ተሰጠው በፌደራል ፓሊስ እስር ላይ የሚገኙት አርሶ አደሮች እና ነጋዴዎች ናቸው ። 1ኛ- አስቻለው ጌታወይ ሽዋተገኝ ከመራቤቴ ስራ አርሶ አደር 2ኛ-ጉሌ ሽዋንግዛው ደገፋው ከመራቤቴ ስራ አርሶ አደር 3ኛ-ንጉስ ገለታው እጅጉ ከመራቤቴ አርሶ አደር 4ኛ- ማሙየ በየነ ሰራ ከመራቤቴ አርሶ አደር 5ኛ-አብነት ጌትዮ በነበሩ ከመራቤቴ አርሶ አደር 6ኛ-ጌታወይ በለጠ ደምስ ከመራቤቴ አርሶ አደር 7ኛ-ብርሃኑ ሽመልስ ሰገን ከመራቤቴ አርሶ አደር 8ኛ-ግዛው ዳምጠው ግምቴ ከመራቤቴ ስራ ነጋዴ 9ኛ-መሀመድ ሽፈራው አለይ ከመራቤቴ ስራ አርሶ አደር 10ኛ-ተስፋማሪያም ተገኝ ተካ ከመራቤቴ ስራ አርሶ አደር 11ኛ- ስንታየሁ አርጋው እሸቴ። ከመራቤቴ ስራ አርሶ አደር 12ኛ- ታደለ ሲፈታ መርድ ከመራቤቴ ስራ አርሶ አደር 13ኛ- ፈሩ ታየ ጥላሁን ከሽዋ ሮቢት ስራ ነጋዴ 14ኛ- አዋሜ ጣሰው ጥላሁን ከሽዋ ሮቢት ስራ አርሶ አደር 15ኛ- ዳዊት ሀብታሙ ድሬባ ከሽዋ ሮቢት ሞባይል ጠጋኝ 16ኛ- አበርብር ወንድም ሲገኝ ከበደ ከሽዋ ሮቢት ስራ ነጋዴ። ብአዴን ወንጀል የፈፀመ ካለ በክልሉ ውስጥ ይጠየቃል እንጅ አንድም የአማራ ተወላጅ ከአማራ ክልል ተላልፎ ለፌደራል መንግስትም ሆነ ለሌላ ክልል አይሰጥም በማለት በአደባባይ ቃል ገብቶ ነበር ። ዛሬ አርሶ አደሮችን እና ግብር ከፋይ ነጋዴዎችን ጭምር የኦሮሞ ብልፅግና በነፃነት አፍኖ እንዲወስድ ተባባሪ በመሆን በወገኖቻችንን ላይ ግፍ እንዲፈፀምባቸው እያደረገ ነው ። እነዚህን ወንድሞቻችንን የሚያውቅ ሰው ቤተሰቦቻቸው በፍለጋ ላይ ስለሚሆኑ ያሉበትን ቦታ እና ሁኔታ አሳውቋቸው ።
إظهار الكل...
"ፍረጃው ሳይጀመር ሕዝብን ማንቃት ያስፈልጋል" ምስጋናው አንዷለም ብልጽግና ከኤርትራ ጋር ጦርነት መግጠሙ አይቀሬ ነው፡፡ የኦነግ ህልም የሚሳካው አማራና ኤርትራ ደካማ ወይም የተሸነፉ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ ደካማ አማራና ኤርትራ ማለት ኦነግ ወደብ አገኘ ማለት ነው፡፡ ኦነግ ወደብ ከያዘ በኋላ አማራ ለስንት ወር ይኖራል የሚለውን ብቻ ነው ማሰብ የምንችለው፡፡ ኦነግ የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ አጀንዳ የለውም፡፡ ከኤርትራ ጋር አደርገዋለሁ የሚለውም ጦርነት የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ አይደለም፡፡ የራሱን የኦነግ አላማ ለማሳካት ነው፡፡ በአሁኑ ሰአት ህወሀት በሻእብያ ተወሰዱብኝ የሚላቸውን ሹካና ማንኪያዎች ለማስመለስ በሚል የበቀል ስሜትና እና ከኤርትራ የሚችለውን ያህል ቦታ በመውረር ትግራይን እንደ አገር ለመመስረት አልሞ እየሰራ ነው፡፡ ይሄ ጦርነት በኦነግ እና ህወሀት አሸናፊነት የሚጠናቀቅ ከሆነ ትልቅ ከሳሪዎች አማራና ኤርትራ ናቸው! ይሄ የኦነግ እና የህወሀት አላማ ኢትዮጵያን በየበኩላቸው መቀራመት ነው፡፡ አዲስ አበባ አትገባም፣ ማዳበሪያ አታገኝም፣ ሾፌር ሆነህ አትበላም፣ ወለጋም፣ አዲስ አበባም የትም አገርህ አይደለም እየተባለ የሚገደል፤ የሚፈናቀልና የሚዘረፍ ህዝብ እና ይሄንኑ የሚያደርገው ኦነግ ተመልሶ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ቆሜያለሁ ሲል የክፍለ ዘመኑ ታላቅ ስላቅ ከማለት ውጭ ሌላ መግለጫ ቃላት አናገኝለትም፡፡ በኋላ በባንዳነት ፍረጃው ሳይጀመር ከአሁኑ ህዝብን ማንቃት ያስፈልጋል፡፡ የአማራ ህዝብም ሆነ ኢትዮጵያ አገሬ ናት የሚለው ህዝብ ይሄንን የኦነግ ጦርነት እንዳይደግፍ ከወዲሁ መቃወም ግድ ይለዋል፡፡ በኋላ "አብይ ሳምባየ ነው" እያለ እስክስታ ከመታ በኋላ በጠኔና በኦነግ ዱላ እንደተጣመመ ሁሉ፤ አሁንም ህዝቡ የኦነግ ዱላ ሆኖ ራሱን በራሱ እንዳያጠፋ ማንቃት ያስፈልጋል፡፡ Dr Mesganaw Andualem
إظهار الكل...
👍 3
እርፍ የጨበጠ ገበሬ፤ መስቀል የያዘ ካህን፤ ከመስገጃ ምንጣፍ ውጪ ምንም ያልታጠቀ ንፁህ ሙሚን፤ በየትኛውም የዕድሜ ክልል የሚገኙ ህፃናት፤ ከነፍሰ ጡር እስከ ወላድ ሴቶች፤ በማህፀን ያለ ፅንስ፤ የእምነት ቦታዎች፤ የትምህርትና የህክምና ተቋማት፤ የመንገደኞች ማመላለሻ መኪኖች፤ የመኖሪያ ቤቶች፤ አዋሳኝ ክልሎች እነዚህና ሌሎችም የወንበዴው የብልፅግና ስብስብ የተቀናጀ ጥቃት ሰለባዎች ሆነዋል። ይሄ ስልጣን ላይ ለመቆየት የሚደረግ ስራ ሳይሆን "እኛ" በሚል category ውስጥ ካካተቱት በቀር ማንም መብቱን የመጠየቅ ሞራል እንዳይኖረው የማድረግ ዕቅድ ነው። እውነታው የቆሙለት ህዝብ የሌላቸው፤ ሀገር የማፍረስ አጀንዳ ባላቸው ስብስቦች መሐል እና በመላው ኢትዮጵያዊ መካከል የሚደረግ ፍልሚያ መሆኑ ነው። የዚህ ዓላማቸው ቁጥር አንድ ጠላት ተደርጎ የሚታሰበው የአማራ ህዝብ ከማጉረምረም ባለፈ እንዲህ ያለው አገዛዝ በእርግማን እንደማይናድ አውቆ የጀመረውን ሁለገብ ትግል ሌላው ህዝብም በገባው መንገድ ተቀላቅሎ ራሱን እና ሀገርን ነፃ ሊያወጣ የሚገባበት ጊዜ ነው። ድል ለአማራ !! https://t.me/nefitgnawamhara #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide
إظهار الكل...
ነፍጠኛው አማራ

አማራ ያሸንፋል !

👍 7👎 1
ብልጽግና በግፍ ያሰራቸውን የአማራ ልጆች ጥፍራቸውን እየተነቀለ ቶርች እያደረገ ነው          ..................... ‹‹የደረሰብንን ስቃይ ቃላት አይገልጹትም፤ በኤሌክትሪክ ቶርች ተደርገናል፣ ጥፍራችን ተነቅሏል፤ በቀዝቃዛ ውሃ እየተነከርን ተገርፈናል፤ አሁንም በአፍና በአፍንጫችን ደም እየፈሰሰን ነው›› በፌደራል ፖሊስ የሚገኙ እስረኞች የሰብአዊ መብት ጥሰት መፈፀሙን ኢትዮ 251 ሚዲያ በደሠሰው መረጃ መሠረት አዲስ አበባ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን በሚገኘው እስር ቤት የኢትዮ 251 ሚዲያ ዘጋቢ  ተገኝቶ የደረሰባቸውን ሁሉ  ጠይቆ ያጠናቀረው ዘገባ ነው። ለኢትዮ 251 ሚዲያ አስተያየታቸውን የሰጡት ግፉኣን የሚከተለውን ብለውናል፡፡ እኛም ጥሬ ሃቆቹን እና ዘጋቢው የተመለከተውን ብቻ ወደ እናንተ አቅርበናል። 👉 ‹‹የደረሰብንን ስቃይ ቃላት አይገልጹትም፡፡ አሁን ስንታሰር ህዝቡ ሊጨነቅ ይችላል፡፡ ለእኛ ግን  በማሰቃያ ቦታው የደረሰብንን ስንመለከት ይህ ፖሊስ ጣቢያ የቅንጦት ቤታችን ነው›› የአንደኛው አስተያየት፤ 👉 ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ደግሞ፤ ‹‹በደረሰብኝ ድብደባ መተንፈስ ተቸግሬያለሁ›› ሲል ተናግሯል፡፡ ዘጋቢያችን በአካል ተገኝቶም የኢንጂነሩን ስቃይ ተመልክቷል፡፡ 👉 በአይን እንደተመለከትነው አንዷ እህታችን እስካሁን በአፍና በአፍንጫዋ ደም እየፈሰሳት ነው። 👉 በግርፋት ብዛት ራሳቸውን የሳቱና ምግብ መመገብ የማይችሉ አሉ፡፡ በኤሌክትሪክ ቶርች የተደረገ አለ፤ በቀዝቃዛ ውሃ እየተነከረ የተገረፈም አለ፣ ጥፍሩ የተነቀለም አለ፡፡ ይህን ሁሉ ግርፋት መቋቋም ያልቻሉ ወንድሞቻችን ምግብ መመገብም ሆነ ራሳቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው እላያቸው የሚጸዳዱም አሉ፡፡ "የእኛ ስቃይ የማይታያቸው ገራፊዎቻችን ሆን ብለው ህክምና ከልክለውናል"፡፡ 👉 በተጨማሪም፤ ‹‹28ታችን ወደ ፖሊስ ጣቢያ መጣን እንጂ አሁንም በማሰቃያ ቤቱ መከራቸውን እያዩ ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ወንድሞቻችን አሉ፡፡ እነዚህ ወንድሞቻችን ከአጣዬ፣ ሽዋሮቢት፣ ቆቦ፣ ወልድያ፣ ጎጃም፣ ጎንደር እና አዲስ አበባ በግፍ ታፍነው የተወሰዱ ናቸው፡፡ <<የሀይማኖት አባቶች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የሀገር ሽማግሌዎች የሚባሉት እውነት ካሉ፤ አሁን መጥተው ያለንበትን ይመልከቱ>> ሲሉ በጋራ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ እነዚህ 28 የአማራ ተወላጆች ከ13 ቀን እስከ 21 ቀን በጨለማ ክፍል ውስጥ እንደነበሩ እና ከዚህ ሁሉ ግፍ እና ስቃይ በኋላ ወደ ፌድራል ፖሊስ ኮሚሽን ወደ ሚገኘው እስር ቤት እንደተዛወሩ ገልጸዋል። ውድ የኢትዮ 251 ሚዲያ ቤተሰቦች በዚህ ጉዳይ ላይ ተጨማሪ ማጣራት እና ተከታታይ ዘገባ ወደ እናንተ እንደምናደርስ እንገልጻለን። ዘገባው የኢትዮ 251 ሚዲያ ነው ድል ለአማራ‼️ ሞት ለፋሽዝምና ለአገዛዙ‼️ #AmharaStruggle #Justice4Amhara #AmharaGenocide @Akingmakers @amharainternational @informamhara
إظهار الكل...
👍 3😢 2
Photo unavailableShow in Telegram
የሸዋ እና የጎጃም አማራ አካባቢዎች ባለፉት ሳምንታት " መከላከያ ሰራዊት " በሚባለው የመንግስት ታጣቂ ሀይል ከፍተኛ ጥቃት ተፈጽሞበታል። ሸዋሮቢት፣ ማጀቴ እና አካባቢው በድሮን ሳይቀር ተደብድቧል። በምስራቅ ጎጃም ደብረ ኤልያስ ገዳም ተደብድቧል። የሸዋሮቢት ነዋሪዎች ዘረፋ እና ሌሎች አስነዋሪ ወንጀሎች ተፈጽሞባቸዋል። በሸዋሮቢተ ያሉ ሽማግሌዎች ለምን < ፋኖን የማጥፋት ዘመቻ አትደግፉም > በሚል ክስ በምስለኔ ጀነራሉ ትዕዛዝ ታፍሰው ታስረዋል። ዛሬው በኦሮሚያ የተካሄደው የካድሬ ሰልፍ ይህን በመደገፍ የተደረገ ነው። የአብይ መንግስት ጸንቼ የምቆመው " አማራን በመስበር ነው " የሚል ትልሙን የሚደግፍ ሰልፍ ነው የተካሄደው፤ ጥላቻን፣ ፋሽዝምን የሚደግፍ ሰልፍ ነው። የብልጽግና ጸረ ህዝብነት ዛሬ ለአብዛኛው ግልጽ ሆኗል። የአማራ ተጋድሎም የተጫነበትን ፋሽስታዊ የባርነት ቀንበር የመስበር እና የፍትህ መሆኑ ሀቅ ነው። እናም የሚደናገር እና ሆ ብሎ ለጥፋት የሚሰለፍላችሁ አይኖርም። ይህ መጥፊያችሁ ነው፤ እኛ ደግሞ ቀጭዎቻችሁ ነን። ድል ለአማራ ! #AmharaStruggle
إظهار الكل...
👍 1👏 1
ፋሺዝምን በመደገፍ ሰልፍ ሊካሔድ ነው!! ከነገ ወዲያ እሁድ ፋሽስትና ፀረ ድሃው የኦሕዴድ ብልፅግና የሚያስተባብረው ሰለፍ ይደረጋል። ኦህዴድ ሰልፉ በመላው ኦሮሚያ እንዲካሄድ ያቀደ ሲሆን ለመዋጥ እያዘጋጃቸው ባሉት ሲዳማና ሀረሪም ሰልፉን ለማስደረግ እያዘዘ ነው። የሰልፉ ዓላማ ከመከላከያ ሠራዊት ጎን እንቆማለን በሚል ሽፋን የተዘጋጀ ቢሆንም በዋናነት ግን ቢጠጋገንም መቆም ያቃተውን የአብይ ፋሽስታዊ ስርዓት ለመደገፍ መሆኑ ታውቋል። የኦሮሙማው ገዳይና አሳዳጅ አገዛዝ የኦሮሞን ሕዝብ በማያምንበት ሰልፍ በመደለልና በማስፈራራትም ጭምር እንዲወጣ አድርጎ መከላከያን እንደግፋለን በሚል ሰበብ አማራን ለማውገዝ አቅዶ የጠራው ሰልፍ እንደሆነ ምንጮች ጠቁመዋል። በአማራ ክልል ከተሰማራው የመከላከያ ኃይል መካከል በሕወሓት ስንጠቃ የደገፈንን ሕዝብ አንወጋም፣ በአንድ ምሽግ ከነበርነው ልዩ ኃይልና ፋኖ ጋርም አፈሙዝ አንዟዟርም የሚል በመብዛቱ የደነገጠው የፋሽስቱ አብይ አገዛዝ በዘረኝነት ያበደውን የኦሮሚያ ልዩ ኃይልና የኦነግ ታጣቂ የመከላከያ ዩኒፎርም እያለበሰ ወደ አማራ ክልል ማዝመቱና ጦርነት መክፈቱ ይታወቃል። አሁን ደግሞ በተጨማሪ ሴራ ሕዝብን ለማፈን ያቀደው የእነ ብርሃኑ ጁላ ዘረኛ የኦሮሙማ ስርዓት አማራ ላይ የዘር ማፅዳት እርምጃው እንዲጠናከር በማሰብ መከላከያውን ከሕዝቡ ጋር የበለጠ ቅራኔ ውስጥ ለማስገባት እየሰራ ነው። በሰልፉ አማራን የሚያንቋሽሽና ፅንፈኛ የሚል መልዕክት ጎልቶ እንዲሰማና አማራን ከተቀረው ሕዝብ ለመነጠል ቢታቀድም አማራም ሆነ መላው ኢትዮጵያዊ የአገዛዙን ነውረኝነት ስለተረዳ የሚሳካለት አይሆንም። ይህን ቀድሞ የሚያውቀው አብይና ፋሽስታዊ ስርዓቱ የሚይዘውና የሚለቀው ጠፍቶታል። የመንግሥትና ብልፅግና ፓርቲ ሚዲያዎች ለሰልፎቹ ልዩ ትኩረትና ስምሪት እንዲያደርጉ ታዘዋል። https://t.me/nefitgnawamhara ድል ለአማራ !! #AmharaStrughle #Justic4Amhara #AmharaGenocide
إظهار الكل...
ነፍጠኛው አማራ

አማራ ያሸንፋል !

Photo unavailableShow in Telegram
የአሁኖች የአማራ ብልጽግና አመራሮች በተለይ ዶ/ር ይልቃል እና ስብስባቸው ከመሠረታዊ የፖለቲካ መርህ የተፋታ፣ የሕዝባቸውን ጥያቄ ፈፅሞ ለመረዳት ፍላጎት የሌላቸው ድኩማኖች ናቸው። የፖለቲካ ሀ ሁ ያልቆጠሩ፥ የፖለቲካ ሽፍታዎች ናቸው። ለዚህም ነው የመጣው የሄደው ሁሉ ባለቤት እንደሌላት የህዳር አህያ የፈለገውን ነገር የሚጭንባቸው። በነገራችን ዶ/ር ይልቃል "እኔና ባልደረቦች ከፈለግን ስልጣን እንለቃለን።" ሲሉ ሰማኋቸው፤ ካልፈለግን ግን ማንም አያወርደንም መሆኑ ነው። እኔ ግን ለፖለቲካ ሽፍታዎቹ የምነግራችሁ ነገር እና እናንተም የምታውቁት ተገዳዳሪ ኃይል ተፈጥሯል። ይሄ ኃይል ተገዳዳሪ ኃይል ብቻ ሳይሆን አሸቀንጥሮ መጣል የሚችል ሶስተኛው የአማራ ብሔርተኝነት ኃይል ነው። ይሄ ሶስተኛው የአማራ ብሔርተኛ ኃይል ስልጣናችሁን መቀማት ብቻ ሳይሆን፤ በራሱ እና በሕዝቡ ላይ መዝግቦ የያዘ ስለሆነ እንደ እስራኤሏ የቀድሞ መሪ ጎልድ አሚሪ "የአምላክ መቅሰፍት ዘመቻ" ሕዝባችሁን በበደላችሁት መጠን እና ዋጋ ምላሽ ይሰጣል። ድል ለአማራ‼️ https://t.me/nefitgnawamhara #AmharaGenocide #Justuce4Amhara #AmharaStruggle
إظهار الكل...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.