cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

አርባምንጭ መድኃኔዓለም ማኅበረ እስጢፋኖስ

"ናሁ ሠናይ ወናሁ አዳም ሶበ ይሄልዉ አኃው ኅቡረ" መዝ ፻፴፪÷፩ "ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ እነሆ መልካም ነው እነሆ ያማረ ነው።"

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
387
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+77 أيام
+3030 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

"ሐምሌ 5 ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወ ጳውሎስ የእረፍታቸው መታሰቢያ እለት ነው" ዳግመኛም በዚህች ቀን የሐዋርያት ፆም ፍስክ ነው። እንዲሁም በዚህች ቀን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አመታዊ በዓላቸው ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ:-በአባቱ የሮቤል በእናቱ የስ ምኦን ነገድ ሲሆን የተወለደው በገሊላ አውራጃ በቤተ ሳይዳ ነው።ወላጆቹ ያወጡለት ስም "ስምኦን" ነበር ኋ ላም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ"ጴጥሮስ" ብሎ ጠርቶታል።ትርጓሜውም " አለት " ወይም ደሞ፤ መሰረት ማለት ነው። ቅዱስ ጴጥሮስ መተዳደሪያው አሳ አጥማጅነት ነበር ነገር ጌታ ጴጥሮስን ሰዎችን በወንጌል መረብ እያጠ መደ ወደ ክርስትና መንገድ ይመልስ ዘንድ ጌታችን ለ ሐውርያነት ጠርቶታል።ሉቃ 5 : 10 ማር 1: 16 ቅዱስ ጴጥሮስ በመንፈሳዊ ቅንአቱና ለጌታችን በነበ ረው ፍቅር የተነሳ የሐዋርያቱ አለቃ ሆኖ ተሹሞአል። ለአገልግሎት ከመጠራቱ በፊት በሮም,በእስያ,በሰማርያ ,በልዳ,በአንጾኪያ,በኢዮጴ,በገላትያና በሌሎች ሀገሮች፤ እየተዘዋወረ ወንጌልን ሰብኳል። በስብከቱ ምክንያት ልዩ ልዩ መከራን ተቀብሏል።በክር ስቶስ ሀይልና አጋዥነት ብዙ ድንቅ ተአምራትን አድርጓል ከተሰጠው ፀጋ ብዛት የተነሳ በጥላው ሕሙማንን ይፈ ውስ ነበር።ሐዋ 5 :15 ሐዋርያው በመፅሐፍ ቅዱስ ፤ በስሙ ሁለት መልዕክታት ፅፋል 1ኛጴጥሮስ እና 2ኛ ጴጥሮስን እንዲሁም በተጨማሪ በቃል አስተምሯል። ቅዱስ ጴጥሮስ የአገልግሎት ዘመን ማብቂያ ሲቃረብ በሮም ንጉስ አካይያ ስቃይ ደረሰበት በዚህም ቅዱስ ጴጥሮስ ሮማዊ ባለመሆኑ በግርፋት በስቅላትና በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበት። በዚህም እንደ ስርአታቸው ቅዱስ ጴጥሮስን ከገረፉት በሁዋላ ሊሰቅሉት ሲሉ ወታደሮቹን እንደ ክብር ጌታ አ ቁማቹ ሳይሆን ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ አላቸው።እነርሱም እንዳላቸው ዘቅዝቀው ሐምሌ 5 ቀን ሰቅለውታል ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ:-የተወለደው ጠርሴስ ከተማ ሲሆን ጠርሴስ በንግድ አለም የታወቀች የኬልቅያ ዋና ከተማ ነበረች። የትውልድ መሠረቱ ከ እብራዊያን ከብንያም ነገድ ነበር።አባቱ በዜግነት ሮማዊ ናቸው። ቅዱስ ጳውሎስ በ15 አመቱ ወደ ኢየሩስአሌም በመመለስ ከ ገማልያ የአይሁድን ሕግ ስርአት ጠንቅቆ ተምሯል። በ30 አመቱ የአይሁድ ሸንጎ አካል ሆኖ ተቆጥሮአል። በአይሁድ ሸንጎ አባልነት ለሁለት አመት ከሰራበት በሁ ዋላ ለኦሪት እምነቱ ቀናተኛና ፈሪሳዊ በመሆኑ ክርስቲያ ኖችን በማንኛውም አጋጣሚ ይቃወምና ያሳድድ ነበር ቅዱስ ጳውሎስ ክርስቲያኖችን ሊያሳድድ ሲሄድ ድን ገት ታላቅ ብርሀን መጥቶ ሳወል ሳወል ለምን ታሳድደኛ ለህ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ።ቅዱስ ጻውሎስ ጌታ ሆይ አንተ ማነህ ብሎ በጠየቀ ጊዜ አንተ ምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ አለው። ቅዱስ ጳውሎስ ከዛ በሁዋላ በሀናንያ ከተጠመቀ እና ከተማረ በሁዋላ አይሁድ ለኦሪት ሕግ ሲቆረቆር የነበረ ው አሁን ደሞ ስለወንጌል ሲሰብክ በማየታቸው አይሁ ድ ሊገሉት ፈለጉ:እርሱ ግን ገላትያ,ጤሮአዳ ,ቆሮንቶስ, ኤፌሶን ,ልስጥራ እና ሌሎች ከተሞች ሲያስተምር ቆየ በመጨረሻም በክርስቲያኖች ላይ ሞት ታውጆ ስለነ በር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከተማ ላይ ተይዞ 2 አመት ከ 7 ወር በ እስር ቤት ከቆየ በሁዋላ በሮም ከተ ማ በኦስትያ መንገድ አንገቱ ተሰይፎ ሐምሌ 5 ቀን በሰማዕትነት አርፏል። https://www.facebook.com/100086666611607/posts/pfbid035PX5nZnyurD6QYGRYHJ2WayXDEGf22KTtCkUoereZ7TRsxTYCBo4rpJ2aPswfxovl/ አርባምንጭ መድኃኔዓለም ማኅበረ እስጢፋኖስ
إظهار الكل...

ሐምሌ 5 2016 ዓ.ም እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ እና ለብርሃናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓለ ንግሥ አደረሳችሁ። በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ እና በአቅራቢያ የሚገኙ የጻድቁን እና የሰማዕታቱን በዓለ ንግሥ የሚያከብሩ አድባራት በተወሰነ መልኩ ለመጠቆም ያክል እንዲሁም እናንተ ምዕመናን የምታውቋቸውን ከእነ አድራሻቻው ኮሜንት ላይ በማስቀመጥ ለምዕመናን እንጠቁም ፦ ➨የኦቾሎ አቦ ➨የዚጊቲ አቦ ➨የጋቶው አቦ ➨ገረሴ ወረዳ ዳንቢሌ አቦ ➨ከምባ ወረዳ ጳሳ ቢልቦ አቦ የጻድቃኑ በረከት እና ምልጃ ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን https://www.facebook.com/100086666611607/posts/pfbid0ut7p3HPxAemRQbZY7Vp6D9zQSWt8ZWQZS58gqmhun3Zss1ax2zc7vbuRoHKZAcfZl/ አርባምንጭ መድኃኔዓለም ማኅበረ እስጢፋኖስ
إظهار الكل...
ቀሲስ ኢንጅነር ገዳሙ አድማሱ የአርባምንጭ ደብረ ጸሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና የደብረ ሎዛ ቅድስት ኪዳነምህረት አብያተክርስቲያናት አስተዳዳሪ። አባቶቻችን ቤተክርስቲያንን እንዲመሩ የረዳቸው እና ያጸናቸው መንፈስ ቅዱስ ከእርሶ ጋር ይሁን። አርባምንጭ መድኃኔዓለም ማኅበረ እስጢፋኖስ
إظهار الكل...
ሰኔ 30 የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓለ ንግሥ በአርባምንጭ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ብፁዕ አባታችን አቡነ ኤልያስ በተገኙበት እንዲሁም በገረሴ ዛዝኤ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከብሯል ። እሁድ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም https://www.facebook.com/share/p/dd6CZrmCS5hank2U/?mibextid=oFDknk አርባምንጭ መድኃኔዓለም ማኅበረ እስጢፋኖስ
إظهار الكل...
👏 3
"እንኳን ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ" "ነገ ሰኔ 30 የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የልደት በዓለ ለማክበር ከተሰናዱት በአርባምንጭ እና በአርባምንጭ ዙሪያ አድባራት መካከል:- -አርባምንጭ ደ/መ/ድኃኔዓለም ካቴድራል -ገረሴ ዛዝኤ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን በዋነኝነት ይጠቀሳሉ ሌሎች አድባራትንም እናንተ ማኅበረ ምዕመናን በኮሜንት መጻፊያ ላይ የምታውቋቸውን አድባራት ማስተዋወቅ ትችላላቹ። https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid028YzQKdAp8PK6hkLbqNKcmsv922WNHRgzrcuQoTVJohJJaEQCmiDnMfmv5NihJKv4l&id=100086666611607&mibextid=Nif5oz አርባምንጭ መድኃኔዓለም ማኅበረ እስጢፋኖስ
إظهار الكل...
👍 4
Photo unavailableShow in Telegram
ዲ/ን አስራት ላካ የአርባምንጭ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል አገልጋይ ከሚዛን ቴፒ ዩንቨርሲቲ በከፍተኛ ውጤት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ። https://www.facebook.com/100086666611607/posts/pfbid0GYhLsfkjtxTyFKFwGUiFMAkg7c9iw9ZPQyt4RYbSK6gg3wr7dBRkpMy8P8bM1MiHl/ አርባምንጭ መድኃኔዓለም ማኅበረ እስጢፋኖስ
إظهار الكل...
👍 6👏 2
Photo unavailableShow in Telegram
"መድኃኔዓለም" መኑ ከማከ መሐሪ፤ሐረገ ነፍስ መታሪ ወልሳነ ኵሉ አሣሪ፤ክረምተ ወሐጋየ ዘታስተባሪ፤በሥጋከ ወደምከ፤ኃጣውኢነ አስተሥሪ። https://www.facebook.com/100086666611607/posts/pfbid02Wb5JyjuyKNk1Dba4hSk5k5vbB6UmvtZLhJw1H9452KzCkMyrUgLjtHgBrhTEZR8ol/ አርባምንጭ መድኃኔዓለም ማኅበረ እስጢፋኖስ
إظهار الكل...
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.