Save Amhara Fano 💚💛❤️
الذهاب إلى القناة على Telegram
የተቀደሰን ነገር በእግሩ ለሚረግጥ ፥ ተመልሶም ያጎረሰውን እጅ ለሚናከስ ርኩስ መጫወቻ የማይሆን የነቃ ማህበረሰብ እስክንፈጥር ድረስ ብዕራችን አይነጥፍም።
إظهار المزيد785
المشتركون
-224 ساعات
-57 أيام
-2430 أيام
أرشيف المشاركات
የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክ/ጦር አትሮንስ ሻለቃ ደፈጣ በመጣል በአገዛዙ ሰራዊት ላይ የማያዳግም እርምጃ ወሰደች!
አፋብን ወሎ ቤተ_አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክ/ጦር የአትሮንስ_ሻለቃ ተናዳፊ ተርቦች በኦህዴድ/ብልፅግና ወንጀለኛ ቡድን ሥልጣን ጠባቂ ቅጥረኛ ኃይል ላይ ደፈጣ በመጣል የክ/ጦርና የሻለቃ አመራሮችን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ከፍተኛ ሰብዓዊ ኪሳራ አድርሰውበታል።
04/11/2018 ዓ.ም በአምሓራ ሳይንት ሰማይ ስር እፁብ ድንቅ ተብሎ በተመሰገነውና ድንገተኝነትን ባተረፈው የደፈጣ ጥቃት ከደንሳ ከተማ ወደ በለጩማ በ 7 መኪና ሲጓጓዝ የነበረ ወራሪ ኃይል ልዩ ቦታው ወጀድ መገንጠያና ጎዴል በተባሉ ስትራቴጅክ ቦታዎች ላይ የአትሮንስ ሻለቃ ትንታጎች አከርካሪውን በማድቀቅ አሽመድምደውታል።
በዚህ አስደናቂ ጥቃት ክ/ጦር ዘመቻ ኃላፊ ሻለቃ ወልደ ጊዮርጊስና የሻንበል ማዕረግተኛ የሆነው አስራት ከባድ ቁስለኛ ሲሆኑ ሌላኛው ማዕረጉ ለጊዜው ያልታወቀ መስመራዊ መኮነን እስከ አጃቢው ለዘላለም ማሸለቡ ታውቋል።
አመራሮቹን አጅበው በፓትሮልና በካሶኒ ታጭቀው ሲጓዙ ከነበሩት በአልታሰበና ድንገተኛ የቦንብና የጥይት ጥቃት ተጋላጭ በመሆናቸው አያሌ ቁጥር ያላቸው መሠረታዊ ወታደሮች ለኦህዴድ/ብልፅግና ወንጀለኛ ቡድን ሥልጣን ለመጠበቅ ሲባል የመስዋዕት በግ ሆነው ወደከርሰ_መቃብር በመውረድ በአፍንጫቸው አፈር ፈሷል።
የክ/ጦር ዘመቻ ኃላፊው ሻለቃ ወልደ ጊዮርጊስ አጃቢ መሠረታዊ ወታደር ከድር ጀማል ከቀናት በፊት ወደ ፋኖ መኮብለሉ የሚታወቅ ነው። ዛሬ ደግሞ ሻለቃ ወልደ ጊዮርጊስና ሌሎች የክ/ጦርና የሻለቃ አመራሮች በከፍተኛ አጀብ ተከበው ለመንቀሳቀስ ቢሞክሩም እነሆ ከመቅሰፍቶቹ የጥይት ሀሩር ግን ማምለጥ አልቻሉም።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!!
ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ_አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
05/11/2018 ዓ.ም
ፋኖ ማርኮ ማሳከሙ፡ የሰብአዊነት እና የጀግንነት መገለጫ ነው።
በጦርነት አውድ ውስጥ ድልን መቀናጀት የአንድን ኃይል ወታደራዊ ብቃት ሊያሳይ ይችላል፤ እውነተኛውን የሞራል ልዕልና እና የውስጥ ጥንካሬ የሚያሳየው ግን ከተኩስ ማቆም በኋላ በምርኮኞች ላይ የሚታየው አያያዝ ነው። የፋኖ አባላት፣ በተለይም በናደው ክፍለ ጦር ስር የሚንቀሳቀሱት ኃይሎች፣ የገጠማቸውን ጠላት ማርከው ከማስቀመጥ ባለፈ፣ የቆሰሉትን በፍቅር እና በርህራሄ ሲያክሙ ታዬታቸው የታሪክ አዲስ ምዕራፍ ነው።
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘረያዕቆብ ኮር ናደው ክፍለ ጦር አባላት የሚመሩበት የቆየው የኢትዮጵያዊነት የቆራጥነት እና የቸርነት እሴት ነው። ማርኮ ማሳከም እንዲሁ ለፕሮፓጋንዳ የሚደረግ ሳይሆን፣ ከተኩስ መስመር በስተጀርባ ያለውን የሰው ልጅ ሕይወት የማክበር ጥልቅ ስሜት ነጸብራቅ ነው። ጠላት በጦር ሜዳ ላይ እያለ የጥፋት መሣሪያ ቢሆንም፣ እጅ ከሰጠና ከተማረከ በኋላ ግን ሰብአዊ ፍጡር መሆኑን በመረዳት ፈጣን የሕክምና እርዳታ እንዲያገኝ ማድረግ ፍጹም ስልጣኔን ያሳያል።
በተለያዩ ግንባሮች የሚንቀሳቀሰው የናደው ክፍለ ጦር፥
▸የቆሰሉ ምርኮኞችን ልክ እንደገዛ ጓዶቻቸው እኩል በመንከባከብና መድኃኒት በመስጠት ሕይወታቸውን ታድጓል።
▸እንደ አገዛዙ ብልፅግና በጥላቻና በጦርነት ስሜት ሳይታወሩ፣ ከበርካታ ሙት ውስጥ ፈልፍለው ባወጧቸው ቆስለው በተማረኩ በጦር ምርኮኞች ላይ ሰብአዊነት የተሞላበት አያያዝ በማድረግ የትግሉን ንጽህና አስመስክሯል።
▸ይህ ድርጊት ፋኖ የሕዝብ ልጅ፣ የፍትሕና የሰብአዊነት ዘብ እንጂ የጥላቻ ኃይል ወይም የሞራል ዝቅተት ያለበት እንዳልሆነ በተግባር ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው።
እውነተኛ ጀግንነት ጠላትን ማሸነፍም ሲሆን፣ ካሸነፉት በኋላም ሰብአዊነቱን ጠብቆ ማኖር ነው።
የናደው ክፍለ ጦር ያሳየው ይህ አኩሪ ተግባር በታሪክ መዝገብ ላይ የሚቀመጥና የፋኖን የሞራል ልዕልና ለዓለም የሚያሳይ ደማቅ አሻራ ነው።
Akeber Smegnew
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ የ303ኛ አሳምነዉ ኮር ከ55 በላይ ጠላትን በመደምሰስ እና ከ40 በላይ ጥቁር ክላሽን በመማረክ ታላቅ ድልን ተጎናጽፈዋል!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል የሆነው 21ኛ(ተከዜ) ክፍለ ጦር ፋኖዎች ራሱን 90ኛ ክፍለ ጦር ብሎ የሚጠራው ከኩልመስክ፣ ከ61ኛ ክፍለ ጦር ሁለት ሻለቃዎችን ይዞ ከላሊበላ ከተማ የተንቀሳቀሰውን የብልፅግና ሰራዊትን ስቦ ወደ መግደያ ቦታ በማስገባት አይቀጡ ቅጣት ቀጥተውታል።
ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ/ም መነሻውን ኩልመስክና ላሊበላ ከተማ አድርጎ ወደ ገነተማርያም የተንቀሳቀሰው የጁላ ሰራዊት በዙ-23 እና በ107 የታገዘ ውጊያ ቢያደርግም መሃል ላይ ስቦ በማስገባት የቆረጣ መሀንዲሶቹ 21ኛ(ተከዜ) ክፍለ ጦር መሀል ከበባ ውስጥ በማስገባት አኩሪ ድል አስመዝግበዋል።
በዚህ አውደ ውጊያ ከ55 በላይ የጠላት ኃይል ሲደመሰስ፣ ከ30 በላይ የቆሰለ፣ 42 ጥቁር ክላሽና አንድ ሬድዮ መገናኛ፣ 27 የደረትና የወገብ ትጥቅ፣ 36 ወታደራዊ ሻንጣ ተማርኳል።
በተያያዘ መረጃ አንድ የመከላከያ ሰራዊት አባል ዛሬ መነሻውን ከላሊበላ ከተማ በማድረግ አንድ ጥቁር ስናይፐርና አንድ ጥቁር ክላሽ በመያዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር 16ኛ ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ ክፍለ ጦርን ተቀላቅሏል ሲል የ303ኛ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!
ሐምሌ:- 04/ 2018 ዓ/ም
ሰበር የድል ዜና ❗❗
ከኮላሽ ተራራማ ስፍራ እስከ አለም ከተማ ጫፍ በናደው ክፍለጦር ታሪክ ሰራ!
ሐምሌ 04 ቀን 2018 ዓ.ም
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት — አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ናደው ክፍለ ጦር በመርሐቤቴ አውራጃ በታሪካዊቷ የኮላሽ ተራራማ ስፍራና በአለም ከተማ ዙሪያ ሰፍሮ በነበረው የብልፅግና አገዛዝ ሰራዊት ላይ የናደው ክፍለጦር ጀግኖች መብረቃዊ ጥቃት በመሰንዘር አኩሪ ድል አስመዝግበዋል።
ዛሬ ከሌሊቱ 10:00 ጀምሮ በላይ ቤት ኮላሽ ተራራ ላይ የገባው የክፍለጦሩ ሻለቃ የጠላትን የቁም ምሽግ ሙሉ በሙሉ በመበተን አካባቢውን በቁጥጥሩ ስር በማድረግ ፤ በተጨማሪም በዞማ ዙሪያ እና ከአለም ከተማ መውጫ በአከያ መስክ ላይ የሠፈረውን የጠላት ኃይል ሌላኛዋ የክፍለጦሩ ሻለቆች በቅንጅት ተቆልፎ የተያዘ ሲሆን፣ በተደረገው የጨበጣ ውጊያ የጠላት ክፉኛ ተመቷል። በዚህ አስደናቂ ውጊያ አንድ ሙሉ የአገዛዙን ታጣቂ የጫነ ኦራል ተሽከርካሪ ልዩ ስሙ ዘይታ በተባለ ቀበሌ በቦንብ ተመቶ ከነጫነው የሰው ሀይል ወደ አመድነት ተቀይሯል።
ሽንፈቱን ተከትሎ ከፌጥራ እስከ አለም ከተማ ያለውን ጥምር ኃይል በማንቀሳቀስ የኮላሹን ኃይል ለመታደግ የሞከረው የጠላት እቅድ፣ በአለም ከተማ አቅራቢያ በተጣለበት አስደንጋጭ ደፈጣ መክኗል። በአሁኑ ሰዓት ጀግኖቹ ቦታቸውን ይበልጥ እያሻሻሉ ሲሆን፣ በጀግኖቹ የአልሞ ገዳይ (ስናይፐር) ቡድን ክፉኛ የተመታውና የተበታተነው የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛውን ለመሰብሰብ በመወራጨት ላይ ይገኛል። ነገር ግን ከጀግኖቹ ባሩድ የተረፈ የለም።
የጠላት ኃይል በኮላሽ ተራራማ ቦታ ከአመራሮቹ ጋር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የተደመሰሰ ሲሆን፣ የሚከተሉት ወታደራዊ ቁሳቁሶች እና የጠላት ሀይል በጀግኖቹ ቁጥጥር ስር ውለዋል፦
✔ 03 የኮማንዶ አመራሮች ተማርከዋል
✔.01 ብሬን (ከነሙሉ ሸንሸሉ)
✔.07 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ
✔.03 ማውዘር (መንቶፍ)
✔.02 መገናኛ ራዲዮ
✔.02 ኤፍ-1 ቦንብ
✔.12 ካዝና እና
✔. 07 የደረት ትጥቅ
360 የክላሽ ተተኳሽ ጥይቶችና ሌሎች ልዩ ልዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶች መማረክ ተችሏል።
የተስፋ መቁረጥ እርምጃ
በጀግናው ናደው ክፍለጦር ክንድ የደረሰበትን ከባድ ኪሳራ መቋቋም ያልቻለው የአገዛዙ ኃይል፣ በተለመደው የሽንፈት ባህሪው ዙ-23 እና ሞርተር በመጠቀም በንፁሃን አርሶ አደሮች መኖሪያ ቤቶችና ንብረቶች ላይ የበቀል ጥቃት በመሰንዘር ላይ ይገኛል። ኮሩ ከግንባር ያደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አሁን የተጀመረው ስልታዊ ማጥቃት ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ጠላትን በእያንዳንዱ ምሽግ የመቅበሩ ስራ ይቀጥላል ሲል ገልጿል ።ሌሎች ተያያዢ ዝርዝር መረጃዎችን በሚደርሰን መረጃ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፤ የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር የአፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ወታደራዊ ግምገማ አካሔደ!!
ቀን 03/11/2018 ዓ.ም
የታጠቀ ሕዝባዊ ኃይሎች የትጥቅ ትግል ጉዟቸውን ስኬታማ ለማድረግ ካላቸው ቁልፍ ስትራቴጂዎች አንዱ የውስጥ ጥንካሬን መፈተሽ፣ ድክመቶችን ማረም እና ቀጣይ ወታደራዊ ግዳጆችን በንቃት ማቀድ ነው። ይህንን መርህ መሠረት በማድረግ፣ በዕለቱ 03/11/2018 ዓ.ም በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚገኘው የአፄ ዘረያዕቆብ ፩ኛ ኮር፣ አፄ ይኩኖ አምላክ ክፍለ ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ ግምገማ አካሂዷል።
በትጥቅ ትግል ስነ-ልቦና ውስጥ የአዛዦችና የሰራዊቱ መግባባት ለውጊያ ዝግጁነት ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በዚህ መድረክ ላይ የኮሩ ወታደራዊ ዋና አዛዥ፣ የክፍለ ጦሩ ዋና መሪ ፣ የክ/ሩ ወታደራዊ አዛዡ፣ የሻለቃ አመራሮች እና ሻምበል መሪዎች ድረስ ያሉ ሁሉም የጦር መኮንኖች በሙሉ ተገኝተዋል። ይህ አይነቱ የተዋረድ መሪዎች ጥምረት በትግሉ መስመር ውስጥ ያለውን የዕዝ ሰንሰለት ለማጠናከር እና መመሪያዎችን እስከ ታችኛው የሰራዊት አባል ድረስ በግልፅ ለማውረድ ትልቅ አቅም ይፈጥራል።
መድረኩ በኮሩ ወታደራዊ ዋና አዛዥ መቶ አለቃ ተፈሪ የተመራ ሲሆን በመድረኩ እንደገለፀው፣ የተካሄደው ጥልቅ ወታደራዊ ግምገማ እጅግ አመርቂና ስኬታማ ነበር።ለቀጣይም የተሻለ ቁመና እንድኖረን እና ወትሮም ለድርጅታዊ ተልዕኮ የሚያነሳሳ ግምገማ ነው ። በትጥቅ ትግል ሂደት ውስጥ የሚገጥሙ ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎችን በወታደራዊ ሳይንስ መነጽር የገመገመው ይህ መድረክ፣ ሠራዊቱ ለቀጣይ ተልዕኮዎችና ግዳጆች በአዲስ መንፈስና በላቀ ዝግጁነት እንዲነሳሳ አድርጓል ብሏል።
ይህ ግምገማ ክፍለ ጦሩ በስትራቴጂካዊና በታክቲክ ረገድ ያለውን ቁመና ያጠናከረበት ሲሆን፣ መላው የክ/ጦር አመራሮችም ለቀጣዩ የትግል ምዕራፍና ለሚሰጡ ማናቸውም ወታደራዊ ግዳጆች ሙሉ ዝግጁ መሆናቸውን በጽናት አንፀባርቀዋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
📌 በትግላችን ውስጥ ካሉ መልካም ጅምሮች ወደ ላቀ ተቋማዊ ስኬት!
[ ሞገሴ ሽፈራው ]
የትግላችን ጉዞ እስካሁን ባሳያቸው ተስፋ ሰጪ ድሎች፣ በጀግኖች ፋኖዎቻችን ተጋድሎ እና በሕዝባችን ጽናት እዚህ ደርሷል። ይሁን እንጂ የጀመርነውን ትግል በትንሽ መሥዋዕትነት ወደ አስተማማኝ ድል ለማድረስ፣ አሁን ካለንበት የወታደራዊና የፖለቲካ ምዕራፍ ጋር የሚመጥን ተቋማዊ አደረጃጀት፣ ደንብና ግልጽ ፍኖተ-ካርታ ማበጀት ይኖርብናል።
ይህ በትግሉ ውስጥ ያለን ሁላችንም (አመራሮች፣ ታጋዮች፣ ሕዝብና ዲያስፖራ) ልናስብባቸውና ልናሳድጋቸው የሚገቡ 5 ዋና ዋና ስትራቴጂካዊ ነጥቦች ናቸው፡-
1. ስልታዊ ድሎችን ወደ ተቋማዊ የበላይነት መቀየር (Institutional Discipline)
በየአካባቢው ጠላትን በመማረክና በመደምሰስ የምናገኛቸው ወታደራዊ ድሎች በጣም የሚያበረቱ ናቸው።
እነዚህን ድሎች ይበልጥ ዘላቂ ለማድረግ፣ ከመንደርና ከአካባቢያዊ ስሜት በላቀ መንገድ አንድ ወጥ የዕዝ ሰንሰለት እና ጥብቅ ወታደራዊ ዲሲፕሊን መፍጠር አለብን።
በታሪክ ስኬታማ የሆኑ የሕዝብ ትግሎች (ለምሳሌ የቪየትናም ነፃ አውጪዎች) ውጤታማ የሆኑት ገና በጫካ ሳሉ ጥብቅ "የአመራርና የወታደር የሥነ-ምግባር ደንብ" አውጥተው፣ ድላቸውን በተቋም መምራት ሲችሉ ብቻ ነው።
2. ግልጽ የፖለቲካ ፍኖተ-ካርታ እና የጊዜ ገደብ (Strategic Roadmap)
በታማኝነትና በጀግንነት እየተዋጋን ነው።
"ከዚህ ምዕራፍ በኋላ ምን እናደርጋለን? ከማንኛቸውም ኃይሎች ጋርስ በምን መርህ ላይ የተመሠረተ ጥምረት እንፈጥራለን?" የሚለውን የሚመልስ ግልጽ ፍኖተ-ካርታ በሰነድ መኖር አለበት። ትግሉን በደረጃዎች ከፋፍሎ፣ ተለዋዋጭ ግን ግልጽ የጊዜ ሰሌዳ ማስቀመጥ የአመራሩንና የሕዝቡን ራዕይ አንድ ያደርገዋል።
3. የሕዝባችንን ማኅበራዊና አስተዳደራዊ መሠረት ማጠናከር (Civil Administration)
ሕዝባችን ደጋፊና ስንቅ አቅራቢ ሆኖ በትግሉ ጎን ቆሟል።
ትግሉ ይበልጥ ሥር እንዲሰድድ፣ ፋኖ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ሁሉ ሲቪል መስተዳድሮችን በመፍጠር፣ ፍትሕና ሰላምን ማስፈን መቻል አለበት። ሕዝቡ በነፃነት አካባቢውን ማስተዳደር ሲጀምር በትግሉ ላይ ያለው ባለቤትነት ይበልጥ ይጨምራል።
4. የዲያስፖራውን ድጋፍ በተደራጀ አቅም መምራት (Institutionalizing Diaspora Support)
በውጭ ያለው ወገናችን በትግሉ መጀመሪያ ጀምሮ ትልቅ የሞራልና የፋይናንስ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ድጋፍ በግለሰቦች ግንኙነት ወይም በጊዜያዊ ስሜት ላይ ብቻ እንዳይመሠረት፣ በአንድ ማዕከላዊና ግልጽነት ባለው አሠራር እንዲመራ ማድረግ ያስፈልጋል። ይህ ሲሆን የሀብት ብክነት ይቆማል፣ የረጅም ጊዜ አቅምም ይገነባል።
5. የሚዲያ፣ የአክቲቪስትና የጋዜጠኞች አዲስ ስልታዊ ሚና (Strategic Media & Narratives)
ሚዲያዎቻችንና አክቲቪስቶቻችን የሕዝቡን ድምፅ በማሰማት ረገድ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል።
ከአካባቢያዊ ዜናዎች ማጋነን ወይም አንዳንዴ በውስጥ ጉዳዮች ላይ ከሚፈጠሩ አለመግባባቶች ወጥተን፣ ትኩረታችንን በትግሉ ዋና ስትራቴጂ ላይ ማድረግ አለብን።
የሚዲያ ሥራ የስነ-ልቦና ጦርነት አካል በመሆኑ፣ ወገንን በሚያጠናክር፣ ጠላትን በሚያዳክም እና የትግሉን ዲሲፕሊን በሚጠብቅ ስልጡን መንገድ መመራት አለበት።
እስካሁን የመጣንበት መንገድ የጀግንነት ነው፤ ወደፊት የምንጓዝበት መንገድ ደግሞ የስትራቴጂ፣ የደንብና የተቋም መሆን አለበት። ሁላችንም በየተሰማራንበት መስክ ይሄንን ተቋማዊነት ለመገንባት በጋራ እንረባረብ።
ድል ለሕዝባችን!
የግብፅ ነገር: –
===========
ኤርትራ
======
#በ1961 የኤርትራ የነፃነት ጦርነት እንደተጀመረ ይነገራል ። ኢድሪስ ሙሐመድ አዳም እና ሌሎች የኤርትራ ምሁራን ELF ን በግብፅ ካይሮ እንደ ዋና የፓን አረብ ንቅናቄ አድርገው እንደመሰረቱም ታሪክ ያትታል። ነገር ግን የመጀመሪያው የትጥቅ ትግል የተጀመረው በሃሚድ ኢድሪስ አዋቴ ነበር። በ1960ዎቹ ዓመታት ELF ከ ግብፅ ፣ ከሱዳንና ከሌሎች የአረብ ሀገራቶች ድጋፍ ማግኘት ችለው እንደነበር ታሪክ ያትታል። የመጀመሪያው መካከለኛ ሞገድ የራዲዮ ስርጭትም በካይሮ አቋቁመው እንደነበር ይታወቃል።
ሕወሀት/ወያኔ
=========
#በትጥቅ ትግላቸው የመጀመሪያዎቹ ዓመታት በተለይ ከ1975-1978 ባሉት አመተታ ህወሃት የሱዳን ምስራቃዊ ግዛቶች:–
#ታጋዮች ከደርግ ጫና ሲደርስባቸው ድንበሩን በማቋረጥ ራሳቸውን ለማትረፍ ያመልጡ ነበር።
#በምስራቅ ሱዳን የሚገኙ የስደተኞች ካምፖች የተዋጊ ቅጥር እና የሎጂስቲክስ የአውታር መረቦች ሆነው ያገለግሉ ነበር።
#የተጎዱ ተዋጊዎች የህክምና፣የማገገሚያና የማረፊያ ቤዝ ሆነው ያገለግሉ ነበር።
#የመሳሪያ፣ትጥቅና ሌሎች አቅርቦቶች በሱዳን ምስራቃዊ ግዛቶች በኩል ወደ ትግራይ ክፍለ ሀገር ይዘዋወሩ ነበር።
ኦነግ
===
#በ1967 የሜጫ ቱለማ መስራች የነበሩት ታደሰ ብሩ ሲታሰሩ የማህበሩ አባላት ከነበሩት አንዱ የሆነው ሁሴን ሶራ ወደ ሶማሊያ ሸሽ። ሁሴን ሶራና ሌሎች የኦሮሞ ስደተኞች ሁሴን ሶራ የማህበሩ ዋና ፀሐፊ ሆነው የተሰየሙበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር የሚባል የአማፂ ቡድን በሶማሊያ ማቋቋማቸው ታሪክ ያስታውሰዋል። ይሄው ድርጅት ብዙም ሳይቆይ ወደ የመን ተዛውሮ የኦሮሞ ዲያስፖራ አባላትን ከየመን ማሰልጠን ጀመሩ።
#ENLF ወደ አገሪቱ ለመግባት ያደረገው የመጀመሪያ ሙከራ በጃራራ አባ ጋዳ መሪነትዘ ነበር።ነገር ግን የሶማሊያ የጸጥታ ኃይሎች ታጣቂዎቹን በሰሜናዊ ሶማሊያ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ሲሞክሩ ተይዘው በመታሰራቸው ሳይሳካ ቀረ ። ሁለተኛው ሙከራ ስኬታማ የነበረው በኮማንደር ሁሴን ኢብራሂም (በተለምዶ ኢልሞ ቂልጡ) ተብሎ የሚታወቀው ግለሰብ የመራው ቡድን ሲሆን ከሶማሊያ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት በጨርጨር ተራሮች ሰፈረ። በዚህ ጊዜ ቡድኑ ከ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር ወደ የ "ኦሮሞ ነፃነት ግንባር" በሚል ስም ለመስራት ወሰኑ።
Ifat
===
THE OROMO OF ETHIOPIA, 1500-1850 : WITH SPECIAL EMPHASIS ON THE GIBE REGION
Mohammed Hassen
Thesis submitted for' the degree of Ph.D. of the University of London, School of Oriental and African Studies, 1983.
Introduction ~ ገፅ 10 ላይ እንዲህ ይላሉ።
"The second source of our information for the first major Muslim Christian struggle comes from the pen of the great Egyptian scholar Al- Umari. He reported on the basis, of information he gathered from Shaikh Abdallah of Zila, the ambassador of Ifat, who went to Egypt on behalf of the Muslims to seek support from Egypt. Al- Umari, who produced this story around 1345, described the seven Muslim states, their cooperation and competition, strength and weakness, the richess and poverty with astonishing clarity. The story of al- Umari, although not as rich as that of the anonymous Christian chronicler, is quite detailed and reliable."
የእኔ ጥያቄ?
========
#የአማራ ህዝብ ለማንነቱ የፖለቲካ ትግል ለዚያውም በቀየው ሲጀምር በራሳችሁ ልክ ለክታችሁ የግብፅ ተላላኪ ለማለት ድፍረቱን ከየት አገኛችሁት የሚል ነው?
#የአማራ ገዢ መደብ ገልምጦኝ፣ፈልጦኝ፣ቆርጦኝ ሲል የኖረ ማህበረሰብ ~ political revolution ~ አካሂዶ ምን አይነት መንግስት ይመሰርቱ ይሆን ተብሎ ሲጠበቅ:–
#ወያኔ ~ ትግሬ መር ትግሬ የሚመስል የትግሬ ገዢ መደብ መንግስት
#ብልፅግና ~ ኦሮሞ መር ኦሮሞ የሚመስል የኦሮሞ ገዢ መደብ መንግስት
መስርተው ቁጭ አሉ!
ጥያቄው: –
#የአማራ ገዢ መድብ ባላችሁበት ወቅት ያነሳችሁትን ጥያቄ ረስታችሁት ነው ወይ?
#ከዚያ ደግሞ ገራሚው ነገር አማራ፣አማራ ብለው ትግሬ መርና ኦሮሞ መር መንግስት መስርተው እያየንና ትናንት ኖረነው፣ዛሬ እየኖርነው እያዩ የአማራ ትውልድ ለፖለቲካ ትግል አይነሳም ብለው መጠበቃቸው ነው!
√እንዴት ሰነበታችሁ!?
እንኳን ለዚህ ቀን አበቃችሁ‼️እንኳን ደስ አላችሁ!
ከፊታችሁ በመቆሜ ታላቅ ክብር ይሰማኛል‼️።
ታሪክ የራሱ ነፍስና የራሱ ረቂቅ የስሌት ቀመር አለው። ከነመፈጠራቸው የማይተዋወቁ ሁለት ሰዎችን በራሱ ልብ መርምሮ፥ በራሱ ቀመር አንጥሮ ከየጥጉ ጎትቶ አምጥቶ ለአንድ ወርቃማ አላማ ሲል ያገናኛቸዋል። እናም ለብዙሃኑ እውነትና ነፃነት እንደጧፍ ያበሩ ዘንድ በፍቅር ያሰልፋቸዋል። ይበራሉ።በድቅድቅ ጨለማ መሃል የተስፋ ብርሃን የነፃነት ወጋገን ይሆናሉ።ይህ አስበው የማይዘልቁት የታሪክ ጥልቅ ምስጢር ነው።ታሪክ እኔንና እናተንም በዚህ ዘመን በዚሁ ስሌት ለአንድ ወርቃማ የትውልድ ፕሮጀክት አገናኝቶናል።ዛሬ እየታገልን ነው፥ነገ እናሸንፋለን።የአማራን ቀን እናመጣለን።
በድጋሜ እንኳን ደስ ያላችሁ‼️
ህልውናችን እስካልተረጋገጠ ድረስ የዛሬ አምሳ አመት በዚህ ቦታ ላይ ሌላ አማራ ቆሞ፥ ሁልጊዜም ስለመሰልጠንና ስለመዘጋጀት አስፈላጊነት ሊናገር ይችላል።መደራጀታችን፥ መሰልጠናችን፥ መታጠቃችንና ለህልውናችን መታገላችን የሚቆመው ህልውናችን የተረጋገጠ እለት ብቻ ነው።ይህ የዛሬው የእናንተ ምርቃት የአማራ ህዝብ ትግልና የሃገሪቱ እጣፋንታ ተገፍቶ አንድ ጫፍ ላይ የቆመበት ምእራፍ ላይ የሚደረግ ነው። ስራ የሚጠይቅ የድል ታዛ ላይ የቆመ እጅግ አጓጊ ምእራፍ ነው ።
ውድ ጓዶቼ በዚህ አጋጣሚ አደራ ልላችሁ የምፈልገው ብዙ ጉዳይ አለ፦
ዛሬ ለመመረቅ ላለፉት በርካታ ወራት ብዙ ወጣችኋል፥ብዙ ወርዳችኋል፥ ብዙ ላብ አፍሳችኋል። በአካልና በመንፈስ ጠንክራችኋል፥ የትግላችን ሀሁ እና ግብ ተገንዝባችኋል።በዚህ ሙሉ ቁመናችሁ መከላከያ የሚባል የአብይ አህመድ ታጣቂ ጋር ፊት ለፊት ትገጥማላችሁ።
ትግል ግን ሌላም መልክ አለው። ከራስ ጋር የሚደረግ ትግልና አብሮ ሲኖር ከጓድ ጋር የሚደረግ ትግል እጅግ ከባድና ፈታኞቹ የትግል መልኮች እንደሆኑ ልትገነዘቡ ይገባል። ወደ አብይ አህመድ መተኮስና አብይን ማሸነፍ ቀላል ነው፥ ከባዱ ወደ ራስና ጓደኛ ድክመቶች ማነጣጠር ነው።
አብይ በታንክና በድሮን ያልቻለውን ጦርነት በገንዘብ፥ በሽማግሌና በወሬ ሊያሸንፍ እየሞከረ ነው።አንዳንዴ ከሽህ የአብይ ታንከኛ አንድ ወሬኛ ትግላችን ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላልና ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል።እንግሊዞች "ስራ ለፈቱ እጆች ሰይጣን ስራ ይፈጥርላቸዋል" ይላሉ።ብዙ ጊዜ የወሬና ሃሜት ምንጩ መቦዘን ስለሆነ እያንዳንዱን ደቂቃ ስለትግላችን በመድከምና በማሰብ እናሳልፍ።
ታጋይ ወንድሞቼ ❗ ይህ በእናንተ ላብ፥በወንሞቻችሁ ደም እና በህዝባችን ሲቃ የተገዛ ትግል ነው። የአቢዮቱ ዘበኞች እናንተ ናችሁ።ስለዚህ ከፋፋይ፥ ለግልና ለቡድን ፍላጎት ብቻ የሚሰሩ መንፈሰ ደካሞች ቢገጥሟችሁ ናቋቸው፥ ታገሏቸው።ይህ ትግል የህልውና አደጋ ለገጠመው የአማራ ህዝብ የህልውና ጉዳይ ነው። የሚሳሱለት አይኖች፥ ሌት ተቀን የሚጠብቁት እጆች ይፈልጋል።እና አደራ!!
ክፋትን፥ ምቀኝነትን፥ ቅናትንና ተንኮልን ተፀየፉ። ማንም የግለሰብም ይሁን የቡድን ጠላት አማራ ላይ ይነሳ መግጠምና መጣል እንችላለን። እነዚህ የመፈስ ደዌዎች ከተጠናዎቱን ግን ከጠላት ቀድመው እኛኑ ይጥሉናል።ፖለቲካችን ችላ ያለው ፥ያልተሄደበት መንገድ ቅንነት ነው።አለም ደጋግሞ የሚወድቀውም በዚህ ምክንያት ነው። በተንኮልና በክፋት በቦካ ፖለቲካ አለም የራሱን እጅ እየበላ ለጊዜው ይረካ ይሆናል እንጅ የትም አይደርስም። ይህ የመሳሪያም የቅንነትም አቢዮት ነውና ክፋትንና ተንኮልን ራቁ።የወንድምን ስኬት ውደዱ።ለሌሎች መኖርን ልመዱ።ራስ ወዳድ እንዳትሆኑ። ህዝባችን እያለቀ ራስ ወዳድ እንደመሆን ትልቅ ወንጀል የለም።ከፍ ባላችሁ ቁጥር የበለጠ ትሁት ሁኑ።
ይህን የምላችሁ የአለም ፖለቲካ እንዴት እንደሚሰራና እንደሚሰራ የማላውቅ ቂል ሆኜ አይደለም፥
ይልቁንም በመደበኛ ፖለቲካው ውስጥ ያለው መደበኛ የቅጥፈት መንገድ ውጤቱ ውድቀት እንደሆነ የአለም ተሞክሮ በተለይ ደግሞ የራሳችን ልምድ ስለሚነግረኝ እንጅ።
ይህ ትግል የህዝብ ትግል ነው። ይህ ትግል ለአማራ ህዝብ የሚደረግ ትግል ነው። መነሻችንም መድረሻችንም ህዝባችን ነው። ምድራዊዩ እግዜራችን ህዝብ ነው። ይህን እግዜር አይኑን መጠንቆል ያስቀስፋል። በስህተት እንኳን ህዝብን የሚያስቀይም ነገር አንዳትሰሩ። ክልክል ነው። ህዝብ እንኳን መብቱን ሰብል የለበሰ የእርሻ መሬቱን ስትረግጥበት፥ የቤት አጥሩን ስትደገፍበት አይወድም። ህዝብ "ፈጣሪያችን" ነውና እንቅስቃሲያችን ያያል፥ እስትንፋሳችን ይለካል።ጥንቃቄ እናድርግ።
የአማራ ህዝብ የራሱ የሆነ ንፁህ ተቋም እንዲኖረው ብዙ ቀደምቶች ብዙ ደክመዋል።ታስረዋል፥ አካላቸውም ቅስማቸውም ተሰብሯል፥ህይወታቸውንም ሰጠዋል። በቀጠለ ጥረትና ብዙ ድካም በዚህ በኛ ዘመን ተሳክቷል። የአማራ ህዝብ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄን ፈጥሯል።ይህ ተቋም መድህናችን ሆኖ ወደምንፈልገው ግብ ያደርሰን ዘንድ በየዘርፉ የተሳሉ ፖሊሲዎች አሉት።የተቋማችን የመጀሪያውና ቋሚው ፖሊሲያችን ራስን መቻል ነው። ሁሉን አቀፍ ራስ በቅነትን በየቀኑ ማሳደግ ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ ድርጅታዊ ውስጣዊ አንድነታችን እናጠናክራለን። ራሱን ያልቻለ አንገት የሚያቅፈው የለውም።ስለዚህ የእዞች ውስጣዊ አንድነት፥ የድርጅታችን አፋብን ጠንካራ ውስጣዊ አንድነት እጅግ አስፈላጊ ነው።የህዝባችን አንድነት የመተንፈስ ያክል ፍፁም አስፈላጊ ነው።የተበተነ ህዝብ ነጥሎ የሚበላውን ጠላት ከየአቅጣጫው ይጋብዛልና።
ሁለተኛውና ተያያዥ ፖሊሲያችን ከራስ መቻል ላይ የመነጨ ከሌሎች ጋር የሚደረግ የተመረጠ በጎ ትብብር ነው። የተሰላና የተጠና ትብብር ሁልጊዜ አስፈላጊ ነው። ጥቅምህን በሚስጢር ኪስህ ይዘህ ፥ የሌላን ወገን ጥቅም ሳትነካ፥ የራስህን ሳታስነካ መተባበር ሁሌም ልክ ነው። ስለዚህ በአጭርም በረጅምም እንተባበራለን።የቀጠናው ሃይሎችም ጋር ቀጠናዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከጥቅማችን አኳያ እናብራለን። ፋኖ ልብ አለውም አላለውም የግዙፉና የውስብስቡ የምስራቅ አፍሪካ መልክአፖለቲካ አካል ሆኗል። ወይ ዋኝቶ ይወጣል ያለበለዚያ ግብግቡ በሚያስነሳው ማእበል ውስጥ ይሰጥማል።ግዙፉ ቁመናችን በስሌትና በጥበብ ታግዞ፥ የምላጭ ጠርዝ ላይ የመቆም ያክል ተጠንቅቆ ሌሎችን ሳይደፍቅ አሸናፊ ይሆናል።
ከዚህ አኳያ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚስተዋለው ግርግር አማራን ብቻውን ለማቆም ነው።‼️
በእርግጥ ማንም ሃይል መተማመኛው የራሱ አቅም ነው።የማይሸሽ፥ የማይለወጥና የማይነቅዝ የራስ አስተማማኝ አቅም ነው።ይህም ሆኖ አማራ በአለም ፊት ቆሞ ብቻውን ገለባብጦ ተራራውን ሜዳ ፥ሜዳውን ተራራ እንዳላደረገ ሁሉ የአማራ ትግል "ተነጥሎ" የቆመ እለት ይከስማል የተባለ ይመስል ይህ ሁሉ ግርግር ፋኖን ብቻውን ለማቆም ነው።
ከሶስት አመታት በፊት ሁሉም የጨዋታው ተሰላፊ የየራሱን ስሌት ይዞ በፕሪቶሪያ መድረክ ቢጫዎትም "በስምምነቱ" ውስጥ የነበረው የብዙዎች ተሰላፊዎች "ድብቅ" የጋራ ግብ ግን መቀጣጠል ጀምሮ የነበረውን የአማራ የአቢዮት እሳት በጋራ የማጥፋት እቅድ ነበር ብዬ አምናለሁ ። በዚህ " አደገኛውን ሰደድ የማጥፋት ተልእኮ" ውስጥ ህወሃትና ብልፅግና በደስታ አብረው እንደሚሰለፉ የፕሮቶሪያ ስምምነት "ሽማግሌዎቹም" እርግጠኞች ነበሩ ማለት ይቻላል። ምናልባት የትግራይ ሃይሎች ታሪካዊ ውሳኔ ወስነው ራሳቸውን ግሉል አድርገው ማቆማቸው እስኪታወቅ ድረስ በቀላሉ አማራን ጨፍልቀው ወደ ኤርትራ መሻገርና የየራሳቸውን ግብ ማሳካት እንደሚችሉ እርግጠኞች ነበሩ።ባልጠበቁት ሁኔታ
የአፋብን/ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክፍለ ጦር በሺዎች የሚሆኑ አዲስ የፋኖ አባላትን በመተከል ቀጠና በድምቀት አስመረቀ!
ሐምሌ 2/11/2018 ዓ.ም
በአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ውስጥ ትልቅ ሚና እየተጫወተ የሚገኘው የአፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 66ኛ ክፍለ ጦር በሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ የፋኖ አባላትን "መተከል ኮርስ" ብሎ በመሰየም በመተከል ቀጠና በዛሬው ዕለት በደማቅ ወታደራዊ ስነስርዓት አስመርቋል።
በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ የአፋብን ሊቀ መንበር አርበኛ ዘመነ ካሴ፣ የቴዎድሮስ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በዕለቱ አርበኛ ዘመነ ካሴ ለአዲስ ተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ይህ የምርቃት ፕሮግራም የአፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ ያለውን የማደራጀትና የማሰልጠን አቅም ማሳያ ከመሆኑም ባለፈ፣ ለህልውና ትግሉ አዲስ ጉልበት ይሰጣል።
ድል ለአማራ ህዝብ!
ክፋት ለማንም፥ በጎነት ለሁሉም
አዲስ ትውልድ፥ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን|ቴዎድሮስ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሐምሌ 02/2018ዓ.ም
ህወሃት የራሱን ስትራቴጅካዊ ስሌት ይዞ አማራን አልወጋም፥ ኤርትራ ላይም አልዘምትም ሲል ቀመሩ ተዛባ። የአማራው የህልውና ትግልም በመካከል በፍጥነት ሌላ ደረጃ ላይ ደረሰ።ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ በአንድ እጁ እየተዋጋ በሌላኛው እጁ የራሱን ትግሉን የሚመራ ተቋም ፈጠረ።ይህ ሲሆን የጨዋታው መልክ ሙሉ በሙሉ ተቀየረ ማለት ነው።
አብይ ግን እድሎች ከተገኙ አሁንም እዛው ጨዋታ ውስጥ መሆኑን እና ተስፋ አለመቁረጡን የሚያሳየው በተለይ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ አማራውን ለመነጠል የሚያደርገው ሩጫ ነው። በዚህ መሃል አንዳንድ አውቀው የተኙ ወይንም በአሞሌ ጨው ራሳቸውን የሸጡ የኛን ወገኖች ሳይ "ሌላው ሁሉ ይቅር ይህ ሁሉ ሩጫና ግርግር አማራን ብቻውን አቁሞ ለማጥፋት በመመኜት የሚደረግ መሆኑን እንዴት ማወቅ ተሳናቸው ?" እላለሁ።ለዚህ እፍኝ እድሜስ ስንት አመት አሞሌ ይላሳል?
በእኔ እምነት፦
የፕሪቶሪያ አፈራራሚዎች ዋና ግብ ፀረ-አማራ ብለው ያሰቧቸውን ሃይሎች አስተባብሮ እየተነሳ ያለው አዲሱ የአማራ አቢዮት መንፈስ ላይ ማዝመት ነበር።ለጊዜው አልተሳካም።
እነዚህ ሃይሎች የአማራ ልዩ ሃይል እንዲፈርስ ለአብይ ቀጭን ትእዛዝ ሰጠዋል።ልዩ ሃይሉ ፈረሰ። ያም ሆኖ ያሰቡት ሳይሳካ እንዴውም የፈረሰው ልዩ ሃይል ለትግሉ ልዩ ግብአት ሆነ።
ትንሽ ገፋ እና ደፈር አድርጌ ከደመደምሁ... የፕሪቶሪያው ስምምነት በራሱ "የአማራ ትንሳኤ" ፍርሃትና ድንጋጤ ውጤት ነው።አማራው ባይነሳ ኖሮ የፕሪቶሪያ ስምምነትም አይፈጠርም ነበር።ለዚህ ነው አንዳንድ ወገኖች የአማራው የህልውና ትግል የዘመናት ፍጅትና መጎሳቆል ውጤት መሆኑን ረስተው በፕሪቶሪያው ስምምነት ምክንያት የተፈጠረ ኩርፊያ የወለደው ሊያስመስሉት ሲሞክሩ ሲታይ አስቂኝና አስተዛዛቢ የሚሆነው።ፕሪቶሪያ የአማራን ትግል አልወለደም፥ የአማራ መነሳት ፕሪቶሪያን ወለደ እንጅ።
ቆላም ነፈሰ ደጋ ጨዋታውን በደንብ ተጫውተናል። ።ስርአቱንም እንደተደገመበት ሰይጣን አፍዝዘን አስቀምጠነዋል። እጣፋንታውንም በምንወስደው ቀጣይ ሙሉ ለሙሉ ገፍቶ የመጣል እርምጃ ላይ እንዲወሰን አድርገነዋል።
የዚህ ትብብር ስኬትና ውድቀት ግን የሚቀጥሉት ብዙ መቶ አመታት የእርስበርስ እልቂት ወይም ሰላምና ልማት ማለት ነው።
በዚህ አጋጣሚ፦ ባለሃብት ነን የምትሉና ይህን ትግል ለማፍረስ በድለላ የተሰማራችሁ ወገኖች ተው።!---ከፀሃይ በታች የምትሰሩት እያንዳንዱ ስራ ይታወቃል።እንኳን ከህዝብ ከጎረቤት ተጣልቶ መኖር ይቸግራልና አስቡበት።አርፋችሁ ስራችሁን ስሩ።
በዚሁ የፖለቲካ ድለላ ውስጥ የተሰማራችሁ አንዳንድ የሃይማኖት አባት ነን የምትሉ የየቤተ እምነቱ ሰዎችም ከዚህ ድርጊታችሁ ተቆጠቡ።ሌላው ቢቀር ቤተ እምነታችሁን ለሚያፈርስ ሃይል አካፋ አቀባይ አትሁኑ።ለምድርም ለሰማይም የማይሆን ነገር አትስሩ። በ80 አመታችሁ የሰላሳ አመት ጆሮ ጠቢን አትፍሩ።በውድቀታችሁ የጣላችሁትን ዘመንና ህዝብ ልናቃና ስንደክም ደንቃራ አትሁኑ።ትንሽ እንኳን እፈሩ።
ለውዱ የአማራ ህዝብ!
የአለምን መከራ ተሸክመሃል፥ እንድታልቅ ፍጅት ታውጆብሃል።ከዘመናት ሞት-ቀመስ እንቅልፍ በኋላ ተነስተሃል። ጠላትህ አቁስለህ የምትተወው አውሬ አይደለምና ሳትቀብረው እንዳትቀመጥ።ጠላት አንድነትህን በወንዝ ለመክፈል፥ በጎጥ ለመተልተል፥እየሰራ በመሆኑ በደምህ የገነባኸውን ቤት የሙጥኝ በል። እንደወትሮው ሁሉ በተለይ ደግሞ ከቅርብ ግዜ ወዲህ አብይ የሃይማኖት ግጭት ለመፍጠር እየሰራ በመሆኑ መዋደድህ የበለጠ መጠንከር ይኖርበታል። በየቀኑ የሚከፈለውን ዋጋ ባውቅም በነፃ ነፃ አይወጣምና አይዞህ በርታ!
ለመላው የኢትዮጲያ ህዝብ‼️
ይህ እብድ ሰውዬና ቡድኑ በስልጣን ላይ እስካሉ ድረስ የማይጎሳቆል፥ የማይራብ፥ የማይታረዝና ህልውናው አደጋ ውስጥ የማይገባ ኢትዮጲያዊ አይኖርም። በኢትዮጲያ ምድር ላይ ቆሞ መራመድ እስከቻለ ድረስ መሬቱንም ህዝቡንም በግራም ሳይቀር እየለካ ከመሸጥና ከማጥፋት አይመለስም። ስለዚህ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ይነሳ።
ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ‼️
ዛሬ ከአብይ ጎን ቁሞ የሚገኝ ብሄራዊ ጥቅም ነገ ከቀጠናው የሚመነጭ ትልቅ ብሄራዊ ኪሳራን ያመጣባችኋልና ከእውነት፥ ከፍትህና ከነፃነት ሃይሎች ጎን ቁሙ። በተለይ አንዳድ ሃገራት አብይን መደገፍ አቁሙ።አብይ አማራን ሲፈጅ፥
የትግራይን፥ የኦሮሞን፥ የጋምቤላን፥ የሲዳማን፥ የጉምዝን፥ የቤኒሻንጉልን፥ የአፋርን፥ የሶማሊን፥ የጉራጌን በአጠቃላይ የሃገሪቱ ህዝብ ላይ እሳት ለኩሶ እያቃጠለ ቆሞ መመልከት ነገ አለም ቢጮህ የማይፈታው ቀጠናዊና አለም አቀፋዊ ምስቅልቅል ይፈጥራልና አስቡበት።ፍትህና ነፃነት ደንበር የላቸውም። እንደ ፀሃይ ለሁሉም መሆን አለባቸው።
ለሚሊሻ፥መደበኛና አድማ ብተና ፖሊስ አባላት።---በራሳችሁ ፀብ ውስጥ የጠላት ዱላም ገላጋይም መሆን ታሪክ የማይረሳው ክህደት ነው። ወደ ወገኖቻችሁ ኑ።ያለበለዚያ እጣ ፋንታችሁ አንደኛው ተራራ ስር ወይ አንዱ ጎዳና ላይ ደመ-ከልብ መሆን ነው።አሁንም ቢረፍድም አልመሸምና ወደ ወገኖቻችሁ ኑ።በኛ በኩል እንደ ወንድምና እንደ አባት እንቀበላችኋለን።
ድል ለአማራ ህዝብ!
ክፋት ለማንም፥ በጎነት ለሁሉም
አዲስ ትውልድ፥ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
በጣም አመሰግናለሁ!!
+1
ዲሽቃና ብሬኑ ተማረከ/ የጠላት ጦር ተሽመደመደ!
በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 55ኛ ክ/ጦር ዛሬ ሃምሌ 02/2018 ዓ/ም ከንጋት ጀምሮ በዳንግላ ወረዳ ጫራ ከተማ ላይ በወሰደው አስደናቂ የማጥቃት እርምጃ አገዛዙን ጥምር ጦር አንድ ሬጅመንት ሙሉ በሙሉ በመደምሰስ ከስምሪት ውጭ አድርጎታል።
በውጊያው ከ55ኛ ክ/ጦር 3ኛ እና 4ኛ ሻለቆች ከክፍለጦሯ ቃኝእና መሀንዲስ እና ከዳንግላ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት አሃዶች ጋር በመናበብ ታአምራዊ ውጊያ በማድረግ በጠላት ላይ ሰብአዊ ቁሳዊ እና ሞራላዊ ጉዳት አድርሰዋል ።
በዚህ አውደ ውጊያ
1 ዲሽቃ
1 የዲሽቃ ተቀያሪ አፈሙዝ
3 ብሬን
2 m14
1ፋል
52 ክላሽንኮፍ
6 አብራራው
13 sks
450 የዲሽቃ ጥይት
250 የብሬን ተተኳሽ
1300 የክላሽ ተተኳሽ
የሟ,ች እና የቁsለኛ ቁጥር በርካታ ስለሆነ ቆጠራ ላይ ነን
ማሳሰቢያ በፎቶው ላይ የሚታዩ መሳሪያዎች በአንድ ግንባር ብቻ የተማረኩ እንጅ ሙሉ የምርኮ መሳሪያ የሚያሳይ አደለም።
ምንጭ፦ በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል!
አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በየቦቅላ ከተማ ድል ተቀዳጅቷል!!
~~~
በዛሬው ዕለት ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር በ206 ኮር ቀጠና የቦቅላ ከተማ ከሌሎች ክፍለ ጦር ጋር ባካሄደው ውጊያ በርካታ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ መማረክ ችሏል።
ድርጅት በመጠበቅና ከሌሎች ክ/ጦሮች ጋር በመቀናጀት ሁሌም ድል በማድረግ የሚታወቀው 64ኛ ክ/ጦር በ206 ኮር በሚያስተዳድረው ቀጠና ጎዛም ወረዳ የቦቅላ ከተማ ሰፍሮ በሚገኘው የአገዛዙ የጠላት ኃይል ላይ ከ24ኛ እና 34ኛ ክ/ጦር ጋር በመቀናጀት ባአካሄደው ውጊያ #አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በተሰጠው የውጊያ ቀጠና ብቻ በርካታ የጠላት ሀይል በመደምሰስና በማቁሰል የአገዛዙ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን መማረክ ችሏል። ክ/ጦሩ በአካሄደው ውጊያ ያገኘው ድል:-
➤2 ጥቁር ክላሽ
➤2 ኮሪያ ክላሽ
➤አንድ 10 ቁጥር ክላሽ
➤ጠ/ድምር= 5 ክላሽ ማርኳል። በአውደ ውጊያ የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ ልጆች ዛሬም እንደ ልማዳቸው ፉከራ በተቀላቀለበት ወኔቸው የጠላት ኃይልን ሲያደባዩት ውለዋል። በእጃቸው ላይ ቁስል አስርው ውጊያው የመሩት ወታደራዊ አመራር እና በአንድ ክላሽ አራት ክላሽ የማርኩ የክፍለ ጦሩ ምሽግ ሰባሪ ጀግኖችን ጀብድ ይዘን እንመለሳለን።
ለአናሸንፍ የጀመርነው ትግል የለም! አማራነት ወይም ሞት!!
ድል ለአማራ ሕዝብ🔥🔥🔥 ድል ለአማራ ፋኖ💪💪💪
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
የድል መረጃ
ዳንግላ አቅራቢያ ጫራ አካባቢ የሚገኘውን የጠላት ሃይል በፋኖ ተመቶ ሙትና ቁስለኛ ሲሆን በርካቶች ምርኮኛ መሆናቸውን ነው ለማወቅ የተቻለው።
ውጊያው ከንጋቱ 11:3ዐ ሰዓት የጀመረ ሲሆን አሁንም እንደቀጠለ መሆኑንነው የታወቀው።ጠላት ተጨማሪ ሃይል ዳንግላ ከሚገኘው መኮድ ለማንቀሳቀስ የሞከረ ቢሆንም ጫራ የሚገኘውን ሙትና ቁስለኛ ማትረፍ አልቻለም።2/11/2018 ዓ/ም
ብልሆች ህይወታቸውን እያተረፉ ነው በዛሬው እለት የፓራ ኮማንዶ አባላቱ እና ዲሽቃ ምድብተኛው ፋኖን ተቀላቅለዋል።
◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍◍
.......ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም
ከፈለገ ብርሀን ከደብረወርቅ ከሞጣ ፣ከግንደወይን እንዲሁም ከድጎፅዮን በመውጣት ከዚህ በሗላ ለስርአቱ መጠቀሚያ መሆን በቃን በማለት 201ኛ ኮር 74ኛ እና 54ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል።
1.ገብሬ ሆነ........ፓሊስ ኮሪያ
2.ፈንታሁን ስማቸው.... ዲሽቃ ምድብተኛ
3.ክንድ ግዛ ...........ፓራ ኮማንዶ
4.እባብየ ድረስ..........ሚሊሻ
5.ወለላው ጌጤ.....ሚሊሻ
6.ገበያው አስቻለ ....ፓራኮማንዶ ጓድመሪ
7.አመት የቆየ..........ፓራኮማንዶ
8.ድንበሩ አበበ.........ሚሊሻ
በክፍለ ጦር አመራሮች አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን ሁላቹህም ይኸን የተሻለ አጋጣሚ በመጠቀም ወደ ትክክለኛው ማንነታቹህ እንድትመለሱ ጥሪያችን እናስተላልፋለን።
< ኑ መተኪያ የሌለው ህይወታቹህን አትገብሩ ራሳቹህን አትርፉ>
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
