ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር ግጥሞች
ይህ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትምህርትን የምንማማርበት Channel ነው ! ወደ ቻናላችን በመቀላቀል 👇 ➲ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መፅሐፍትን በPDF ➲ስንክሳር ትምህርቶች ➲ መዝሙራትን ➲ ግጥሞች ➲ ፊልሞችን ➲ ጥያቄዎችን በሐይማኖት ብትኖሩ እራሳችሁን መርምሩ" ( 2ኛቆሮ -13 ፥ 5)👇 Group ገጽ👇👇 https://t.me/Orthodoxs_Tewahdo_menfeswi_group
إظهار المزيد9 118
المشتركون
-424 ساعات
+2557 أيام
+44630 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
Repost from መዝሙር ግጥሞች ቤት
Photo unavailableShow in Telegram
የዘማሪ ዲያቆን ይገረም ፀጋዬ የአቀባበል እና ሽኝት መርኃ ግብር
👉አስክሬኑ ካለበት ከደቡብ አፍሪካ አርብ ከቀኑ 8:35 ይነሳል።
👉አርብ ማታ ከምሽቱ 3:00 ሰአት ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ይደርሳል ።
👉አስክሬኑ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፣በአድባራት እና በገዳማት አስተዳዳሪዎች፣በመምህራን በዘማሪያን እና በወዳጆቹ ታጅቦ ቦሌ መድኃኔዓለም ካቴድራል ይገባል።
👉ከለሊቱ 10:00 እስከ ከጠዋቱ 1:00 ሰአት በሊቃነ ጳጳሳት እየተመራ ጸሎት እና ስርአተ ቅዳሴ ይደረጋል።
👉ቅዳሜ ከጠዋቱ ከ1:00 ሰአት እስከ 2:30 የሽኝት መርኃ ግብር ይሆናል።
👉ከከጠዋቱ 3:00 ሰአት ጀምሮ ወደ ትውልድ ሀገሩ ወደ ሆሳዕና በአገልጋይ አባቶች፣በመምህራን፣ዘማሪያን እና በወዳጅ ቤተሰቦቹ ታጅቦ ይሄዳል።
👉እሁድ ከቅዳሴ ቡኃላ ስርአተ ቀብሩ በሆሳዕና ደብረ ምህረት ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተክርስቲያን ስርአተ ቀብሩ ይፈፀማል።
ከአስተባባሪ ኮሚቴ
በስመዓብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
"በቀራንዮ የተከፈለውን ዋጋ ባሰብኩ ግዜ አንደበቴ ዝም ይል ዘንድ ልተወው አልችልም መንፈሴም እመሰክር ዘንድ ያነሳሳኛል።"
ተናገር አለኝ መስክር
ተናገር አለኝ ዘምር
ለቀራንዮ ውለታ
አርምሞ የለም ዝምታ
ለመድኃኔዓለም ውለታ
አርምሞ የለም ዝምታ
ሰው አድርጎኝ ሞቶ በደሙ
ኑሮዬን ባርኮት ሕመሙ
ሰላም አውጥቶ ካስገባ
ልያዝ ለክብሩ ዘንባባ
ሆሳዕና ልበል መድኃኒት
ከፍ በልልኝ የኔ አባት
ተጠምተኸ እኔ ረካሁ
ስራህ ግሩም ነው ደነቀኝ
አዝ_
እጆቹን እዩት በእምነት
ቆሰለ ሊሰጠኝ ሕይወት
በዚያ ታትሞ ውበቴ
እየሱስ ለኔ ብርታቴ
ከማንም በላይ ከምንም
ለኔ ልዩ ነው ዘላለም
ሕይወቴን ለእርሱ አስማርኬ
እኔስ በረታሁ በአምላኬ
አዝ_
የእሾህ አክሊሉ በራሱ
ለእኔ ቤዛ ነው ሞገሱ
ሞቴን ገድሎታል አባቴ
ሰላሜ እርሱ ነው እረፍቴ
ሰው የመሆኔ ምስጢሩ
የማይለወጥ ነው ፍቅሩ
የገባኝ እውነት በምድር ላይ
ፍቅር ነው ጌታ ኤልሻዳይ
አዝ_
ክብሩን ለማወጅ ተነሳሁ
ሲያድነኝ ከሞት እያየሁ
ገመና ሸፋኝ ኪዳኔ
ተራበ ውዴ መድኃኔ
ይሄ ነው የቆመኝ በፊቱ
ወሰን የሌለው ምሕረቱ
ለዚህ ደግነት ውለታ
ምን ይከፈላል ለጌታ
👉ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
https://t.me/qidus_Michael_abate12
✞ የከበረ ስሙን ✞
የከበረ ሥሙን እንድታስከብር
ጠላት ዲያብሎስን እንድታሳፍር
አንተን የመረጠ እግዚአብሔር ይክበር
የከሃዲን ትዕቢት ምንም ሳትፈራ
የእግዚአብሔር ሰማዕት ተቀበልክ መከራ
በመከራው ብዛት ደከመኝ ሳትል
ጸንተህ ተጋደልክ ጊዮርጊስ ኃያል
አዝ= = = = =
በፈጣሪ ሥም ድካም ያላገኘህ
በብርቱ ተጋደልክ ጽናትን አሳየህ
ገድልህን ልናገር ጊዮርጊስ አባቴ
ጽናትህ አስቀናኝ እኔም በሃይማኖቴ
አዝ= = = = =
የሄድክበት መንገድ ቢሆንም ጠባብ
ልቤን ማሳረፊያ ሆኖኛል ወደብ
መንፈሳዊ ጀግና ጠላት ያልገዛህ
ሰይጣንን ተዋጋህ ጸናህ በእምነትህ
አዝ= = = = =
ፈጥኖ የሚያልፈው የዚህ ዓለም ክብር
ሊለየኝ አይችልም ከጌታዬ ፍቅር
ብለህ የዘመትከው የጽድቅ ወታደር
የኢየሱስ ክርስቶስ ታማኝ ምስክር
አዝ= = = = =
በኃይሉ እግዚአብሔር ጸንቼ አምናለሁ
ሁሉን ለፈጠረ አምላክ እሰግዳለሁ
የሥቃይ መሳሪያው አያስፈራራኝም
እኔ ክርስቲያን ነኝ ወደ ኋላ አልልም
ብለህ ስትመሰክር ብቻህን ሆነህ
በመንፈስቅዱስ ፍቅር በረታ ልብህ
አዝ= = = = =
ጽናትህን አይቶ ዱድያኖስ ቢቆጣ
በትዕቢት ተነሳ ሥጋህን ሊቀጣ
የልዳው ሰማዕት ቅዱስ መምህር
ገድልህን ልናገር እንዲሆነኝ ክብር
አዝ= = = = =
መከራው ቢጸና ጊዮርጊስ ታግሶ
ቀራንዮ ሄደ በልቡ ገሥግሶ
እረዳቱን አውቆ ታምኖ የተሰማራ
ጊዮርጊስ በጸሎቱ ፈጣሪውን ጠራ
መዝሙር|
ፋንቱ ወልዴ
https://t.me/qidus_Michael_abate12
ማመስገን ብቻ ነው ስራዬ
መዘመር ተግባሬ
አንተ እማ አትለይም ከአንደበቴ
አንተ እማ አትነጥፍም ከከንፈሬ
ውለታህ ነው ውዴ የሚቀሰቅሰኝ
ማለዳ ማለዳ አዚመው የሚለኝ
የቀመስኩህ ውዴ
ያጣጣምኩት ፍቅር
እንዴት ያስችለኛል በአፌ ሳልናገር
ልናገር ያንተን ነገር
ላምልክህ ላውጅህ
በአዲስ መዝሙር
አልጠግብህ ባወራህ
አንተ እማ ልዩ ነህ
ኢየሱስ ልዩ ነህ
ወዳጄ ልዩ ነህ
ከቋንቋ ይልቃል ከቃላቴ በላይ
ምድር አትወስነው
አይከልለው ሰማይ
የፍቅርህን መጠን አለካውምና
እፁብ እፁብ ብዬ ላንሳልህ ምስጋና
ማረፍ ሆኖልኛል ስምህን ስጠራ
አሜን ነው መዝሙሬ
ስኖር ካንተ ጋራ
በናቁኝ ሰዎች ፊት ያማረው ነገሬ
ኢየሱስ ሆነህ ነው አዲሱ መዝሙሬ
በሞገስ ያቆምከኝ በጠላት ከተማ
አሜን ነው መዝሙሬ
ስኖር ካንተ ጋራ
ማጉረምረም አይኖርም
ማመስገን ብቻ ነው
ሲሞላም ሲጎድል ኢየሱስ ጌታ ነው
🌿🌿🌿🌿🌿🌿
━━━━━━━━━━━━
ዘማሪ ዘላለም ይንገስ
https://t.me/qidus_Michael_abate12
ትምክተ ዘመድነ /2/ ማርያም እምነ
ማርያም ትምክተ ዘመድነ
አዝ
የድነታችን አርማ የነፃነታችን
የህይወት መሠረት ነሽ ድንግል እናታችን
አንቺ ለኛ ዘርን ባያስቀር እንደ ጥንቱ እንደ ሰዶ ምድር
ሁላችን በጠፋን ነበር
/አዝ/
የአብርሀም ድንኳን ነሽ አምላክ ያደረብሽ
የጌዲዮን ፀምር ለይቶ ያከበረሽ
የኛ ቤዛ በጉ የተያዘብሽ
የዋህ ርግብ ከአበው ስር የተገኘሽ
እፀሳቤት የህይወት ሀረግ ነሽ
/አዝ/
አምላክ ከሰማይ ሆኖ ይቺን አለም ሲቃኝ
ንፅይት ቅድስት ሆነሽ ማርያም አንቺን ቢያገኝ
ትህትናሽን ህይወትሽን ወዶ
ቃል ሰው ሆነ ከሰማያት ወርዶ
አከበረሽ በፍፁም ተዋህዶ
/አዝ/
የመዳናችን ምክንያት የሰው ልጆች ሰላም
ከሀጢያት ከመርገም የዳነብሽ አለም
አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን
በሲኦል ውስጥ ተግዘን የኖርን
ድንግል ባንቺ ነፃነት አገኘን
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር
https://t.me/qidus_Michael_abate12
በስመዓብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
"በቀራንዮ የተከፈለውን ዋጋ ባሰብኩ ግዜ አንደበቴ ዝም ይል ዘንድ ልተወው አልችልም መንፈሴም እመሰክር ዘንድ ያነሳሳኛል።"
ተናገር አለኝ መስክር
ተናገር አለኝ ዘምር
ለቀራንዮ ውለታ
አርምሞ የለም ዝምታ
ለመድኃኔዓለም ውለታ
አርምሞ የለም ዝምታ
ሰው አድርጎኝ ሞቶ በደሙ
ኑሮዬን ባርኮት ሕመሙ
ሰላም አውጥቶ ካስገባ
ልያዝ ለክብሩ ዘንባባ
ሆሳዕና ልበል መድኃኒት
ከፍ በልልኝ የኔ አባት
ተጠምተኸ እኔ ረካሁ
ስራህ ግሩም ነው ደነቀኝ
አዝ_
እጆቹን እዩት በእምነት
ቆሰለ ሊሰጠኝ ሕይወት
በዚያ ታትሞ ውበቴ
እየሱስ ለኔ ብርታቴ
ከማንም በላይ ከምንም
ለኔ ልዩ ነው ዘላለም
ሕይወቴን ለእርሱ አስማርኬ
እኔስ በረታሁ በአምላኬ
አዝ_
የእሾህ አክሊሉ በራሱ
ለእኔ ቤዛ ነው ሞገሱ
ሞቴን ገድሎታል አባቴ
ሰላሜ እርሱ ነው እረፍቴ
ሰው የመሆኔ ምስጢሩ
የማይለወጥ ነው ፍቅሩ
የገባኝ እውነት በምድር ላይ
ፍቅር ነው ጌታ ኤልሻዳይ
አዝ_
ክብሩን ለማወጅ ተነሳሁ
ሲያድነኝ ከሞት እያየሁ
ገመና ሸፋኝ ኪዳኔ
ተራበ ውዴ መድኃኔ
ይሄ ነው የቆመኝ በፊቱ
ወሰን የሌለው ምሕረቱ
ለዚህ ደግነት ውለታ
ምን ይከፈላል ለጌታ
👉ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
https://t.me/qidus_Michael_abate12
🌼 እመኑ በእርሱ 🌼
እመኑ በእርሱ ድንቅ ያደርጋል ጌታ
በረዶ አዝንቦ ጠላት እየመታ
ውቅያኖስ ጥልቁን ፈጥኖ እያተነነ
ነገር ለወጠ ሁሉ በእርሱ ሆነ ፪
አዝ
እመኑ በርሱ.... ተራራው ነደደ
እመኑ በርሱ.... ሸለቆው ታወከ
እመኑ በርሱ.... ዝግባው ተሰባብሮ
እመኑ በርሱ.... አለቱ ደቀቀ
እመኑ በርሱ.... የአሕዛብ ጣኦታት
እመኑ በርሱ.... በፊቱ ረገፉ
እመኑ በርሱ.... በስሙ የታመኑ
እመኑ በርሱ.... ወጀቡን ቀዘፎ
አዝ
እመኑ በርሱ.... የማይነጋ ለሊት
እመኑ በርሱ.... የማያልፍ ቀን የለም
እመኑ በርሱ.... ሁሉም ይቻለዋል
እመኑ በርሱ.... ጌታ መድሃኒአለም
እመኑ በርሱ.... ፍቅር ነው ዘላለም
እመኑ በርሱ.... ደግ አባት ለልጁ
እመኑ በርሱ.... ሁሌ ተዘርግታ
እመኑ በርሱ.... ትኖራለች እጁ
አዝ
እመኑ በርሱ..... ሞገድ የማይሰብረው
እመኑ በርሱ..... ፅኑ መርከብ አለን
እመኑ በርሱ.... አንፈራም አንሰጋም
እመኑ በርሱ..... ከሱጋር እያለን
እመኑ በርሱ..... ጠላት ተሸንፏል
እመኑ በርሱ.... ሰይጣን አፍሯል ዛሬ
እመኑ በርሱ ..... ውህኒው ይነዋወፅ
እመኑ በርሱ.... በታላቅ ዝማሪ
አዝ
እመኑ በርሱ.... ባዶ ነው አይሰራም
እመኑ በርሱ.... የጠላት ፉከራ
እመኑ በርሱ.... የማይተወን ጌታ
እመኑ በርሱ.... አለ ከኛ ጋራ
እመኑ በርሱ.... እጅግ አትረፍርፎ
እመኑ በርሱ.... ፀጋ ከበዛልን
እመኑ በርሱ.... በሞት ጀርባ ቆመን
እመኑ በርሱ.... ገና እንዘምራለን
https://t.me/qidus_Michael_abate12
✞ማር ሊቀ ሰማዕት✞
ማር ሊቀ ሰማዕት ገባሬ መንክር
ጊዮርጊስ ኃያል(፪)
የዱድያኖስ አምላክ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ያንን ደራጎን - - ጊዮርጊስ ኃያል
አምላክ እንዳልሆነ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ገድለህ አሳየኸን - - ጊዮርጊስ ኃያል
የቤሩት ኮከብ ነህ - - ጊዮርጊስ ኃያል
የልዳ ፀሐይ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ለባሴ ሞገስ ነህ መክብበ ሰማዕት(፪)
አዝ= = = = =
መከራና ስቃይ - - ጊዮርጊስ ኃያል
እያጸኑብህ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ትናገር ነበረ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ስለ አምላክህ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ሥጋህን ፈጭተው - - ጊዮርጊስ ኃያል
ይድራስ ሲበትኑት - - ጊዮርጊስ ኃያል
ዳግመኛ አስነሳህ አምላከ ምሕረት(፪)
አዝ= = = = =
አንገትህ ሲታረድ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ምድር ተናወጠች - - ጊዮርጊስ ኃያል
ወተትና ውሃ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ደምም አፈለቀ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ሰብዐ ነገሥታት - - ጊዮርጊስ ኃያል
እስኪደነቁብህ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ሰባት አክሊላትን ጌታ አቀዳጀህ(፪)
አዝ= = = = =
የዚህን ዓለም ጣዕም - - ጊዮርጊስ ኃያል
ንቀኸው ጥቅሙን - - ጊዮርጊስ ኃያል
በፍቅር ተቀበልክ - - ጊዮርጊስ ኃያል
መራራ ሞትን - - ጊዮርጊስ ኃያል
ሰማይና ምድር - - ጊዮርጊስ ኃያል
ሳርና ቅጠሉ - - ጊዮርጊስ ኃያል
ሰማዕተ ክርስቶስ ቅዱስ ጊዮርጊስ አሉ(፪)
https://t.me/qidus_Michael_abate12
ጊዮርጊስ
ሰማዕተ ኢየሱስ የእውነት ምስክር
ህያውን ነው በሰማይ
ብፁዕ ነው በምድር
ደራጎንን በጦር ወግቶ ገደለና
ከሞት አዳነኝ ጊዮርጊስ ደረሰና
የሀዘን ማዕበል እንዳያንገላታኝ
ታምር ሰሪው ሰማዕት ፈጥኖ አረጋጋኜ
በእግዚአብሔር ጣዕም በፍቅሩተጠምዷል
ይህን አለም ንቆ በክብር አጊጧል
አፍጣኒተ ረድኤት ቅዱስ ጊዮርጊስ
ፈጥነህ የምትደርስ ከአውሎ ነፋሴ
ስምህ የተጠራ የኢትዮጵያ ገበዝ
አድናት ሃገሬን ከገጠማት ትካዝ
እርሱ ለምጠራው ሲመሽም ሲነጋ
ዋስ ጠበቃዬ ነው በነፍስም በስጋ
ድንቅ የሚፈፅም ሀያል ሰማዕት ነው
በቅድመ እግዚአብሔር ለእኔ የሚቆመው
አፍጣኒተ ረድኤት ቅዱስ ጊዮርጊስ
ፈጥነህ የምትደርስ ከአውሎ ነፋሴ
ስምህ የተጠራ የኢትዮጵያ ገበዝ
አድናት ሃገሬን ከገጠማት ትካዝ
የምስጋናን አውታር የታጠቀ ሰማዕት
ስሙን ተሸክሞ የታመነ እስከሞት
ሙታንን የሚያስነሳ ስልጣን ተቀብሏል
በአባቱ መንግስት እንደ ፀሐይ ደምቋል
አፍጣኒተ ረድኤት ቅዱስ ጊዮርጊስ
ፈጥነህ የምትደርስ ከአውሎ ነፋሴ
ስምህ የተጠራ የኢትዮጵያ ገበዝ
አድናት ሃገሬን ከገጠማት ትካዝ
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
https://t.me/qidus_Michael_abate12
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈