ar
Feedback
Bashewam Primary & Junior School 1-8

Bashewam Primary & Junior School 1-8

الذهاب إلى القناة على Telegram

Bashewam School Grade 1-8

إظهار المزيد
2 750
المشتركون
+324 ساعات
+327 أيام
+4330 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

photo content

photo content

photo content

የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ድረስ ይሰጣል #የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 የትምህርት ዘመን የሚካሄዱ ፈተናዎች የሚሰጡባቸውን ቀናት ይፋ አደረገ። #በዚህም መሰረት የሪሚዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ 20፣ የቅደመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ 12 እንዲሁም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ #በተመሳሳይ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከሐምሌ 29 እና 30 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሰጥ፤ የመሰረታዊ የንብባና የስሌት ክህሎት ምዘና ፈተና ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት ውስጥ ይሰጣል፡፡ #የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር )÷ እስከ ተጠቀሱት ጊዜያት ድረስ ተፈታኞች አስፈላጊውን የይዘትና የስነ-ልቦና ዝግጅት እንዲደርጉ አስገንዝበዋል። ወላጆች፣ መምህራንና በየደረጃው ያለው የትምህርት አመራር ተፈታኞቻቸው የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል፡፡ ለተጨማሪ መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬ https://t.me/moedu123

ለውድ የተማሪ ወላጆች ፡ የ3ኛው ሩብ አመት የማጠቃለያ ፈተና ሚያዝያ 13--16/2018ዓም የሚሰጥ መሆኑን በደብዳቤ ማሳወቃችን ይታወቃል፡ ሆኖም ግን የልጅዎ የትምህርት ቤት ወርሐዊ ክፍያ ፡ የማጠናከሪያ ትምህርት ክፍያ እና የሰርቪስ /ትራንስፖርት/ ክፍያ  ከማጠቃለያ ፈተና አስቀድማችሁ እንድትከፍሉ እያሳሰን፡ የሚያዝያ ወር የትምህርት ቤት ክፍያ በተለያየ ምክንያት ያልከፈላችሁ ወለጆች እስከ ሚያዝያ 16/2018ዓም ድረስ ያለቅጣት መክፈል የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

ውድ ወላጆች ከ1-4ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የፈተና ፕሮግራም በኮመኒኬሽን መፅሐፍ ላይ የተለጠፈላቸው ስለሆነ ፡ በተላከው መረሐ ግብር መሰረት ተማሪዎችን በማስጠናት እንዲያግዟቸው እናሳስባለን።

photo content

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ተማሪዎች፡ ወላጆች፡ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች፡ በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደ
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ተማሪዎች፡ ወላጆች፡ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች፡ በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን መልካም የትንሳኤ በዓል ይሁንላችሁ! ባሸዋም ትምህርት ቤት ትውልድ እንቀርፃለን፡  ሁሌም ለለጥ ዝግጁ ነን !

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ተማሪዎች፡ ወላጆች፡ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች፡ በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደ
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ተማሪዎች፡ ወላጆች፡ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች፡ በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን መልካም የትንሳኤ በዓል ይሁንላችሁ! ባሸዋም ትምህርት ቤት ትውልድ እንቀርፃለን፡  ሁሌም ለለጥ ዝግጁ ነን !

photo content
+3

photo content
+1

photo content
+2

photo content
+1

photo content
+1

👉በቀን 25/07/2018ዓ.ም የወርሃዊ የስራ አፈፃፀም ግምገማ የመማር ማስተማር ሂደትን, የተማሪዎች ዉጤት ትንተና,የተማሪዎች ስነ-ምግባር, የተጕዳኝ ትምህርት እንቅስቃሴን በተመለከተ የስራ አፈፃፀም ገምገማ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የመማር ማስተማር ቅድመ ዝግጅትና የተማሪዎች ዉጤት አያያዝ ላይ የእዉቀት ሽግግር ተካሄደ:: 👉በእለቱ የእዉቀት ሽግግር ላቀረቡልን 👉መ /ር ጌቱ ሙሉጌታ👉የተማሪዎች ዉጤት ትንተና ሪፖርት ላቀረቡልን 👉ም/ር/መ/ር አቶ መስፈን ለገሰ, 👉ንቁ ተሳትፎ ላደረጋችሁ 👉መ/ራን እና የት/ቤት አመራር በት/ቤቱ ስም ከልብ እናመሰግናለን::

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎች ይፋ ሆኑ # የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅባቸውን የትምህርት ዓይነቶችና የክፍል ደረጃዎችን ይፋ አድርጓል። #በዚሁ መሠረት ፈተና የሚሰጥባቸው የትምህርት አይነቶች በተፈጥሮ ሳይንስ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪና ፊዝክስ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው። ፈተናው በየትምህርት ዓይነቱ ከ9ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች የሚሸፍን ይሆናል። የዝግጅት አግባቡም 9ኛ ክፍል ላይ የቀድሞውና የአዲሱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘት ላይ ያተኩራል። ከ10ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ያለው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ይሆናል። የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ሆኖ ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን የሚሸፍን መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡ ለተጨማሪ መረጃዎች https://t.me/moedu123

#​የ2018 የብሔራዊ ፈተና ዝግጅት "ካርታ" ይፋ ሆኗል! 📍 ​ለተማሪዎች ትልቅ የምስራች! የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የ12ኛ ክፍል ፈተና በምን መልኩ እንደሚዘጋጅ ይፋዊ መግለጫ አውጥቷል። ራሳችሁን አሁኑኑ ለማዘጋጀት ይህንን መረጃ በሚገባ ተረዱት! ​📚 ፈተናው የሚካተቱባቸው የትምህርት ዓይነቶች ​🔬 ለተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science): ​እንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ (Aptitude)፣ ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ እና ፊዚክስ። ​🌍 ለማህበራዊ ሳይንስ (Social Science): ​እንግሊዘኛ፣ ሒሳብ፣ ስኮላስቲክ አፕቲትዩድ (Aptitude)፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ እና ኢኮኖሚክስ። ​🔍 ፈተናው ከየትኛው ክፍል ይወጣል? (አዲሱ መመሪያ) ​በጣም ሊታወቅ የሚገባው ነጥብ እዚህ ጋር ነው! ፈተናው 👉 ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፦ 👉​9ኛ ክፍል፦ የድሮውና የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የጋራ ይዘቶች (Common Contents) ላይ ያተኩራል። 👉​ከ10ኛ - 12ኛ ክፍል፦ ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ላይ የተመሠረተ ይሆናል። ​ልዩ ማሳሰቢያ ለኢኮኖሚክስ፦ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ብቻ ይወጣል። ​💡 የስኬት ቁልፉ ምንድነው? 👉​አሁኑኑ ይጀምሩ፦ ከ9ኛ ክፍል ጀምሮ ያሉትን የጋራ ይዘቶች መከለስ አይርሱ። 👉​አዲሱን ስርዓተ ትምህርት ይላመዱ፦ አብዛኛው የፈተና ይዘት በአዲሱ መፅሐፍ ላይ የተመሰረተ ነው። 👉​ታማኝነት ያሸንፋል፦ የፈተና ስርቆትንና ኩረጃን በጋራ በመከላከል የለፋችሁበትን ውጤት ተቀዳጁ! 💪 ​🔔 ይህ መረጃ ለጓደኞችዎ እንዲደርስ "Share" ያድርጉት! አንድ ላይ ሆነን ለተሻለ ውጤት እንዘጋጅ! 🎓✨ ​#Ethiopia #Grade12 #NationalExam #Education #2018E.C #Success #Students #ኢትዮጵያ

የ8ኛ ክፍል የክልል አቀፍ ፈተና የ2015፣2016፣ እና 2017 ጥያቀዎችን በዚህ መለማመድ ይችላሉ 👆