ar
Feedback
Secrets of Truth - 𝘽𝙮 𝙍𝙚𝙨𝙝𝙖𝙙

Secrets of Truth - 𝘽𝙮 𝙍𝙚𝙨𝙝𝙖𝙙

الذهاب إلى القناة على Telegram

● ዲናችንና በሚመለከት ወቅታዊ መረጃዎችን ➶ Current information about Muslims and Islam 🔗 ሌሎችንም አንገብጋቢ ጉዳዮችን የምንተዋወስበት Channel ነው‼️ ➞ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አጠር ያሉ ስንኞች (በተለይም ስለ ፈለስጢን 🇵🇸) 🎯 አላማዬ:- የእውነትን ሚስጥሮች ማጋለጥ ነው‼️ #Free_Palestine 🇵🇸

إظهار المزيد
213
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-17 أيام
-430 أيام
أرشيف المشاركات
📚 መፅሀፍትን ስናነብ 📚 መፅሀፍት ዝም ብለው አይፃፉም። ታሪክን ከመሀረክ ከማስተላለፍ በዘለለ በአንባቢው ህይወት ውስጥ የሚፈጥሩት አንዳች ነገር ወይም አላማ አለ ተብሎ ይታመናል። 🕞 ስለዚህ ጊ
📚 መፅሀፍትን ስናነብ 📚 መፅሀፍት ዝም ብለው አይፃፉም። ታሪክን ከመሀረክ ከማስተላለፍ በዘለለ በአንባቢው ህይወት ውስጥ የሚፈጥሩት አንዳች ነገር ወይም አላማ አለ ተብሎ ይታመናል። 🕞 ስለዚህ ጊዜን ለማሳለፍና ለመዝናኛ ከማዋል በዘለለ በህይወቴ ላይ ምን ፋይዳ አመጣ ማለት መልካም ይመስለኛል።ለዚህ ደግሞ አጭር ማስታወሻን እየያዙ ማንበብ በጣም ጠቃሚ ነው። 📚 በመፅሀፉ ውስጥ ያነበብነውን ሀሳብ ወይም አንድ አረፍተ ነገር በተለያዩ ቦታዎችና በውይይቶች ላይ ማሰላሰል የመፅሀፉን አላማ ከመረዳትም በዘለለ በህይወቴ ምን ነገረኝ የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ይረዳል። በእኔ አስተሳሰብ ጎበዝ እንባቢ መፅሀፍን በትንሽ ጊዜ አንብቦ የጨረሰ ሳይሆን፤ መፅሀፉን ለሚገባው ጥቅም ያዋለ ወይም በትክክል ከመፅሀፉ የተጠቀመ ሰው ነው። ስለዚህ በምናነብበት ጊዜ አጭር አጭር ነገሮችንና ዋና ሀሳቡን በመያዝ እነሱንም በማሰላሰልና ጠቃሚ ነገሮችን ከህይወታችን ጋር ለማዋሀድ ጊዜ ይኑረን!! ✅ ማንበብ መሰልጠን ነው❕ ✅ ማንበብ በእውቀት መብሰል ነው❕ ✅ ማንበብ ዕርድና ነው ❕ ✅ ማንበብ በጥሩ ቅመሞች ተቀምሞ እንደተሰራ ወጥ የራስን ስብዕና ማጣፈጥ ነው❕ ✅ የሚያነብ ሰው ዛሬንና የቀደመ በታሪክ ጠንቅቆ የሚያውቅ ሰው ይሆናል ❕ ✅ የሚያነብ ሰው ሁሌም የመፍትሄ ሰው ነው❕ ✅ የሚያነብ ሰው በወንዝ ዳር እንደተተከለ ፍሬዋንም በየግዜው እንደምትሰጥ ለምለም ዛፍ ነው❕ ◉ ማንበብ ማንበብ እና ማንበብ!! እናንብብ፤ እንወቅ፤ እንብሰል፤ እንመርምር፤ እንጠይቅ፤ እንሰልጥን‼️          ➴ማንበብ ባህል ነው ❕       ➴ማንበብ መሉ መሆን ነው❕        ➴ማንበብ መሰልጠን ነው❕ 📚 እናምብብ❕ እናምብብ❕ በማምበብ እውቀትን ትጋትን ባህልን እናሳድግ! የመፍትሄ ሰው እንሁን! ©️ 📚 ለተማሪዎች የተላለፈ መልዕክት

Night 25 in Masjid Al Haram
Night 25 in Masjid Al Haram

AnimatedSticker.tgs0.18 KB

AnimatedSticker.tgs0.17 KB

Spectacular Images of Masjid Al Haram last night !
+2
Spectacular Images of Masjid Al Haram last night !

💬 የዕለቱ መልዕክት... 💬 💡💡💡💡💡 🔰 በህይወት እያለህ አንተን ይበልጥ የሚገድልህ በሰዎች አልያም በፈተናዎች መጎዳትህ፣ መጎሳቆልህ፣ ወድቀሀል መባልህ ሳይሆን ዳግም የመመለስ፣ ራስህን
💬 የዕለቱ መልዕክት... 💬 💡💡💡💡💡 🔰 በህይወት እያለህ አንተን ይበልጥ የሚገድልህ በሰዎች አልያም በፈተናዎች መጎዳትህ፣ መጎሳቆልህ፣ ወድቀሀል መባልህ ሳይሆን ዳግም የመመለስ፣ ራስህን የማደስ፣ አዲስ ራዕይ እንዲኖርህ የሚያደርግ «ተስፋ» ከሌለህ ነው❗️ ወንድምና እህቶቼ ተስፋ አትቁረጡ። ➤ ጊዜው ረፍዶብኛል.....፣ ➤ ካሁን በኋላ ሁለንም የትምህርት አይነት ጨርሼ ማንበብ አልችልም ወይም ይህ ትምህርት አይገባኝም አትበሉ። አዎ ወንድምና እህቶቼ..... እስካሁን ማንበብ ካልጀመራችሁ እራሱ አሁኑኑ ጀምሩ! ✅ የምትችሉትን ሁሉ ጥረት አድርጉ፤ ጥረት ካደረጋችሁ በኋላ በአላህ ሙሉ ተስፋ ይኑራችሁ። ✅ አላህ ለቤተሰብ ደስታ፣ ለማህበረሰቡ ተድላ፣ ስኬትና ግርማሞገስ ሰበብ የሚሆንን ውጤት ይሰጣችኋል። ኢንሻአላህ!! ✍️ በወንድማችሁ:- ረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል ══════════════ 📚 ለተማሪዎች የተላለፈ መልዕክት ══════════════ ይ🀄ላ🀄ሉን👇👇👇 share👇 Join our channel ➊ t.me/Grade1_4Infot.me/Grade5and6Infot.me/Grade7Infot.me/Grade8Infot.me/Grade9Infot.me/BasicComputer_Skills

Masjid Al Haram pictured tonight 23 Ramadan 1446
+1
Masjid Al Haram pictured tonight 23 Ramadan 1446

በ1 ሪያል 5 ዳቦ‼ ለተከታታይ 12 አመታት የዘለቀና አሁንም ያለ፤ በሃገረ ሳዑዲ ዓረቢያ በ1 ሪያል 5 ዳቦ ይገዛል። በቀን ያ ሁሉ 10 ሚሊዮን አዲስ የውጭ እንግዳ መካ ላይ ጠግቦ ውሎ ጠግቦ ያድራ
በ1 ሪያል 5 ዳቦ‼ ለተከታታይ 12 አመታት የዘለቀና አሁንም ያለ፤ በሃገረ ሳዑዲ ዓረቢያ በ1 ሪያል 5 ዳቦ ይገዛል። በቀን ያ ሁሉ 10 ሚሊዮን አዲስ የውጭ እንግዳ መካ ላይ ጠግቦ ውሎ ጠግቦ ያድራል። የሚገዛውና የሚበላው አያጣም። የበረካና የእዝነት ምድር የሆነ የተባረከ ቦታ‼ አላህ ይጨማምርላቸው‼ Unchanged for over a decade! In Saudi Arabia, bread prices have remained the same for 12 years—5 pieces for just 1 riyal! || t.me/MuradTadesse

مشاهد جوية لأجواء المسجد النبوي في رمضان Aerial scenes of the atmosphere of Masjid Al Nabawi this Ramadan.
+5
مشاهد جوية لأجواء المسجد النبوي في رمضان Aerial scenes of the atmosphere of Masjid Al Nabawi this Ramadan.

የሸይኽ ሹረይም ወርቃማ ምክሮች

የዛሬዋ ለሊት ለይለተል ቀድር በጣም የሚከጀልባት ለሊት ናት! "ጁምዓ ሌሊት ከረመዳን የመጨረሻው አስርት ቀናት ጎዶሎ ቁጥር ያላቸው ሌሊቶች (21፣ 23፣ 25፣ 27፣ 29) ጋር ብትገጥም፣ እርሷ ለይለቱል ቀድር ለመሆን ይበልጠ የቀረበች ናት።"**" ❤️ — ኢብን ሩጀብ ከኢብን ሁበይራ "ለጣኢፍ አልማዓሪፍ" ውስጥ ጠቅሰውታል።

🌿🌿🌿🍃ጥቆማ🍃🌿🌿🌿 ጥቂት ነጥቦች ስለ ኢዕቲካፍ! ~ 🌿ትርጓሜው፦ ለአላህ ዒባዳ ለመፈፀም በማሰብ መስጂድ ውስጥ መቆየት ማለት ነው። 🌿ብይኑ፦ በቁርኣን በሱና የተረጋገጠ ሙስተሐብ (የተወደደ) ዒባዳ ነው። ስለት ለተሳለበት ሰው ግዴታ ይሆናል። አዕቲካፍ ለሴቶችም የተፈቀደ ነው። 🌿 አላማው፦ ልብንም አካልንም ስብስብ አድርጎ በዒባዳ መጠመድ ነው። ኢዕቲካፍ የገባ ሰው ከትርፍ ወሬ፣ ከትርፍ ቅልቅል፣ ከትርፍ እንቅልፍ መቀነስ ይገባል። 🌿ጊዜው፦ አብዛኞቹ ዑለማእ ዘንድ በረመዷንም ይሁን ከረመዷን ውጭ መፈፀም ይቻላል። በላጩ ጊዜ ግን ረመዷን ነው። ከረመዷንም የመጨረሻዎቹ አስሮቹ የበለጡ ናቸው። 🌿ቦታው፦ ለወንድም ይሁን ለሴት መስጂድ ውስጥ ብቻ ነው። 🌿 የጀመረ ሰው መጨረስ ግዴታ ነው? የሚያስገድድ ማስረጃ የለም። 🌿ዝቅተኛው ጊዜ ምን ያህል ነው? ገደብ የለውም። ያሰኘውን መጠን ያክል ነይቶ መቀመጥ ይችላል። 🌿ኢዕቲካፍ የገባ ሰው ለመፀዳዳት መውጣት ይችላል። የታመመን ለመጠየቅ፣ ጀናዛ ለመሸኘትና መሰል ጉዳዮች ግን አይወጣም። ግንኙነት፣ ግብይት፣ ስራ መስራት አይቻልም። ኢዕቲካፍ ላይ እያለ የታመመ ሰው መታገስና መቆየት የሚችል ከሆነ መውጣት የለበትም። 🌿የረመዷን የመጨረሻዎቹን አስር መግባት የፈለገ መቼ ይጀምር? የረመዷን 20ኛው ቀን ከመጥለቋ በፊት ቢሆን መልካም ነው። 🌿የሚወጣበት ደግሞ ረመዷን ተጠናቆ የዒድ ሌሊት ሲገባ ነው። ወላሁ አዕለም። ✍IbnuMunewor 🌿🌿🌿🍃ጥቆማ🍃🌿🌿🌿 የሌሊት ሶላት ~ ተራዊሕ፣ ተሀጁድ እና የሌሊት ሶላት የሚባሉት ለተለያዩ ሶላቶች የተሰጡ የተለያዩ ስያሜዎች አይደሉም። ይሄ የኢስጢላሕ ጉዳይ ነው። ትኩረት ልንሰጥ የሚገባው ከቃሉ ይልቅ ጭብጡ ላይ ነው። የሌሊት ሶላት የሚለው ተሀጁድንም፣ ተራዊሕንም ይገልፃል። ተራዊሕ የሚለውን ቃል ዑለማኦች በረመዷን ወር ከዒሻእ በኋላ በጀማዐ የሚሰገደውን ሶላት ለመግለፅ ይጠቀሙታል። ልብ በሉ! ከአፈፃፀሙ በስተቀር አመቱን ሙሉ ካለው የሌሊት ሶላት የተለየ አይደለም። ተሀጁድ ሰዎች ሌሊት ተነስተው የሚሰግዱት ሶላት ነው። የሌሊት ሶላት ወቅቱ ከዒሻእ ሶላት በኋላ ጀምሮ እስከ ፈጅር ድረስ መሆኑ ይታወቃል። ስለዚህ እነዚህ ሶስት ስያሜዎች (ተራዊሕ፣ ተሀጁድ እና የሌሊት ሶላት) የአንድ ሶላት መጠሪያዎች ናቸው ማለት ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ትንሽ ማለት የፈለግኩት አመት ጠብቆ መነታሪኪያ ስለሚሆን ነው። ነጥቡን ለማጥራት ከመሞከሬ በፊት አንድ ቀዳሚ ነጥብ ላንሳ። እሱም በርእሱ ላይ የትኛውንም አቋም ብንይዝ ሃሳባችን ቢለያይ እንኳ በልክ እንሁን። ዑለማኦች የተለያዩበት፣ ከመለያየታቸውም የጎሪጥ ያልተያዩበት ጉዳይ እንደሆነ አውቀን እነሱ በያዙት መጠን እንያዘው። ዑለማኦች ብቻ ሳይሆኑ ራሳችንም በጉዳዩ ላይ ያለን አቋም ሊቀያየር ይችላል። ከስሜት ነፃ እስከሆን ድረስ ይሄ የሚጎዳ አይደለም። ወደ ነጥቦቹ ልግባ፦ 🔻1. የተራዊሕ ሶላት "መልካም" ቢድዐ ሳይሆን በቀጥታ ከነብዩ ﷺ የተገኘ ሱና ነው። [ቡኻሪይ፡ 872] [ሙስሊም፡ 1271] ከዚያም በአንድ ጀማዐ መስገዱ ተቋርጦ ከፊሉ በጥቂት በጥቂት ተከፋፍሎ ከፊሉ ደግሞ በተናጠል ሲሰግድ ከቆየ በኋላ ልክ በነብዩ ﷺ ኢማምነት ተጀምሮ እንደነበረው በአንድ ጀማዐ በዑመር አማካኝነት ተሰብስቧል። [ቡኻሪይ፡ 2010] 🔻2. ቁጥሩ ከነብዩ ﷺ በተግባር የተገኘው እስከ 11 ረከዐ ድረስ ነው። ይህንን ይዘው ጭማሪው ቢድዐ ነው ያሉ አሉ፤ የብዙሃን ዑለማእ ምርጫ ባይሆንም። የነብዩን ﷺ ቃላዊ መረጃዎች እና የቀደምቶችን አፈፃፀም ለተመለከተ ግን ጉዳዩ በቢድዐ ለመግለፅ የሚያስደፍር አይደለም። ስለዚህ ከአንድ አቅጣጫ ጥናት በመውጣት ጠለቅ ብሎ በማየት ጥንቃቄ ቢኖረን ይመረጣል። ከመሆኑም ጋር አፈፃፀማችንን ከነብዩ ﷺ ተግባራዊ አፈፃፀም ማለትም 11 ረከዐ ጋር ብናጣጥም የበለጠ ነው፣ ወላሁ አዕለም። 🔻3. በረመዷን የመጨረሻው 10 ላይ ሌሊት ላይ ተነስቶ መስገዱ ቢድዐ ይደርሳል? በፍፁም! 🔻3.1. ከጊዜ አንፃር፦ ሙሉ ሌሊቱ የሶላት ወቅት ነው። እንዲያውም ለሚችል ሰው የሌሊቱ መጨረሻ ከመጀመሪያው በላጭ ነው። በላጭ በሆነ ወቅት ላይ መሰባሰቡ ከቢድዐ ጋር የሚገናኝበት ነጥብ የለም። 🔻3.2. አፈፃፀም፦ በጀማዐ መስገድም ቢሆን ተጨባጭ መረጃ የመጣበት ስለሆነ በዚህም በኩል ክፍተት የለም። 🔻3.3. በመጨረሻው አስር ላይ ትጋት መጨመሩ፦ ተጨባጭ መረጃዎች የመጡበት ነው። አንድ ሁለት ልጥቀስ፦ ከእናታችን ዓኢሻ ተይዞ እንዲህ ብላለች፦ كان رسول الله صلى الله عليه وسلم إذا دخل العشر أحيا الليل، وأيقظ أهله، وجدَّ وشدَّ المئزر "የአላህ መልእክተኛ ﷺ የመጨረሻው አስር ሲገባ ጊዜ ሌሊቱን በንቃት ያሳልፉ፣ ቤተሰባቸውን ያነቁ፣ በእጅጉ ይጣጣሩና ትጥቃቸውን ያጠብቁ ነበር።" [ቡኻሪይ፡ 2024] [ሙስሊም፡ 1174] 🌿* ሌሊቱን በንቃት ያሳልፉ ነበር ማለት በዒባዳ ንቁ ሆነው ማለት ነው። 🌿* ቤተሰባቸውን ያነቁ ነበር ማለት ለሌሊት ሶላት ነው። 🌿* ትጥቃቸውን ያጠብቁ ነበር ማለት ከሴት ያገሉ ወይም ዒባዳ ላይ ያላቸውን ትጋት ከቀደመው ይጨምሩ ነበር ማለት ነው። [ፈትሑልባሪ፡ 4/316] በሌላም መረጃ እናታችን ዓኢሻ እንዲህ ብላለች፦ كان رسول الله صلى الله عليه وسلم يجتهد في العشر الآخر ما لا يجتهد في غيره "የአላህ መልእክተኛ ﷺ በመጨረሻው አስር ላይ በሌላው ላይ የማይተጉትን በተለየ ይተጉ ነበር።" [ሙስሊም፡ 1175] 🔻3.4. ቁጥሩ፦ ከ11 በላይ መስገድ ይቻላል የሚል ሰው እዚህ ላይ ጥያቄ ሊያነሳ አይገባም። አይቻልም ለሚል አካል ግን ዐምር ብኑ ዐበሰህ ረዲየላሁ ዐንሁ "የትኛው የሌሊቱ ክፍል ነው ይበልጥ ለዱዓእ ተቀባይነት በላጭ የሆነው?" ብለው ሲጠይቋቸው ነብዩ ﷺ እንዲህ ሲሉ መልሰዋል፦ فصلِّ ما شئتَ فإنَّ الصَّلاةَ مشْهودةٌ مَكتوبةٌ حتّى تصلِّيَ الصُّبحَ "ያሻህን ስገድ። በዚህ ጊዜ የሚሰገድ ሶላት መላእክት የሚጣዱባት ነችና። ፈጅር እስከምትሰግድ ድረስ።" [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 1277] በተጨማሪም እንዲህ ብለዋል፦ صلاة الليل مثنى مثنى فإذا خشي أحدكم الصبح صلى واحدة توتر له ماقد صلى. "የሌሊት ስግደት ጥንድ ጥንድ ነው። አንዳችሁ ንጋትን ከሰጋ የሰገደውን ዊትር ታደርግ ዘንድ አንድ ረከዐ ትሰግዳለህ።" [ቡኻሪይ፡ 472] [ሙስሊም፡ 749] 🔻3.5. በአንድ መስጂድ ላይ ድጋሚ ጀማዐ መቋቋሙም ቢሆን ለተቃውሞ የሚቀርብ አይደለም። ምክንያቱም ዑመር በአንድ እስከሚሰበስቡት ድረስ በአንድ መስጂድ ውስጥ የተለያዩ ጀማዐዎች ሲቋቋሙ ነበርና። ስለዚህ ማታ ለሰገደም ይሁን ላልሰገደ ሌሊት ላይ በጀማዐም ይሁን ለብቻ መስገድ ይችላል። ከዊትር በኋላ መስገድም መረጃ መጥቶበታል። ባይሆን ሁለት ጊዜ ዊትር አይሰገድም። "በአንድ ሌሊት ሁለት ዊትር የለምና።" [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 7567] ወላሁ አዕለም! ✍IbnuMunewor https://t.me/ibnukedir

🌙 🌙 ቀን 2⃣0⃣ ረሱል (☪) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿تَحَرَّوْا لَيْلَةَ الْقَدْرِ فِي الْعَشْرِ الْأَوَاخِرِ مِنْ رَمَضَانَ﴾ “ለይለተል ቀድርን በመጨረሻ
🌙 🌙 ቀን 2⃣0⃣ ረሱል (☪) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿تَحَرَّوْا لَيْلَةَ الْقَدْرِ فِي الْعَشْرِ الْأَوَاخِرِ مِنْ رَمَضَانَ﴾ “ለይለተል ቀድርን በመጨረሻ አስር የረመዳን ቀናቶች ውስጥ ፈልጉት።” 📚 ቲርሚዚ ሶሂህ ብለውታል: 792 ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ ✅ በነዚህ አድራሻዎች ይከታተሉን፦ 🌐፦ https://bit.ly/4ayf0xJ 💬፦ https://bit.ly/486xnrS 🌐፦ https://bit.ly/41zEZkk 🌐፦ https://bit.ly/4arMbTx 🌐፦ https://bit.ly/41tIUPv 🌐፦ https://bit.ly/3UTTSwh