Mark Tech Info | Mark Technology Information
الذهاب إلى القناة على Telegram
Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot
إظهار المزيد6 218
المشتركون
-324 ساعات
-337 أيام
-31730 أيام
أرشيف المشاركات
‼️በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሚገኙ 50 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 80 በመቶ የሚሆኑት ከደረጃ በታች ናቸው፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር
ከደረጃ በታች የሆኑ ትምህርት ቤቶችን ለማሻሻልና ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን በትምህርት ሚኒስቴር ፕሮግራሞችና ጥራት ማሻሻያ ኃላፊ ዳዊት አዘነ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል፡፡
በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ እስካሁን ከ7,900 በላይ የቅድመ መደበኛ፣ 1ኛ ደረጃ እና 2ኛ ደረጃ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን የገለፁት ኃላፊው፤ የ29,900 ትምህርት ቤቶች እድሳትና ጥገና ሥራ መከናወኑን ገልፀዋል፡፡
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
"የቤት ስራ አልሰራሽም" በሚል በአንዲት ተማሪ ላይ ተገቢ ያልሆነ ቅጣት የፈጸመችው መምህርት በቁጥጥር ስር ዋለች
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በሰላም በር አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2ኛ ክፍለ ተማሪን "የቤት ስራ አልሰራሽም" በማለት ተገቢ ያልሆነ ቅጣት በፈጸመችው መምህርት ላይ እርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።
ትውልድን ከመቅረፅ፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ተተኪ ዜጋን ከመፍጠርና የቀለም እናት ከመሆን ባለፈ ከእናት የማይጠበቅ፤ ያለንበትን ዘመንና ወቅት የማይዋጅና የማይመጥን መሰል ድርጊት መፈጸም ተገቢ አይደለም ብሏል።
ድርጊቱ እንደተፈጸመ ጥብቅ ክትትል በማድረግ ወዲያውኑ የማጣራት ስራዎች እንዲሰሩና መምህርቷ በህግ ከለላ ውስጥ እንድትሆን መደረጉም ተገልጿል።
ጉዳዩም በህግ አግባብ እንዲታይና ፍትህ እንዲያገኝ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።
ጉዳቱ የደረሰባት ተማሪም ህክምና አግኝታ በጥሩ የጤንንነት ሁኔታ ላይ የምትገኝ ሲሆን በነገው እለትም ትምህርቷን ትጀምራላች ተብሏል፡፡
መሰል ችግሮች እንዳይፈጸሙና ለሌሎችም ትምህርት እንዲሆን ይህ ርምጃ መወሰዱም ነው የተገለጸው።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
ናሚቢያ ትምህርት በነፃ እንዲሰጥ ወሰነች❗️
የሀገሪቱ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዝዳንት ኔቱምቦ ናንዲ ከ2026 በሃገሪቱ ባሉ በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ ተቋማት ዩኒቨርስቲና ኮሌጅ ትምህር በነፃ እንዲሰጥ ተወሰነ ።
ፕሬዘዳንቷ ሀሙስ ማምሻውን ባደረጉት ንግግር ሀገሪቱ የሚገኙ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እና የቴክኒክ ኮሌጆች “ምንም የምዝገባ [ወይም] የትምህርት ክፍያ አይከፍሉም ለተማሪዎቹም የምግብና መሰረታዊ ወጭዎች በመንግሥት ይሸፈናል ።አቅም ለሌላቸዉም ድጎማ እና የገንዘብ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል ።
አክለዉም የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት በሁሉም የሀገሪቱ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ነፃ በሚሰጥባት ናሚቢያ ለትምህርቱ ዘርፍ ትኩረት በመስጠት ከቀጣይ አመት ጀምሮ የሀገሪቱ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በነፃ ለማስተማር መንግስታቸው ከፍተኛ በጀት መመደቡን ገልፀዋል ሲል የዘገበው ቢቢሲ ነዉ ።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️" የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።
ሚኒስትሩ ፥ " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና በተናገሩበት ወቅት 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ብርሃኑ (ፕሮፌሰር) ፥ " እንደ ከዚህ ቀደሙ አድካሚ በሆነ ከቦታ ቦታ ልጆችን እያዘዋወሩ ከመሄድ ባለፈው ዓመት 29 ሺህ ተማሪ ነበር ኦንላይን ፈተና የሰጠነው ዘንድሮ ደግሞ 150 ሺህ ተማሪ ኦንላይን ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጀን ነው " ብለዋል።
ሚኒስትሩ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
150ሺህ ተማሪዎች በኦንላይን ይፈተናሉ ‼️
ከጥቂት ሳምንታት በኋላ በሚሰጠው የዘንድሮ የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተና 150ሺህ ተማሪዎች በኦንላይን ለማስፈተን ዝግጅት መጠናቀቁን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ባለፈው ዓመት በተሰጠው የዩንቨርሲቲ መውጫ ፈተና 29ሺህ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናውን መውሰዳቸው ይታወሳል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️" ከ2019 ጀምሮ 3ኛ ዓመት የጨረሱ ተማሪዎች 4ኛ አመት ከመግባታቸው በፊት የ1 ዓመት አገልግሎት እንዲሰጡ ይደረጋል " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)
በዩኒቨርሲቲ የሚማሩ 3ኛ ዓመት የጨረሱ ተማሪዎች 4ኛ ዓመት ሳይገቡ በፊት የአንድ ዓመት አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ የተጀመረው እንቅስቃሴ ከ2019 ዓ/ም ጀምሮ ተግባር ላይ እንደሚውል የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ጠቁመዋል።
ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ፤ " በሚቀጥለው ዓመት ላይደርስልን ይችላል ግን ህጋዊ ስርዓቱን በሙሉ ጨርሰን በ2019 ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚማሩ 3ኛ ዓመት የጨረሱ ተማሪዎች ከ2019 ጀምሮ 4ኛ አመት ከመግባታቸው በፊት የ1 ዓመት አገልግሎት እንዲሰጡ ይድረጋል " ብለዋል።
" ከዚህ በፊት የነበረ ነው አዲስ አይደለም በጃንሆይ ጊዜ (በአጼ ኃይለስላሴ ጊዜ ማለታቸው ነው) የነበረ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ሁለት ጥቅም አለው ብለን ነው ይሄን የምናደርገው አንደኛ ልጆቹ ዝም ብሎ የቀለም ትምህርት ብቻ ተምረው ሳይሆን ተግባራዊ የሆነ ትምህርትም ለአንድ ዓመት ሄደው የሚሰሩበት ከማህበረሰቡ ጋር የሚተዋወቁበት ነው። ሁለተኛ የአስተማሪዎች እጥረትም ስላለ ልጆችን ወደ አስተማሪነት ለአንድ አመት ቢሆንም ለማስገባት ነው " ብለዋል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
" ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ስልክ ይዘው እንዳይሄዱ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)
ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ስልክ የሚባል ነገር ይዘው እንዳይገቡ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ትምህርት ሚኒስቴር አሳወቀ።
የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) በሚመሩት የትምህርት ዘርፍ ላይ ስለአፈጻጻምና ስለታቀዱ እቅዶች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በሰጡት ማብራሪያም በሚቀጥለው ሳምንት ከትምህርት ቢሮዎች ጋር ውይይት እንደሚካሄድ ጠቁመዋል።
በዚህም ወቅት ተማሪዎች ስልክ ትምህርት ቤት ይዘው እንዳይገቡ ለማድረግ ስለሚደረገው እንቅስቃሴ እንደሚመከር ገልጸዋል።
" የጋራ ስምምነት ላይ ከደረስን ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ተማሪዎች ትምህርት ቤት ገብተው ትምህርት መከታተል ነው እንጂ ከስልክ ጋር የሚጫወቱበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ይደረጋል " ብለዋል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
📢 ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች አስፈላጊ ምክር!
ውድ ተማሪዎች 📚✍️፣
የዲጂታል መታወቂያ (ፈይዳ) በብዙ ቦታዎች (ዩኒቨርሲቲዎች፣ ሥራ ቦታዎች፣ የመንግስት አገልግሎቶች፣ ወዘተ...) ግዴታ እየሆነ መጥቷል፣ ስለዚህ ከአሁኑ የፋይዳ መታወቂያ እጃችሁ በማስገባት ተጠቃሚ ሁኑ።
👉 በአቅራቢያችሁ በሚገኙ የፈይዳ መታወቂያ አገልግሎት መስጫ ተቋማት በመሄድ ሂደቱን አሁኑኑ ይጀምሩ።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
ፈተናው በዩኒቨርሲቲዎች ሳይሆን በትምህርት ቤቶች እንዲሰጥ ተጠየቀ፡
የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት "በኢትዮጵያ መልቀቂያ የብሔራዊ ፈተና ውጤት የቅርብ ጊዜ ተለዋዋጭነት ግምገማ" በሚል ርዕስ ለአንድ ዓመት የቆየ ጥናት ውጤት ይፋ አድርጓል።
ኢንስቲትዩቱ ካቀረባቸው የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦች መካከል፣ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች እየተሰጠ የሚገኘው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ይሰጥ የሚለው ይገኝበታል፡፡
በኢንስቲትዩቱ የማኅበራዊ ልማትና አካታችነት ማዕከል ኃላፊና ከፍተኛ ተመራማሪ ደሳለኝ አንጭሶ (ዶ/ር)፥ የተማሪዎች ውጤት እንዲቀንስ ካደረጉ ቁልፍ ምክንያቶች መካከል የፈተና አሰጣጥ ስርዓቱ መቀየር በተለይ ከከተሞች ራቅ ካሉ አካባቢዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚመጡ ተማሪዎች ላይ የፈጠረው የስነ-ልቦና ችግር ተጠቃሽ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተፈጠረው የስነ-ልቦና ችግር ምክንያት ጥሩ ውጤት ማምጣት የነበረባቸው ተማሪዎች ውጤት ሳያመጡ መቅረታቸው ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል፡፡
"ተማሪዎች የባዮሜትሪክ መረጃዎች እንዲሞሉ በማድረግ እንዲሁም በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የደኅንነት ካሜራዎችን በመግጠም የቁጥጥር ስራ በመስራት፣ ተማሪዎች ከሚኖሩበት አካባቢ ሳይርቁ ፈተናውን እንዲፈተኑ ትምህርት ሚኒስቴር የረዥም ጊዜ ዕቅድ ይዞ እንዲሠራ" ምክረ ሐሳብ መቅረቡን ገልፀዋል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
608 ሺህ ❗️
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ600 ሺህ በላይ ተማሪዎች ተመዝግበዋል፡፡ - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
ለዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተማሪዎች ምዝገባ ከታህሳስ 6 እስከ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ.ም መከናወኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) አስታውሰዋል፡፡
በዚህም ከ608 ሺህ በላይ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች መመዝገባቸውን ገልፀዋል።
ሀገር አቀፍ ፈተናው በወረቀት እና በበይነ መረብ የሚሰጥ ሲሆን፤ ክልሎች በኦንላይን እና በወረቀት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን መረጃ እስከ የካቲት 25/2017 ዓ.ም ድረስ ለይተው እንዲያሳውቁ ይጠበቃል፡፡
የፈተና ዝግጅቱ ከኢኮኖሚክስ በስተቀር ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ የትምህርት አይነቶችን ያካተተ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ኢኮኖሚክስ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የገባ በመሆኑ ለዚህ ዓመት ከ12ኛ ክፍል ብቻ እየተዘጋጀ መሆኑን አንስተዋል። #ENA
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️በኦሮሚያ ክልል በ2017 ዓ.ም ከ212 ሺህ በላይ ተማሪዎች ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ይወስዳሉ፡፡ - የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ
በኦሮሚያ ክልል በ2017 ዓ.ም ከ212 ሺህ በላይ ተማሪዎች ሀገር አቀፍ ፈተና የሚወስዱ ሲሆን፤ 59 በመቶ የሚሆኑት የተፈጥሮ ሳይንስ ቀሪዎቹ ደግሞ የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡
ሀገር አቀፍ ፈተና በወረቀት እና በኦንላይን ይሰጣል ያሉት ኃላፊው፤ ከ50 ሺህ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን የሚወስዱበት ሁኔታ እየተመቻቸ ነው ብለዋል፡፡ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን የሚወስዱባቸው ማዕከላት እየተለዩ እንደሆነ ጠቁመዋል። #FMC
💳 የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ይዘት ይዘጋጃል፡፡
የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ - 10ኛ በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ - 12ኛ ደግሞ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው። ነገር ግን በ2015 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በናሙናነት በተመረጡ ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ ላይ የተሳተፉ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው፡፡ በአማራ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን መፈተን ሲገባቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የሚፈተኑ አሉ፡፡ በመሆኑም የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከላይ የተገለጹትን ሶስቱንም ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ሁሉንም የዘመኑን ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል።
ስለሆነም የፈተና ዝግጅቱ፡-
✅ ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣
✅ ከ10ኛ ክፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
✅ ከ11ኛ ከፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
✅ ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል።
ከላይ የተዘረዘረው የዝግጅት ሂደት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ላይ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ ይሆናል።
በአጠቃላይ ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ -12ኛ ክፍል በየተማሩበት የሥርዓተ ትምህርት ይዘት ላይ መመስረት ፈተናው እንደሚዘጋጅ አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን። ስለሆነም ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ወላጆች፣ መምህራንና መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት!
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+4
‼️ፈተና በበይነ መረብ ኦን ላይን ለመስጠት ዝግጅት
የ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በበይነ መረብ ኦን ላይን ለመስጠት በተዘጋጀ እቅድ ላይ የቢሮ ማኔጅመንት አባላት ውይይት አካሄዱ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ማኔጅመንት አባላት በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በከተማ አስተዳደሩ በበይነ መረብ ኦን ላይን በውጤታማነት ለመስጠት በሚያስችል እቅድ ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡
በመድረኩም የ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በበይነ መረብ ኦን ላይን ለመስጠት የተዘጋጀ እቅድ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ በአቶ ሳምሶን መለሰ አማካኝነት ቀርቦ ውይይት ተካሄዳል፡፡
በውይይቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ የ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በከተማ አስተዳደሩ በበይነ መረብ በውጤታማነት ለመስጠት እንዲቻል ከወዲሁ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ለማከናወን እቅድ መዘጋጀቱንና ወደ ስራ መገባቱን የገለጹ ሲሆን ፈተናው ኦን ላይን እንደመሰጠቱ ኮምፒውተሮችና እና መሟላት የሚገባቸውን መሰል ግብዓቶች የመለየት ስራ መጀመሩን አስታውቀዋል። ለፈተናው አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን የማዘጋጀት ተግባራት ከወዲሁ በመጀመር ፈተናው በታቀደለት መርሀ ግብር እንዲሰጥ በትኩረት መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ኃላፊው አክለውም ከባለፈዉ አመት ፈተና አሰጣጥ ብዙ ተምክሮዎች መቀሰማቸዉን በመጥቀስ ለፈተናዉ አሰጣጥ ውጤታማነት ከተለያዩ ጉዳዩ ከሚመለከታቸዉ ተቋማት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
የ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ለመውስድ በከተማ አስተዳደሩ በማህበራዊና በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት መስኮች 50807 ተማሪዎች ተመዝግበዋል፡፡
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️ $10 Per hour
ℹ️ We are offering an exciting opportunity to earn up to $10 per hour by completing simple tasks.
🎉 Requirments
📱Phone/Laptop
🌐 Good Internet access.
🔔We are hiring from around the world
📮Apply through our bot👇
⭐️⭐️⭐️⭐️
✔️ ይመዝገቡ ✔️
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና #በድጋሜ መውሰድ የምትፈልጉ #የግል አመልካቾች የኦንላይን ምዝገባ አድርጉ!
ከዚህ ቀደም በመደበኛ ፕሮግራም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ነጥብ ያላመጣችሁና ፈተናውን በድጋሜ መውሰድ የምትፈልጉ የግል አመልካቾች ምዝገባ ማድረግ ትችላላችሁ፡፡
🔗 https://register.eaes.et/Online ሊንክ ላይ በመግባት Apply Now የሚለውን ይጫኑ፤ የሚመጣላችሁን ቅፅ በጥንቃቄ ይሙሉ፤ አስፈላጊ ሰነዶችን ይጫኑ፤ የምዝገባ ክፍያ ብር 750 ክፍያ በመፈጸም ምዝገባዎትን ያከናውኑ፡፡
🗓 ምዝገባው የሚያበቃው፦ ጥር 20/2017 ዓ.ም
በምዝገባ ሒደቱ ማንኛውም ድጋፍ ቢያስፈልግዎ ከላይ በምስሉ ላይ በተጠቀሱት የስልክ ቁጥሮች በመደወል ድጋፍ ማግኘት ይችላሉ፡፡
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
⭐️⭐️⭐️⭐️
✔️ ይመዝገቡ ✔️
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና #በድጋሜ መውሰድ የምትፈልጉ #የግል አመልካቾች የኦንላይን ምዝገባ አድርጉ!
ከዚህ ቀደም በመደበኛ ፕሮግራም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ነጥብ ያላመጣችሁና ፈተናውን በድጋሜ መውሰድ የምትፈልጉ የግል አመልካቾች ምዝገባ ማድረግ ትችላላችሁ፡፡
🔗 https://register.eaes.et/Online ሊንክ ላይ በመግባት Apply Now የሚለውን ይጫኑ፤ የሚመጣላችሁን ቅፅ በጥንቃቄ ይሙሉ፤ አስፈላጊ ሰነዶችን ይጫኑ፤ የምዝገባ ክፍያ ብር 750 ክፍያ በመፈጸም ምዝገባዎትን ያከናውኑ፡፡
🗓 ምዝገባው የሚያበቃው፦ ጥር 20/2017 ዓ.ም
በምዝገባ ሒደቱ ማንኛውም ድጋፍ ቢያስፈልግዎ ከላይ በምስሉ ላይ በተጠቀሱት የስልክ ቁጥሮች በመደወል ድጋፍ ማግኘት ይችላሉ፡፡
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
⭐️⭐️⭐️⭐️ይመዝገቡ✔️
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና #በድጋሜ መውሰድ የምትፈልጉ #የግል አመልካቾች የኦንላይን ምዝገባ አድርጉ!
ከዚህ ቀደም በመደበኛ ፕሮግራም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ነጥብ ያላመጣችሁና ፈተናውን በድጋሜ መውሰድ የምትፈልጉ የግል አመልካቾች ምዝገባ ማድረግ ትችላላችሁ፡፡
🔗 https://register.eaes.et/Online ሊንክ ላይ በመግባት Apply Now የሚለውን ይጫኑ፤ የሚመጣላችሁን ቅፅ በጥንቃቄ ይሙሉ፤ አስፈላጊ ሰነዶችን ይጫኑ፤ የምዝገባ ክፍያ ብር 750 ክፍያ በመፈጸም ምዝገባዎትን ያከናውኑ፡፡
🗓 ምዝገባው የሚያበቃው፦ ጥር 20/2017 ዓ.ም
በምዝገባ ሒደቱ ማንኛውም ድጋፍ ቢያስፈልግዎ ከላይ በምስሉ ላይ በተጠቀሱት የስልክ ቁጥሮች በመደወል ድጋፍ ማግኘት ይችላሉ፡፡
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
🏵እንኳን ለከተራ በዓል በሰላም ፤ አደረሳችሁ 🏵
🤩 በዓሉ የሰላምና የፍቅር በዓል ይሁንላችሁ 🤩
🇪🇹መልካም የከተራ በዓል🇪🇹
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
