ar
Feedback
Mark Tech Info | Mark Technology Information

Mark Tech Info | Mark Technology Information

الذهاب إلى القناة على Telegram

Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot

إظهار المزيد
6 218
المشتركون
-324 ساعات
-337 أيام
-31730 أيام
أرشيف المشاركات
❗️ዩኒቨርሲቲዎች ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚወስዱ ተፈታኞችን ዛሬ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም መቀበል ጀምረዋል፡፡ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈ
+1
❗️ዩኒቨርሲቲዎች ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚወስዱ ተፈታኞችን ዛሬ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም መቀበል ጀምረዋል፡፡ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። በወጣው መርሐግብር መሰረት ሰኞ ሰኔ 23/2017 ዓ.ም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ይጀምራል፡፡ ፈተናውን ለመውሰድ 608 ሺህ ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ 150 ሺህ የሚሆኑት በበይነ መረብ የሚፈተኑ ናቸው። 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗️የ12ኛ ክፍል ፈተናን በበይነ መረብ ለሚወስዱ ተማሪዎች የሙከራ ፈተና ተሰጠ የዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም በሃገር አቀፍ ደረጃ እንደሚ
+1
❗️የ12ኛ ክፍል ፈተናን በበይነ መረብ ለሚወስዱ ተማሪዎች  የሙከራ ፈተና ተሰጠ የዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም በሃገር አቀፍ ደረጃ እንደሚሰጥ ይታወቃል ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፈተናው  በበይነ መረብ እና በተለመደው የወረቀት ፈተና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ በመሆኑም ፈተናቸውን በበይነ መረብ ለሚወስዱ ተማሪዎች የሙከራ ፈተና ሰኔ 17/2017 ዓ.ም እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ይህም ተፈታኞች በበይነ መረብ መፈተንን እንዲለማመዱ እና  ምንም አይነት ችግር ሳይገጥማቸው ፈተናቸውን በተሳካ ሁኔታ ለመውሰድ የሚያችላቸውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ዩኒቨርሲቲው በበይነ መረብ የመፈተን አቅም ዝግጅት የሚገመገምበት መሆኑ ተገልጿል፡፡ 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

ጦርነቱ አብቅቷል‼️ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤል እና ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸውን ገለጹ። " እስራኤል እና ኢራን አሁን የያዟቸውን የመጨረሻ ተልእኮዎች ካ
+1
ጦርነቱ አብቅቷል‼️ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤል እና ኢራን የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ መስማማታቸውን ገለጹ። " እስራኤል እና ኢራን አሁን የያዟቸውን የመጨረሻ ተልእኮዎች ካጠናቀቁ በኃላ በ6 ሰዓታት ውስጥ  ለ12 ሰዓታት የሚቆይ የተሟላ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ ሙሉ በሙሉ ተስማምተዋል " ብለዋል። በዚህም ጦርነቱ እንደተጠናቀቀ እንደሚቆጠር ትራምፕ ገልጸዋል። " ኢራን በስምምነቱ መሰረት ስምምነቱን ተኩስ አቁሙን በይፋ ትጀምራለች " ያሉት ትራምፕ " እስራኤል በ12ኛው ሰዓት ትከተላለች " ብለዋል። በ24ኛው ሰዓት " የ12 ቀናት ጦርነቱ " ማብቃቱን ለዓለም ህዝብ በይፋ እንደሚበሰር ፤ ሁለቱም ወገኖች ለስምምነቱ መከበር ተከባብረው እንደሚሰሩ ገልጸዋል። " ይህ ጦርነት ለዓመታት ሊቆይ መላው መካከለኛውን ምስራቅ ሊያጠፋ ይችል ነበር " ያሉት ዶናልድ ትራምፕ " ግን በፍጹም አልሆነም አይሆንም " ብለዋል። " አምላክ እስራኤልን ይባርክ፣ አምላክ ኢራንን ይባርክ፣ አምላክ መካከለኛውን ምስራቅን ይባርክ፣  አምላክ አሜሪካን ይባርክ፣ እንዲሁም አምላክ መላው ዓለምን ይባርክ " ሲሉ ገልጸዋል። 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

🔓 PRIVATE CHANNEL now OPEN +$154.382 per day raised by Jack subs⚡️ 👉 https://t.me/+qRKP9TmigCwxM2Iy Don’t miss signals and
🔓 PRIVATE CHANNEL now OPEN +$154.382 per day raised by Jack subs⚡️ 👉 https://t.me/+qRKP9TmigCwxM2Iy Don’t miss signals and start make money 🔥

‼️ማሳሰቢያ ከትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና የመጀመሪያ ቀን የኦንላይን ፈተና ውሎን ተከትሎ ከትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠ ማሳሰቢያ፦ ✅ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናውን ሲጨርስ Finish and Submi
‼️ማሳሰቢያ ከትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና የመጀመሪያ ቀን የኦንላይን ፈተና ውሎን ተከትሎ ከትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠ ማሳሰቢያ፦ ✅ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናውን ሲጨርስ Finish and Submit ሳያደርግ መውጣት የለበትም። ተፈታኙ ይህንን ማድረጉንም በፈተና ክፍሉ የተመደበ ባለሙያ ማረጋገጫ ሳይሰጠው እና ተፈታኙም ፈተናውን መጨረሱን በፊርማው ሳያረጋግጥ ከመፈተኛ ክፍል መውጣት አይኖርበትም። ✅ በተለያየ ምክንያት ሲስተም ዘጋብን በማለት ፈተና ክፍል ውስጥ የሚቀመጡ ተፈታኞችን በተለያዩ መንገዶች የማጣራት ሥራ በመስራት አስፈለጊውን የእርምት ወይም አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰድ ይኖርበታል። (ሚኒስቴሩ ለዩኒቨርሲቲዎች ያስተላለፈው ሙሉ መረጃ ከላይ ተያይዟል።) 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗️" በተማሪው አሟሟት ዙሪያ ተገቢውን ማጣራት እያደረግኩ ነዉ " - የአዲሎ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ " ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸዉ የተባሉ አካላት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ ነው ! " በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፤ ከንባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወረዳ ኡዳሜ ቀበሌ አንድ ወጣት የፍጥኝ ታስሮና በገመድ ታንቆ በዛፍ ላይ ተንጠልጥሎ መሞቱን ለፖሊስ መረጃ እንደደረሰዉና ወደ ስፍራው በማቅናት አስክሬኑ ዉርዶ ለምርመራ ወደ ወራቤ መላኩን የወረዳዉ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፆል። የወረዳዉ ፖሊስ ከወጣቱ አሟሟት ጋር በተያያዘ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸዉ ያላቸዉን አካላት በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ገልጿል። " በተለያዩ ማህበራዊ የትስስር ገፆች ወጣቱ በዚህ መንገድና በዚህ ቦታ ተገደለ እየተባለ የሚሰራጩ መረጃዎች የፖሊስን መግለጫና የምርመራ ዉጤት ያካተቱ አይደሉም " ብሏል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከወጣቱ ሞት ጋር አብሮ ስሙ እየተነሳ ወዳለዉ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ደዉሎ የዩኒቨርሲቲዉን ሕዝብ ግንኙ አቶ ፈቃዱ ማሞን አነጋግሯል። በተደረገው ማጣራት ወጣቱ ምንተስኖት ሰንበቱ እንደሚባልና በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ 1ኛ ዓመት የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪ እንደነበር ገልፀዉ " ለእረፍት ወደ ቤተሰቦቹ ሄዶ በነበረበት ይህ ጉዳይ መከሰቱን ሰምተን የሃዘን መግለጫ አዉጥተናል " ብለዋል። ከዚህ ውጭ ግን በተሳሳተ መንገድ የሚሰራጩ አንዳንድ መረጃዎች ስለመኖራቸዉ ያነሱት አቶ ፈቃዱ " ይህ ተገቢነት የለዉም " ሲሉ ተናግረዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ተጨማሪ መረጃዎችን እየተከታተለ የሚያደርስ ይሆናል። 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

‼️ተማሪው በገመድ ተሰቅሎ ሕይወቱ ጠፍቶ ተገኘ በዛሬው እለት የወልቂጤ ዩኒቨርስቲ የ2ኛ አመት ተማሪ የሆነ ወጣት ምንተስኖት ሰንበቱ በከምባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወረዳ በገመድ ተሰቅሎ ሕይወቱ ጠፍቶ ተ
‼️ተማሪው በገመድ ተሰቅሎ ሕይወቱ ጠፍቶ ተገኘ በዛሬው እለት የወልቂጤ ዩኒቨርስቲ የ2ኛ አመት ተማሪ የሆነ ወጣት ምንተስኖት ሰንበቱ በከምባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወረዳ በገመድ ተሰቅሎ ሕይወቱ ጠፍቶ ተገኝቷል። አስክሬኑ ለምርመራ ወደ ወራቤ ሆስፒታል ተልኳል። 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗️የጸጥታ ችግር አጋጥሞኛል ብሎ ያመለከተ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የለም ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ የ2017 አገር አቀፍ የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተናን ለመስጠት 'የጸጥታ ችግር አጋጥሞኛል' ብሎ
❗️የጸጥታ ችግር አጋጥሞኛል ብሎ ያመለከተ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የለም ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ የ2017 አገር አቀፍ የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተናን ለመስጠት 'የጸጥታ ችግር አጋጥሞኛል' ብሎ ያመለከተ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም እንደሌለ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ኤባ ሚጀና "እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ 'በፀጥታ ችግር ምክንያት ማስፈተን አልችልም' ብሎ ያመለከተ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የለም" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡ በ87ቱም ማዕከላት የፈተናው አስተባባሪዎች መድረሳቸውን አንስተው፤ መምህራኑ በትናንትናው ዕለት ወደማዕከላቱ መግባታቸውንም ገልጸዋል፡፡ በ238 የትምህርት መርሃ ግብሮች ለ190 ሺሕ 787 ቅድመ መደበኛ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች ፈተናውን በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ 102 ሺሕ 360 ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ፣ 88 ሺሕ 422 ተማሪዎች ደግሞ ዳግም ለፈተናው እንደሚቀመጡ መሪ ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡ ዘንድሮ ከ608 ሺሕ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ የተመዘገቡ ሲሆን፤ ፈተናው በ51 ዩኒቨርስቲዎች በተዘጋጁ 87 የፈተና ማዕከላት ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 10 /2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወሳል፡፡ 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗️የመውጫ ፈተና ላይ የፋይዳ መታወቂያ የሌላቸው ተማሪዎች ያላቸው አማራጮች 👇 ከብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ጽ/ቤት የተሰጠ አጭር ማብራሪያ፤ ተፈታኞች የትኞቹን የፋይዳ መታወቂያ አማራጮች መያዝ ይ
❗️የመውጫ ፈተና ላይ የፋይዳ መታወቂያ የሌላቸው ተማሪዎች ያላቸው አማራጮች 👇 ከብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ጽ/ቤት የተሰጠ አጭር ማብራሪያ፤ ተፈታኞች የትኞቹን የፋይዳ መታወቂያ አማራጮች መያዝ ይችላሉ ? ✅ በኢትዮ ቴሌኮም ወይም የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት አማካኝነት የታተሙ የፋይዳ መታወቂያዎችን፤ ✅ ከ "Fayda ID" ሞባይል መተግበሪያ ፣ ከቴሌብር ሱፐር አፕ፣ እንዲሁም ሲቢኢ ብር ሞባይል መተግበሪያ ላይ #QR_ኮድ በማውረድ እና በወረቀት በማሳተም መያዝ ይችላሉ። የማይፈቀደው ወይም የማይቻለው የቱ ነው ? ❌ ዲጂታል ኮፒ (በስልክ ይዞ መገኘት) አይቻልም። የፋይዳ ቁጥር ከጠፋብዎ ወይም ካልደረስዎ *9779# ላይ በመደወል በድጋሚ ማስላክ ይችላሉ። 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗️EXIT-EXAM ከሰኔ 2 እስከ 10/ 2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል። የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) " የ2017 የዩኒ
❗️EXIT-EXAM ከሰኔ 2 እስከ 10/ 2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል። የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) " የ2017 የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 10 /2017 ዓ.ም. በ51 ዩኒቨርስቲዎች በተዘጋጁ 87 የፈተና ማዕከላት ይሰጣል " ብለዋል። ፈተናውን በ238 የትምህርት መርሃ ግብሮች ለ190 ሺ 787 ቅድመ መደበኛ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በበይነ መረብ ለመስጠት  አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ ለፈተናው 102 ሺ 360 ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ፤ 88 ሺ 422 ተማሪዎች ደግሞ ዳግም የሚፈተኑ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ተማሪዎች ወደ ፈተና ማዕከላት ሲመጡ አገር አቀፍ ፋይዳ /ብሄራዊ መታወቂያ መያዝ እንደሚጠበቅባቸውም ኃላፊው አስገንዝበዋል፡፡ በፈተና ወቅት ፦ - ተንቀሳቃሽ ስልክ ፣ - ሜሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት ፣ - የራስ ያልሆነ መታወቂያ፣ - ያልተፈቀዱ ሂሳብ ማሽኖች፣ - አጫጭር ማስታወሻዎች፣ - የተጭበረበሩ ሰነዶች - ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት ክልክል መሆኑን አስገንዝበዋል። ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ ፦ ° አደንዛዥ ዕጽ ተጠቅሞ መምጣት፣ ° ከፈተና አስፈጻሚዎች ጋር አሉታዊ ተጽእኖ ያላቸው ውዝግቦችን መፍጠር ፣ ° ያለመታወቂያ ካርድ ወደ ፈተና ማእከል መሄድ ፣ ° ያለፈቃድ ፈተና ማዕከል መገኘት ° ለሌላ ሰው መፈተን ፍጹም የተከለከሉ ዲሲፒሊን ጥሰቶች መሆናቸውን አሳስበዋል። 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗️በኦንላይን ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እየተከናወኑ በሚገኙ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ። ውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ስትራቴጂክ ካውንስል
+3
❗️በኦንላይን ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እየተከናወኑ በሚገኙ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ። ውይይቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ስትራቴጂክ ካውንስል አባላት ፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮች እንዲሁም የቢሮው የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልማት ዳይሬክቶሬት ባለሙያዎች በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በመርሀ ግብሩ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እየተሰሩ የሚገኙ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እና በቀጣይ መከናወን በሚገባቸው ተግባራት ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ በበይነ መረብ የሚሰጠው የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ስኬታማ እንዲሆን የሙከራ ፈተና ከመስጠት ጀምሮ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ኃላፊው አያይዘውም ፈተናው በሚፈለገው ደረጃ ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት እና የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ መዋቅሮችን ጨምሮ የኢትዮ ቴሌኮም ባለሙያዎች የፈተና ጣቢያዎቹ ምን ያህል ዝግጁ እንደሆኑ በድጋፍና ክትትል ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመው ቢሮው በየጊዜው ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ የሚያስቀምጥ መሆኑን አመላክተዋል። 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗️የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተናን የሚሰጡ ከ28 ሺህ በላይ #ፈታኞች መመልመላቸው ተገለፀ፡፡ ፈታኞቹ በወረቀት እና በበይነ መረብ የሚሰጠውን ፈተና በብቃት ለመስጠት ዝግጅ
+1
❗️የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተናን የሚሰጡ ከ28 ሺህ በላይ #ፈታኞች መመልመላቸው ተገለፀ፡፡ ፈታኞቹ በወረቀት እና በበይነ መረብ የሚሰጠውን ፈተና በብቃት ለመስጠት ዝግጅት ያደረጉ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለኢቲቪ ተናግረዋል፡፡ ዘንድሮ መልቀቂያ ፈተናውን በበይነመረብ የሚፈተኑ 150 ሺህ ተማሪዎች አስፈላጊውን ልምምድ እያደረጉ እንደሆነ ጠቅሰዋል። በፈተናው ወቅት የኢንተርኔት እና የመብራት መቆራረጥ እንዲሁም ሌሎች ችግሮች እንዳይፈጠሩ፤ ከ10 ተቋማት የተወጣጣ ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ እየሠራ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ገልፀዋል። 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በበይነ መረብ ለሚፈተኑ ተፈታኞች የቴክኒካል ድጋፍ የሚሰጥ ቡድን ተቋቁሟል። በበይነ መረብ ፈተና ለመውሰድ እየተዘጋጁ የሚገኙ የ12ኛ ክፍል
❗በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በበይነ መረብ ለሚፈተኑ ተፈታኞች የቴክኒካል ድጋፍ የሚሰጥ ቡድን ተቋቁሟል። በበይነ መረብ ፈተና ለመውሰድ እየተዘጋጁ የሚገኙ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ማንኛውንም ድጋፍ በመጀመሪያ በትምህርት ቤታቸው ቀጥሎም በመፈተኛ ማዕከላት ካሉ የትምህርት አመራር እና ቴክኒክ ድጋፍ ሰጪዎች ማግኘት እንደሚችሉ ይታወቃል። ተጨማሪ ድጋፍ ለተፈታኝ ተማሪዎቹ የሚሰጥ ቴክኒካል ቡድን በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተቋቁሞ ወደ ሥራ ገብቷል። ዘጠኝ አባላት በውስጡ የያዘው ቴክኒካል ቡድኑ፤ በክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ተከፋፍሎ የተደራጀ ነው። (የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ ቡድኑን ድጋፍ ለማግኘት ከላይ የተያያዘውን ምስል ይመልከቱ።) 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗️ግንቦት 20 መደበኛ የትምህርት ቀን እንደሚሆን ተገለጸ። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ነገ ግንቦት 20/2017 ዓ.ም መደበኛ የትምህርት ቀን እንደሆነ ገልጿል። ሁሉም ትምህርት ቤቶች ዝግ እ
❗️ግንቦት 20 መደበኛ የትምህርት ቀን እንደሚሆን ተገለጸ። የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ነገ ግንቦት 20/2017 ዓ.ም መደበኛ የትምህርት ቀን እንደሆነ ገልጿል። ሁሉም ትምህርት ቤቶች ዝግ እንዳይሆኑና መደበኛ የትምህርት እንቅስቃሴ በተለመደው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት መቀጠል እንዳለባቸው ቢሮው በአስተዳደሩ ስር ለሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች ባስተላለፈው መልዕክት አሳስቧል። 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗️የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል። መንግሥት ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ የ12ኛ ክፍል ሀገረ አቀፍ ፈተና
+1
❗️የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል። መንግሥት ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ የ12ኛ ክፍል ሀገረ አቀፍ ፈተናን ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲገቡ በማድረግ ፈተናውን ሲሰጥ ቆይቷል። ይህም የፈተና ስርቆትና ኩረጃ እንዲቀንስ ማድረጉን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለኢቢሲ ተናግረዋል። ዘንድሮ ከ608 ሺህ በላይ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ ተመዝግበዋል። ሀገር አቀፍ ፈተናው በወረቀት እና በበይነ መረብ የሚሰጥ ሲሆን፤ ፈተናውን በተሳካ መልኩ ለመስጠት የትምህርት ተቋማት የቁሳቁስ እና ሌሎች ዝግጅቶችን አጠናቀው ተማሪዎችን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። ፈተናውን በብይነ መረብ የሚፈተኑ 150 ሺህ ተማሪዎች በየትምህርት ቤታቸው ልምምድ በማድረግ ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል። የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23/2017 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 8/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

❗️የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ኦንላይን ፈተና ቅድመ ዝግጅት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ የ12ኛ ክፍል ኦንላይን ፈተና መስጫ ጣቢያዎች ላይ ያለውን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች አስመልክቶ ጉብኝ
+3
❗️የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ኦንላይን ፈተና ቅድመ ዝግጅት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ የ12ኛ ክፍል ኦንላይን ፈተና መስጫ ጣቢያዎች ላይ ያለውን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች አስመልክቶ ጉብኝት ተካሄደ፡፡ በጉብኝቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዲናኦል ጫላ እና የቢሮ አማካሪ አቶ ጥላሁን ፈቃዱ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመስጠት እየተደረገ ያለውን ቅድመ ዝግጅትና የተማሪዎችን ልምምድ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በሚገኘው አሳይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና በጉለሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው እቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመገኘት ምልከታ አካሂደዋል፡፡ በምልከታው ተማሪዎች የኦንላይን ፈተና ልምምድ በማካሄድ ላይ መሆናቸዉ የተገለጸ ሲሆን ፤ በቅድመ ዝግጅቱ የተማሪዎች ኦንላይን ፈተና ልምምድ ፤ የመፈተኛ ክፍሎች ፤ የኮምፒውተርና ኢንተርኔት እንዲሁም ጀነሬተሮች ዝግጁነት ላይ የፈተና መስጫ ጣቢያዎቹ ያላቸው ዝግጁነትና የማስፈተን አቅም ላይ ጉብኝት ተደርጓል፡፡ በቀጣይም የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናውን ለመስጠት ያላቸውን ዝግጁነት ላይ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ለፈተናው ውጤታማነት ቢሮው በትኩረት እየሰራ እንደሆነ የቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዲናኦል ጫላ ተናግረዋል፡፡ 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●

Enjoy our content? Advertise on this channel and reach a highly engaged audience! 👉🏻 It's easy with Telega.io. As the leadi
Enjoy our content? Advertise on this channel and reach a highly engaged audience! 👉🏻 It's easy with Telega.io. As the leading platform for native ads and integrations on Telegram, it provides user-friendly and efficient tools for quick and automated ad launches. ⚡️ Place your ad here in three simple steps: 1 Sign up 2 Top up the balance in a convenient way 3 Create your advertising post If your ad aligns with our content, we’ll gladly publish it. Start your promotion journey now!

❗️በ2017 ዓ.ም ለሚሰጠው ሀገር አቀፍ እና ክልል አቀፍ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን መምሪያው አስታወቀ። የወልድያ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ በ2017 ዓ.ም ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና እና ለ6ኛና 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናን በሚመለከት ከአጋርና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል። በውይይቱም ተማሪዎች በሚሰጡ ፈተናዎች ላይ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በየትምህርት ቤቱ የተለያዩ ተግባሮች መከናዎናቸውን የወልድያ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አስራት በሪሁን ተናግረዋል። ኃላፊው አክለውም በተያዘው የበጀት ዓመት 1,253 የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎችን በ16 ትምህርት ቤት፣ 1,235 የስምንተኛ ክፍል ተማሪዎችን በ11ትምህርት ቤት እና 1003 የአስራ ሁለተኛ ክፍል ተማሪዎችን በአራት መደበኛ ትምህርት ቤት እና በሰባት የርቀት የትምህርት ተቋማት ለማስፈተን ዝግጅት መደረጉን ገልፀዋል። ሁሉም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን የሚወስዱ መሆኑ ተገልጿል። ሀገርን ለመገንባትና ትውልድን ለመቅረጽ ትምህርት መሠረታዊ ጉዳይ ነው ያሉት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ንጉስ ዝናቡ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የፈተናን ጥራትና ውጤት ሊመጥን በሚችል መልኩ ፈተናውን መስጠትና ማጠናቀቅ ይገባል ነው ያሉት። ተማሪዎች ያለምንም የድምጽ ብክለትና የፀጥታ ስጋት እንዲፈተኑ ሰላሙን ለማስጠበቅ በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀው ማህበረሰቡ ከፀጥታ መዋቅሩ ጋር በመተባበር የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል። ባለው ቀሪ ጊዜ ለተማሪዎች በቂ ኦረንቴሽን ሊሰጥ ይገባል ያሉት ተሳታፊዎቹ በትምህርት ቤቶች የተጀመረው የስነ-ልቦና ግንባታ ስልጠና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። ከፀጥታ መዋቅሩና ከተሽከርካሪ ጋር በተያያዘ የቅድመ ዝግጅት ስራው ሊጠናከር እንደሚገባ ተሳታፊዎቹ ጠቁመዋል። የ6ኛ ክፍል እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 03 እስከ ሰኔ 08/2017 ዓ.ም እና የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሀምሌ 08/2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ተገልጿል። 🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥 ●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬● 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌 ●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●