cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

ትክክለኛ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ! #Ethiopia #Ethiopianews #Addismereja

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
3 350
المشتركون
+324 ساعات
+187 أيام
+4230 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

#በአዳማ ከተማ ከቤት ፈረሳ ጋር በተያያዘ በተፈጠረ ግጭት ነፍሰ ጡር እናትን  ጨምሮ 7 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ 👉🏼 ቁጥራቸው በዉል ያልታወቁ ሰዎችም ቆስለዋል ተብሏል በኦሮሚያ ክልል በአዳማ ከተማ አሮሬቲ እና ቶርበን ኦቦ በተባሉ ቀበሌዎች ዛሬ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ ላይ የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች በተኮሱት ጥይት አንዲት ነፍሰ ጡርን ጨምሮ 7 ሰዎች እንደተገደሉና ቁጥራቸው ያልታወቁ ሌሎች ሰዎች እንደቆሰሉ ዋዜማ ተመልክቷል። ተቃውሞው የተቀሰቀሰው፣ የከተማዋ አስተዳደር 1 ሺሕ 500 ገደማ መኖሪያ ቤቶችን ሕገወጥ ናቸው በማለት ማፍረስ ሲጀምር መኾኑን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ፣ መሬቶቹን ከአካባቢው አርሶ አደሮች ገዝተው ከ2005 ዓ፤ም ጀምሮ ለከተማዋ አስተዳደር ግብር ሲከፍሉ መቆየታቸው ገልጸዋል። ነዋሪዎቹ ቀደም ሲል ለጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ባቀረቡት አቤቱታ መሠረት፣ ጉዳዩ በይደር እንዲታይ ተወስኖላቸው እንደነበርም ዋዜማ ተረድታለች። ዋዜማ በክስተቱ ዙሪያ የከተማዋን አስተዳደር ለማነጋገር ያደረገችው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም ስትል ዘግባለች። https://t.me/Satenawmedia1
إظهار الكل...
ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

ትክክለኛ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ! #Ethiopia #Ethiopianews #Addismereja

Photo unavailableShow in Telegram
ዶ/ር ፍሰሀ እሸቱ ማስረጃ አለኝ ያሉትን ለሚድያ ሰጥተው እውነታው ቢጣራስ? የፐርፐዝ ብላክ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ፍሰሀ እሸቱ "በመንግሥት አካላት የ200 ሚሊዮን ብር ጉቦ ተጠይቀናል፣ አክራሪዎችን በመደገፍ እና በሙስና...ወዘተ ተከሰናል" በቅርቡ ማለታቸው ይታወሳል። የፐርፐዝ ብላክ አጠራጣሪ ጉዳዮችን (በተለይ በ1.5 ሚልዮን ብር ሜክሲኮ ላይ አፓርትመንት ገንብተን እንሰጣለን ያሉትን) አንስቼ መጀመርያው አካባቢ ለህዝብ አቅርቤ ነበር፣ ብዙ ሰው መረጃውን አይቶ ራሱን ቢያተርፍም ገንዘቡን የከፈለም በርካታ ህዝብ አለ። ታድያ በዚህ ሁሉ መሀል ዶ/ር ፍሰሀ "ከአመታት በፊት በዩኒቲ ዩኒቨርስቲ ጉዳይ የተጫወቱትን ጨዋታ መልሰው አጫወቱት" የሚሉ በርካቶች ናቸው። ታድያ ያኔም፣ አሁንም ተጠያቂ ያረጉትን መንግስትን ነው። ግን እውነታው እሱ ነው? በመንግሥት አካላት የ200 ሚሊዮን ብር ጉቦ ተጠይቀናል ያሉበትን ሰነድ በይፋ ለሚድያዎች አጋርተው፣ እኛም ተሳትፈንበት እውነታው ተጣርቶ ቢወጣስ? ፅንፈኞችን በመደገፍ፣ በሀይማኖት፣ በብሄር አክራሪነትና የሙስና ክሶች ሲቀርብባቸዉ እንደነበርም አንስተዋል። የእነዚህን ክሶች ዝርዝር ቢያስረዱና ህዝብ ቢያውቀስ? ክስ እንደነበረባቸው እኛም እንድናጣራው ቢተባበሩስ? ማስረጃ እንዳላቸው በመግለፅ ወረቀት ሲያወዛውዙ ነበር፣ ለማንም ግን አላሳዩትም። ይህ በራሱ ጥርጣሬ አጭሯል። ፈቃዳቸው ከሆነ ምላሽ እንጠብቃለን። https://t.me/Satenawmedia1
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
#77ሚልዮንብር ከሰሞኑ የቀድሞ የናይጄርያ ተጫዋቾች እና ፋሽን ሞዴሎች "ሸነን አፍሪካ" በሚል ፕሮግራም ለሶስት ቀናት ኢትዮጵያ ተገኝተው ላደረጉት እንቅስቃሴ (የህዳሴ ግድብ ጉብኝት፣ ኳስ ጨዋታ፣ ኮንፈረንስ መካፈል...ወዘተ) በድምሩ ከመንግስት የወጣው ወጪ 77 ሚልዮን ብር ገደማ ነበር፣ አንዳንድ ወጪዎች በመንግስት ድርጅቶች በአገልግሎት መልክ ባይሸፈኑ ኖሮ ወጪው 110 ሚልዮን ተገምቷል። አንዳንድ ሚድያዎች ሸነን አፍሪካን አህጉር አቀፍ ፕሮግራም እንደሆነ ለማመልከት "በኢትዮጵያ ለመጀመርያ ግዜ" ቢሉም ፕሮግራሙ መቼም፣ የትም ሌላ ሀገር ከዚህ በፊት ተካሂዶ አያውቅም። የፕሮግራሙ አዘጋጅ የሸነን ኮስሜቲክስ ባለቤት ዮርዳኖስ ሙሴ ናት። Via:EliasMeseret https://t.me/Satenawmedia1
إظهار الكل...
👍 8🤔 1
Photo unavailableShow in Telegram
ይቺው ናት ኢትዮጵያ ይህችው ናት አለምህ ብቻዋን የተኛች ከአለም ተደብቃ አኪርዋ ቀዝቅዝዞ ያንቀላፋች ውቢት ያንተው የክት እቃ ልቡዋን አታውልቃት አትጨቅጭቃት በቃ አብረህ አንቀላፋ ወይ አብረሀት ንቃ ነፍስ ይማር ደራሲ፣ ገጣሚ እና ጋዜጠኛ ነብይ መኮንን Via:EliasMeseret https://t.me/Satenawmedia1
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
#በአዲስ አበባ ከተማ ዳቦ ከግራም በታች ሲሸጡ የተገኙ 260 ዳቦ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ‼️ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ለህብረተሰቡ ተደራሽ የሚሆነው ዳቦ በሶስት አይነት መንገድ እየቀረበ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታውቋል። ለህብረተሰቡ የሚቀርበው ዳቦ  ከ1ሺ በላይ በሚሆኑ በሸገር ዳቦ ማከፋፈያ ፣17 በሚሆኑ በመንግስት የግል ባለሀብቶች ጥምረት የሚቀርቡ እና 1700 በሚሆኑ የግል ዳቦ ቤቶች አማካይነት ለነዋሪዎች እንደሚደርስ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ተናግረዋል። በእነዚህ ዳቦ ቤቶች ላይ የሚቀርቡ ዳቦዎች በሸገር ዳቦ 70 ግራሙ 5ብር፣ የመንግስት የግል ባለሀብቶች ጥምረት የሚዘጋጀው በ6 ብር የሚቀርቡ ናቸው። እንዲሁም በግል ዳቦ መጋገሪያ ቤቶች የሚዘጋጁት ከ7 ብር ጀምሮ የሚሸጡ ናቸው። ለህብረተሰቡ የሚቀርቡት ዳቦዎች ዝቅተኛው የግራም መጠናቸው  70 ግራም እንደሆነ እና ከተቀመጠው ግራም በታች መጋገርም ሆነ መሸጥ በየትኛውም መንገድ የሚቀርቡ ዳቦዎች ላይ የተከለከለ ነው ብለዋል። ለህብረተሰቡ የሚቀርቡት ዳቦዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግ እና ከግራም በታች ሲጋግሩ የተገኙት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ገልፀዋል። በዚህም በዘንድሮው 2016 በጀት አመት ብቻ ከ260 በላይ ከግራም በታች ሲጋግሩ የተገኙ ዳቦ ቤቶች ላይ  እርምጃ ተወስዶባቸዋል። እንዲሁም ዳቦ መሸጫ ሱቆች የዋጋ ዝርዝር ማሳወቂ መለጠፍ ግዴታ እንዳለባቸው አቶ ሰውነት አየለ ጨምረው ተናግረዋል። #ብስራትሬዲዮ 👉ትኩስ ዜናዎችን ማግኘት ከፈለጉ ቻናላችንን join አድርጉ https://t.me/Satenawmedia1
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
"ጥላቻ፣ ጦርነት፣ ጠብ፣ ክርክር፣ ሞኝ መሆኑን፡ እያወቅን እዚያ ላይ እንንከባለላለን። የሰው ልጅ ህልውናውን ለመጠበቅ ሰላምን መምረጥና መከተል ይኖርበታል። የሰላምን እጦት ያመጣነው ራሳችን ነን። ማንም አምጥቶ አልጫነብንም።ሰላም ከሌለ መንፈሳዊም ሆነ ዓለማዊ ተቋማት ምንም መሰራት እንደማይችሉ አውቀን ለሰላም በአንድነት መቆምና ሰላምን መከተል ይኖርብናል። ለዚህም ሁላችንም ከቀደመው እየተማርን መጪውን ሰላማዊ ለማድረግ መጣር ይኖርብናል። የሔድንበት መንገድ ጎድቶናል።ስለሆነም ወደ ሰላም፡ እንመለስ ብለን መወሰን አለብን።ለዚህም ሁላችንም ወደ አእምሮችን ተመልሰን ሰላምን እንከተላት።" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወክጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት *** "የሃይማኖት ተቋሞቻችን ለዘላቂ ሰላማችን"በሚል ርእስ በሸራተን አዲስ ዛሬ በተካሔደው መድረክ ላይ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰደ። #አዩ 👉ትኩስ ዜናዎችን ማግኘት ከፈለጉ ቻናላችንን join አድርጉ https://t.me/Satenawmedia1
إظهار الكل...
3🥰 1
Photo unavailableShow in Telegram
ከመጭው መስከረም ጀምሮ ከዚህ በፊት የተሰጠው የሆቴሎች የኮከብ ደረጃ ስራ ላይ አይውልም ተብሏል። የሆቴሎች የኮኮብ ደረጃ ምደባ በአዲስ መልክ ሊሰራ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በዳግም ደረጃ ምደባ ዙሪያ ከሆቴል ባለንብረቶችና ስራ አስፈጻሚዎች ፣ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ ምክክር አድርጓል። የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የደረጃ ምደባ ደንብ ሆቴሎች በየሶስት አመቱ በዳግም የደረጃ ምደባ ሂደት ማለፍ እንዳለባቸው ይደነግጋል፡፡ በዚህም መሰረት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በአዲስ አበባ ከተማ እና በክልሎች የሚገኙ ሆቴሎችን የደረጃ ምዘና ለማድረግ ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል። ሆቴሎች ከዚህ ቀደም የተሰጣቸው የኮከብ ደረጃ በህጉ መሰረት የአገልግሎት ጊዜው ያበቃ በመሆኑ የኮከብ ደረጃው እንደሚሰረዝ የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ አሳውቀዋል። ይህ ዳግም ምደባ በዋናነት ሆቴሎች የሚሰጡትን አገልግሎት ማሻሻል እና የሀገሪቱን የቱሪዝም አገልግሎት ተወዳዳሪነት ማሳደግ ላይ ትኩሩቱን ያደረገ መሆኑንም ኢዜአ በዘገባው አመልክቷል:: ቤተሰብ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ https://t.me/Satenawmedia1
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
#በሕንድ ሃይማኖታዊ ፌስቲቫል ላይ ከ110 በላይ ሰዎች ተረጋግጠው ሞቱ! በሰሜናዊ ሕንድ በሃይማኖታዊ ፌስቲቫል ላይ ቢያንስ 116 ሰዎች ተረጋግጠው መሞታቸውን ፖሊስ አስታወቀ።አደጋው ያጋጠመው አትራ ፕራዴሽ ግዛት ሳትሳንግ በተባለ የሂንዱ እምነት ተከታዮች ሃይማኖታዊ ፌስቲቫል ላይ መሆኑን የፖሊስ ኃላፊ ሻላብህ ማቱር ተናግረዋል።ከሟቾቹ መካከል ሴቶች እና ሕጻናት እንደሚገኙበት ተገልጿል። እስካሁን ድረስ የመረጋገጥ አደጋው እንዴት ሊከሰት እንደቻለ ግልጽ ባይሆንም የዓይን እማኞች ፌስቲቫሉ የተካሄደበት ስፍራ መውጫ በጣም ጠባብ መሆኑን እና አቧራማ አውሎ ንፋስ ግራ መጋባት እና ድንጋጤ ፈጥሮ ሰዎች መሯሯጥ መጀመራቸውን ተናግረዋል።ከአንደጋው የተረፈ አንድ ግልሰብ ለቢቢሲ ሲናገር፤ “ሁሉም ነገር በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ነበር። ድንገት ጩኅት ሰማሁ። መሯሯጥ እና መረጋገጥ ተፈጠረ” ብሏል። ሌላ የፌስቲቫሉ ተሳታፊ ደግሞ የነበረውን ሁኔታ ስትናገር፤ “ስነ-ስርዓቱ እንዳበቃ ሰዎች በፍጥነት ለመውጣት ሲሞክሩ መገፈታተር እና መረጋገጥ ተፈጠረ። በጣም ብዙ ሰዎች ቱቦ ውስጥ ወድቀው ሕይወታቸው አልፏል” ስትል ተናግራለች።እስካሁን የሟቾች ቁጥር 116 ነው የተባለ ቢሆንም በአደጋው የሞቱ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል የአትራ ፕራዴሽ ግዛት የፖሊስ ቃል አቀባይ ለቢቢሲ ዘጋቢ ተናግረዋል።
ቤተሰብ
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው ይከታተሉ https://t.me/Satenawmedia1
إظهار الكل...
ራያ‼️ በ #ራያ #አላማጣ ከተማ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ላይ ሰፍረው የነበሩት የትግራይ ታጣቂዎች ትናንት ጀምረው አካባቢው ለቀው እየወጡ መሆኑን የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገልፀዋል። የትግራይ ታጣቂዎች ከሁለት ወር በፊት ወደ ራያ አላማጣ ወረዳ በመግባት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ሰፍረው እንደነበር ይታወሳል። በዚህ የተነሳ ህዝቡ ታጣቂዎቹ በደል እያደረሱብን ስለሆነ እንዲወጡ በሰላማዊ ሰልፍ ሲጠይቅ እንደነበር ይታወቃል። 👉ትኩስ ዜናዎችን ማግኘት ከፈለጉ ቻናላችንን join አድርጉ https://t.me/Satenawmedia1
إظهار الكل...
ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

ትክክለኛ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ! #Ethiopia #Ethiopianews #Addismereja

Photo unavailableShow in Telegram
#Update መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር ተፈቱ። የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ  መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር መለቀቃቸውን የማሕበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል። ዋና ሥራ አስኪያጁ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ነበር ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ለእስር የተዳረጉት። ከሁለት ወራት በኋላ ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016  ዓ.ም  ከእስር  መለቀቃቸውን  ከቤተሰቦቻቸው ማረጋገጥ ተችሏል https://t.me/Satenawmedia1
إظهار الكل...
🙏 4🔥 3
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.