ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር
"ወደ ደግነት በጎ አድራጎ ማህበር እንኳን በደህና መጡ" የድግነት ዋናው አላማ ለተቸገሩ ያቅማችንን ማድረግ እና እርስ በርሳችን መጠያየቅ መረዳዳት ነው ✍️ "ደግነት የአቅም ጉዳይ ሳይሆን የልብ ጉዳይ ነው " ባለን ነገር ሁሉ እንረዳዳ፤እንተዛዘን 👉"ሰው ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው"👈 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ( 1000532242685 ) ናትናኤል ታደለ እና ቴዎድሮስ አበራ
إظهار المزيد16 211
المشتركون
+6824 ساعات
+3797 أيام
+2 03030 أيام
- المشتركون
- التغطية البريدية
- ER - نسبة المشاركة
جاري تحميل البيانات...
معدل نمو المشترك
جاري تحميل البيانات...
Photo unavailableShow in Telegram
የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ?👇👇👇
🎤 ሊቀ መዘምራን . ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ
🎤 ሊቀ መዘምራን ይልማ ሐይሌ
🎤 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
🎤 ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
🎤 ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
📌 የሁሉንም ዘማሪዎች መዝሙር 🔐
🙋♀ ጥያቄ
========
💠• ከመንፈስ ፍሬዎች መካከል ቀዳሚነትን የሚይዘው የትኛው ነው❓
ሀ. ትዕግስት
ለ. እምነት
ሐ. ደስታ
መ. ፍቅር
ሀገር
መሰዋትነት
💁♀ መልሱን ለማግኘት
† እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃን ወከዋክብተ ገዳም አቡነ ኪሮስ: አባ ብሶይ እና አባ ሚሳኤል ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። †
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †🕊 † አቡነ ኪሮስ ጻድቅ † 🕊 † የጻድቁን ስም የሚጠራ አፍ ንዑድ ነው: ክቡር ነው:: በእውነት የቅዱሱን አባት ክብር ለማግኘት መፋጠን ይበጃል:: አቡነ_ኪሮስ የተወለዱት በ፬ [4] ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን ወላጆቻቸው ነገሥታት ናቸው:: ተወልደው ባደጉባት ሃገር ቁስጥንጥንያ ገና በልጅነት ምቾት ሳያሳሳቸው መጻሕፍትንና ትሕርምትን ተምረዋል:: ወንድማቸው [ታላቁ ቴዎዶስዮስ] በነገሠባቸው የመጀመሪያ ዓመታት በቤተ መንግስቱ ዙሪያ ግፍ በዝቶ ነበርና አቡነ ኪሮስ ከኃጢአት ለመራቅና ለጌታ ለመገዛት ከከተማው ጠፍተው: አሕጉር አቋርጠው ወደ ግብፅ [ገዳመ አስቄጥስ] መጡ:: እርሳቸውን ለመፈለግ የተደረገው ሙከራ አልተሳካም:: ይባስ ብሎ የንጉሡ ልጅ ገብረ ክርስቶስ ሙሽርነቱን ጥሎ ወደ ሌላ ሃገር መነነ:: "የቅኖች ትውልድ ይባረካል" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት:: አቡነ ኪሮስ ለሙሽራው ገብረ ክርስቶስ አጎቱ ናቸው:: አቡነ ኪሮስ በገዳም ውስጥ የታላቁ አቡነ በብኑዳ ደቀ መዝሙር ሆነው ለዘመናት ቆይተዋል:: ቅዱስ በብኑዳን አንበሳ በበላው ጊዜ በጣም አዝነው "ለምን ጌታ ሆይ?" በሚል መሬት ላይ ወድቀው አለቀሱ:: "ምክንያቱ ካልተነገረኝ አልነሳም" ብለው ከወደቁበት መሬት ላይ ሳይነሱ ለ40 ዓመታት አልቅሰዋል:: በዚህ ምክንያት ግማሹ አካላቸው አፈር ሆኖ ሣር በቅሎበታል:: ጌታችን ተገልጦ ምክንያቱን ነግሯቸዋል:: አካላቸውንም እንደነበረ መልሶላቸዋል:: አንድ ቀን ጻድቁ ለቅዱስ በብኑዳ ሞት ምክንያት የሆነው መነኮስ ታንቆ መሞቱን ሰምተው በጣም አዘኑ:: ሱባዔ ገብተው: ፍጹም አልቅሰው: ከጌታም አማልደው: የዛን ኃጥእ ነፍስ ከሲዖል አውጥተዋል:: በሌላ ጊዜ ደግሞ ኃጥአን የሞሉበት አንድ ገዳም በግብጽ ነበርና መቅሰፍት ወርዶ ሁሉንም ባንድ ቀን ሲያጠፋቸው አዩ:: ጻድቁ በዚህም ምክንያት ለ፴ [30] ዓመታት አልቅሰው: ሙታኑን አስነስተው: ንስሃ ሰጥተው: ገዳሙን የጻድቃን: ሕይወታቸውንም የፍቅር አድርገውታል:: ጻድቁ እመቤታችንን ከመውደዳቸው የተነሳ በስዕሏ ፊት አብዝተው ይሰግዱና ያለቅሱ ነበር:: እመ አምላክም ተገልጣ ትባርካቸው ነበር:: ከዚህ በሁዋላ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ሒደው ለ፶፯ [57] ዓመታት ማንንም ሳያዩ ተጋደሉ:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ [ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና] በየቀኑ ይጐበኛቸው: ቁጭ ብሎም ያወራቸው ነበር:: በመጨረሻም በዚህች ቀን ጌታ አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን: ድንግል እመቤታችንና ቅዱስ ዳዊትን አስከትሎ ወረደ:: ቅዱስ ዳዊት ቀርቦ እያጫወታቸው: በበገናው እየደረደረላቸው: ከዝማሬው ጣዕም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ጌታችንም ታቅፎ: ስሞ ይዟቸው አረገ:: ሥጋቸውን #አባ_ባውማ ቀበሩት:: የአቡነ ኪሮስ ቁመታቸው ቀጥ ያለ: ጽሕማቸውም የተንዠረገገ ነበር:: እድሜአቸውን ግን መገመት የሚቻል አይመስለኝም:: 🕊 † የበርሃው ኮከብ አባ ብሶይ † 🕊
† ታላቁ አባ ብሶይ [ቢሾይ] :-
• በ፬ [4] ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ
• በመላእክት መሪነት የመነኑ
• የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር ባልንጀራ
• የአባ ባይሞይ ደቀ መዝሙር የነበሩ
• በአጭር ጊዜ የብዙዎች አባት የሆኑ ሰው ናቸው::
† እንቅልፍን የማያውቁ
• በ፵ [40] ቀን ብቻ እህል የሚቀምሱ
• የጌታችንን እግር በየቀኑ እያጠቡ የሚመገቡ
• ፈጣሪያቸውን በጀርባቸው ያዘሉ [ነዳይ መስሎ አግኝተውት]
• በስብከተ ወንጌል አገልግሎት የተጉ
• በርካታ ጻድቃንን የወለዱ ታላቅ የፍቅር ሰው ናቸው::በዘመናቸው ብዙ ተአምራትን ሰርተው: ቤተ ክርሰቲያንን በንጽሕናቸው አስደስተው: ሐምሌ ፰ [8] ቀን ዐርፈዋል:: ግብፅ ውስጥ የሚገኘው ገዳማቸው ዛሬም ቤተ አበው: ተአምራት የማይለዩትና ተወዳጅ ነው:: ቦታው መካነ ሱባዔ ወመንክራት ነውና:: 🕊 † አባ ሚሳኤል ነዳይ † 🕊 † መቼም ያ ዘመን [፬ [4] ኛውና ፭ [5] ኛው ክ/ዘመን] እጅግ የተባረከ ነው:: ቅዱሳኑ በብዛት የባለጸጐችና የነገሥታት ልጆች ናቸው:: አባ ሚሳኤልም የኬልቄዶን ንጉሥ ልጅ ሳሉ መንነው በበርሃ ለ፷፭ [65] ዓመታት ተጋድለዋል:: በመጨረሻ ግን በደዌ ምክንያት ወደቁ:: ለ፭ [5] ዓመታት መነኮሳቱ ሲጠይቁዋቸው ቆይተው ሰለቹ:: ከዛም ለ፲፭ [15] ዓመታት ላበታቸው በግንባራቸው እየተቀዳ: ያለ ምንም ምግብ እያቃሰቱ በበዓታቸው ወድቀው ኑረዋል:: ቸሩ አምላክ ግን ፬ [4] ቱን ሊቃነ መላእክት [ሚካኤል: ገብርኤል: ሩፋኤልና ሳቁኤልን] አዞላቸው ሲጠብቁዋቸው ኑረዋል:: በዚህች ቀንም አቡነ_ኪሮስ መጥተው አጽናንተው: ጌታችንንም ጠርተው እንዲያርፉ አድርገዋል:: መላእክት እያጠኑና እየዘመሩ ጻድቁ ቀብረዋቸዋል:: በመቃብራቸውም ላይ ፈውስ የሆነ ጸበል ፈልቁዋል::
† እግዚአብሔር የእኛን ያይደለ የጻድቃኑን ቅድስና አስቦ ይራራልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::[ † ሐምሌ ፰ [ 8 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. አቡነ ኪሮስ ጻድቅ [አረጋዊና ገዳማዊ] ፪. አባ ብሶይ ጻድቅ [ኮከበ ገዳም] ፫. አባ ሚሳኤል ነዳይ [ጻድቅ] ፬. አባ ቢማ ሰማዕት ፭. አባ በላኒ ሰማዕት ፮. ቅዱሳን አቤሮንና አቶም [ሰማዕታት] [ † ወርሐዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት ፪. ኪሩቤል [አርባዕቱ እንስሳ] ፫. አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን ፬. ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ [ከ፲፪ [12] ቱ ሐዋርያት]
† "በረከት በጻድቅ ራስ ላይ ነው:: የኃጥአንን አፍ ግን ግፍ ይከድነዋል:: የጻድቅ መታሠቢያ ለበረከት ነው::" † [ምሳ.፲፥፯] (10:7)
† "እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና:: ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና:: ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል. . . ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም::" † [መዝ.፴፮፥፳፰-፴፩] (36:28-31)† ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር †
ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ† † † @degnitKindness
Photo unavailableShow in Telegram
የሰንበት እንግዳችን
ዘማሪት ፅጌሬዳ ጥላሁን🥰
ምሽት 4:00 ሰአት ላይ
ዛሬ ማንም እንዳይቀር👈
👇👇
https://t.me/+5awDknpL-2g5ZGVk
https://t.me/+5awDknpL-2g5ZGVk
👍 1
🛑live የዲላ ኦርቶዶክሳውያን live🛑
ይ🀄️ላ🀄️ሉ
💁♂ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ ግዴታዬ ነው የሚል የማንኛውም ኦርቶዶክስ ሊቀላቀለው የሚገባ ቻናል። ጥያቄ ይጠየቃል ምዕመኑም ይሳተፋል ቻናሉን ለመቀላቀል
🔐ከስር ክፈት የሚለውን
በመጫን ይቀላቀሉ👇👇👇
ክፈት ክፈት ክፈት
ክፈት ክፈት ክፈት
ክፈት ክፈት ክፈት
................💚💛❤️...............
ክፈት ክፈት ክፈት ክፈት ክፈት ክፈት
ክፈት ክፈት ክፈት
...............💚💛❤️................
ክፈት ክፈት ክፈት ክፈት ክፈት ክፈት
ክፈት ክፈት ክፈት
📖ሥርዓተ ቤተክርስትያን⛪️
💁♂ይ🀄️ላቀ🀄️ሉ🔐
Photo unavailableShow in Telegram
የሰንበት እንግዳችን
ዘማሪት ፅጌሬዳ ጥላሁን🥰
ምሽት 4:00 ሰአት ላይ
ዛሬ ማንም እንዳይቀር👈
👇👇
https://t.me/+5awDknpL-2g5ZGVk
https://t.me/+5awDknpL-2g5ZGVk
🛑live የዲላ ኦርቶዶክሳውያን live🛑
ይ🀄️ላ🀄️ሉ
🔹 ✥● ከሚከተሉት ውስጥ ቅድስት ሃገራችን ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ከሚለው መጠርያ ስሟ ሌላ በየትኛው ትጠራ ነበር?? ✥●
🎤ድምፅ ተዋህዶ🎙
⚫️ሀ. ቶኔቶር
🔴ለ. የኩሽ ምድር
🔵ሐ. የሳባ ምድር
⚪️መ. ሁሉም መልስ ነው
إظهار الكل...
በካራን
በሎዛን
በቤርሳቤህ
اختر خطة مختلفة
تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.