cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

"ወደ ደግነት በጎ አድራጎ ማህበር እንኳን በደህና መጡ" የድግነት ዋናው አላማ ለተቸገሩ ያቅማችንን ማድረግ እና እርስ በርሳችን መጠያየቅ መረዳዳት ነው ✍️ "ደግነት የአቅም ጉዳይ ሳይሆን የልብ ጉዳይ ነው " ባለን ነገር ሁሉ እንረዳዳ፤እንተዛዘን 👉"ሰው ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው"👈 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ( 1000532242685 ) ናትናኤል ታደለ እና ቴዎድሮስ አበራ

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
16 211
المشتركون
+6824 ساعات
+3797 أيام
+2 03030 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

Photo unavailableShow in Telegram
የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ?👇👇👇
إظهار الكل...
🎤 ሊቀ መዘምራን . ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ
🎤 ሊቀ መዘምራን ይልማ ሐይሌ
🎤 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
🎤 ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ
🎤 ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
📌 የሁሉንም ዘማሪዎች መዝሙር 🔐
🙋‍♀ ጥያቄ ======== 💠• ከመንፈስ ፍሬዎች መካከል ቀዳሚነትን የሚይዘው የትኛው ነው❓
إظهار الكل...
ሀ. ትዕግስት
ለ. እምነት
ሐ. ደስታ
መ. ፍቅር
ሀገር
መሰዋትነት
💁‍♀ መልሱን ለማግኘት
†  እንኳን ለቅዱሳን ጻድቃን ወከዋክብተ ገዳም አቡነ ኪሮስ: አባ ብሶይ እና አባ ሚሳኤል ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን።  †
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊  †   አቡነ ኪሮስ ጻድቅ   †   🕊 † የጻድቁን ስም የሚጠራ አፍ ንዑድ ነው: ክቡር ነው:: በእውነት የቅዱሱን አባት ክብር ለማግኘት መፋጠን ይበጃል:: አቡነ_ኪሮስ የተወለዱት በ፬ [4] ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን ወላጆቻቸው ነገሥታት ናቸው:: ተወልደው ባደጉባት ሃገር ቁስጥንጥንያ ገና በልጅነት ምቾት ሳያሳሳቸው መጻሕፍትንና ትሕርምትን ተምረዋል:: ወንድማቸው [ታላቁ ቴዎዶስዮስ] በነገሠባቸው የመጀመሪያ ዓመታት በቤተ መንግስቱ ዙሪያ ግፍ በዝቶ ነበርና አቡነ ኪሮስ ከኃጢአት ለመራቅና ለጌታ ለመገዛት ከከተማው ጠፍተው: አሕጉር አቋርጠው ወደ ግብፅ [ገዳመ አስቄጥስ] መጡ:: እርሳቸውን ለመፈለግ የተደረገው ሙከራ አልተሳካም:: ይባስ ብሎ የንጉሡ ልጅ ገብረ ክርስቶስ ሙሽርነቱን ጥሎ ወደ ሌላ ሃገር መነነ:: "የቅኖች ትውልድ ይባረካል" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት:: አቡነ ኪሮስ ለሙሽራው ገብረ ክርስቶስ አጎቱ ናቸው:: አቡነ ኪሮስ በገዳም ውስጥ የታላቁ አቡነ በብኑዳ ደቀ መዝሙር ሆነው ለዘመናት ቆይተዋል:: ቅዱስ በብኑዳን አንበሳ በበላው ጊዜ በጣም አዝነው "ለምን ጌታ ሆይ?" በሚል መሬት ላይ ወድቀው አለቀሱ:: "ምክንያቱ ካልተነገረኝ አልነሳም" ብለው ከወደቁበት መሬት ላይ ሳይነሱ ለ40 ዓመታት አልቅሰዋል:: በዚህ ምክንያት ግማሹ አካላቸው አፈር ሆኖ ሣር በቅሎበታል:: ጌታችን ተገልጦ ምክንያቱን ነግሯቸዋል:: አካላቸውንም እንደነበረ መልሶላቸዋል:: አንድ ቀን ጻድቁ ለቅዱስ በብኑዳ ሞት ምክንያት የሆነው መነኮስ ታንቆ መሞቱን ሰምተው በጣም አዘኑ:: ሱባዔ ገብተው: ፍጹም አልቅሰው: ከጌታም አማልደው: የዛን ኃጥእ ነፍስ ከሲዖል አውጥተዋል:: በሌላ ጊዜ ደግሞ ኃጥአን የሞሉበት አንድ ገዳም በግብጽ ነበርና መቅሰፍት ወርዶ ሁሉንም ባንድ ቀን ሲያጠፋቸው አዩ:: ጻድቁ በዚህም ምክንያት ለ፴ [30] ዓመታት አልቅሰው: ሙታኑን አስነስተው: ንስሃ ሰጥተው: ገዳሙን የጻድቃን: ሕይወታቸውንም የፍቅር አድርገውታል:: ጻድቁ እመቤታችንን ከመውደዳቸው የተነሳ በስዕሏ ፊት አብዝተው ይሰግዱና ያለቅሱ ነበር:: እመ አምላክም ተገልጣ ትባርካቸው ነበር:: ከዚህ በሁዋላ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ሒደው ለ፶፯ [57] ዓመታት ማንንም ሳያዩ ተጋደሉ:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ [ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና] በየቀኑ ይጐበኛቸው: ቁጭ ብሎም ያወራቸው ነበር:: በመጨረሻም በዚህች ቀን ጌታ አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን: ድንግል እመቤታችንና ቅዱስ ዳዊትን አስከትሎ ወረደ:: ቅዱስ ዳዊት ቀርቦ እያጫወታቸው: በበገናው እየደረደረላቸው: ከዝማሬው ጣዕም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ጌታችንም ታቅፎ: ስሞ ይዟቸው አረገ:: ሥጋቸውን #አባ_ባውማ ቀበሩት:: የአቡነ ኪሮስ ቁመታቸው ቀጥ ያለ: ጽሕማቸውም የተንዠረገገ ነበር:: እድሜአቸውን ግን መገመት የሚቻል አይመስለኝም:: 🕊  † የበርሃው ኮከብ አባ ብሶይ  †  🕊
† ታላቁ አባ ብሶይ [ቢሾይ] :-
• በ፬ [4] ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ
• በመላእክት መሪነት የመነኑ
• የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር ባልንጀራ
• የአባ ባይሞይ ደቀ መዝሙር የነበሩ
• በአጭር ጊዜ የብዙዎች አባት የሆኑ ሰው ናቸው::
† እንቅልፍን የማያውቁ
• በ፵ [40] ቀን ብቻ እህል የሚቀምሱ
• የጌታችንን እግር በየቀኑ እያጠቡ የሚመገቡ
• ፈጣሪያቸውን በጀርባቸው ያዘሉ [ነዳይ መስሎ አግኝተውት]
• በስብከተ ወንጌል አገልግሎት የተጉ
• በርካታ ጻድቃንን የወለዱ ታላቅ የፍቅር ሰው ናቸው::
በዘመናቸው ብዙ ተአምራትን ሰርተው: ቤተ ክርሰቲያንን በንጽሕናቸው አስደስተው: ሐምሌ ፰ [8] ቀን ዐርፈዋል:: ግብፅ ውስጥ የሚገኘው ገዳማቸው ዛሬም ቤተ አበው: ተአምራት የማይለዩትና ተወዳጅ ነው:: ቦታው መካነ ሱባዔ ወመንክራት ነውና:: 🕊  †  አባ ሚሳኤል ነዳይ  †   🕊 † መቼም ያ ዘመን [፬ [4] ኛውና ፭ [5] ኛው ክ/ዘመን] እጅግ የተባረከ ነው:: ቅዱሳኑ በብዛት የባለጸጐችና የነገሥታት ልጆች ናቸው:: አባ ሚሳኤልም የኬልቄዶን ንጉሥ ልጅ ሳሉ መንነው በበርሃ ለ፷፭ [65] ዓመታት ተጋድለዋል:: በመጨረሻ ግን በደዌ ምክንያት ወደቁ:: ለ፭ [5] ዓመታት መነኮሳቱ ሲጠይቁዋቸው ቆይተው ሰለቹ:: ከዛም ለ፲፭ [15] ዓመታት ላበታቸው በግንባራቸው እየተቀዳ: ያለ ምንም ምግብ እያቃሰቱ በበዓታቸው ወድቀው ኑረዋል:: ቸሩ አምላክ ግን ፬ [4] ቱን ሊቃነ መላእክት [ሚካኤል: ገብርኤል: ሩፋኤልና ሳቁኤልን] አዞላቸው ሲጠብቁዋቸው ኑረዋል:: በዚህች ቀንም አቡነ_ኪሮስ መጥተው አጽናንተው: ጌታችንንም ጠርተው እንዲያርፉ አድርገዋል:: መላእክት እያጠኑና እየዘመሩ ጻድቁ ቀብረዋቸዋል:: በመቃብራቸውም ላይ ፈውስ የሆነ ጸበል ፈልቁዋል::
† እግዚአብሔር የእኛን ያይደለ የጻድቃኑን ቅድስና አስቦ ይራራልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::
[ † ሐምሌ ፰ [ 8 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ] ፩. አቡነ ኪሮስ ጻድቅ [አረጋዊና ገዳማዊ] ፪. አባ ብሶይ ጻድቅ [ኮከበ ገዳም] ፫. አባ ሚሳኤል ነዳይ [ጻድቅ] ፬. አባ ቢማ ሰማዕት ፭. አባ በላኒ ሰማዕት ፮. ቅዱሳን አቤሮንና አቶም [ሰማዕታት] [ †  ወርሐዊ በዓላት ] ፩. ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት ፪. ኪሩቤል [አርባዕቱ እንስሳ] ፫. አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን ፬. ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ [ከ፲፪ [12] ቱ ሐዋርያት]
† "በረከት በጻድቅ ራስ ላይ ነው:: የኃጥአንን አፍ ግን ግፍ ይከድነዋል:: የጻድቅ መታሠቢያ ለበረከት ነው::" † [ምሳ.፲፥፯] (10:7)
† "እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና:: ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና:: ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል. . . ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ:: በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ:: የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል:: አንደበቱም ፍርድን ይናገራል:: የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው:: በእርምጃውም አይሰናከልም::" † [መዝ.፴፮፥፳፰-፴፩] (36:28-31)
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር †
ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ 
         †              †               † @degnitKindness
إظهار الكل...
إظهار الكل...
ስንክሳር ሐምሌ - ፰ - .mp36.83 MB
Photo unavailableShow in Telegram
የሰንበት እንግዳችን ዘማሪት ፅጌሬዳ ጥላሁን🥰 ምሽት 4:00 ሰአት ላይ      ዛሬ ማንም እንዳይቀር👈           👇👇 https://t.me/+5awDknpL-2g5ZGVk https://t.me/+5awDknpL-2g5ZGVk
إظهار الكل...
👍 1
🛑live የዲላ ኦርቶዶክሳውያን live🛑
ይ🀄️ላ🀄️ሉ
Photo unavailableShow in Telegram
የሰንበት እንግዳችን ዘማሪት ፅጌሬዳ ጥላሁን🥰 ምሽት 4:00 ሰአት ላይ      ዛሬ ማንም እንዳይቀር👈           👇👇 https://t.me/+5awDknpL-2g5ZGVk https://t.me/+5awDknpL-2g5ZGVk
إظهار الكل...
🛑live የዲላ ኦርቶዶክሳውያን live🛑
ይ🀄️ላ🀄️ሉ
🔹 ✥● ከሚከተሉት ውስጥ ቅድስት ሃገራችን ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ከሚለው መጠርያ ስሟ ሌላ በየትኛው ትጠራ ነበር?? ✥●
إظهار الكل...
🎤ድምፅ ተዋህዶ🎙
⚫️ሀ. ቶኔቶር
🔴ለ. የኩሽ ምድር
🔵ሐ. የሳባ ምድር
⚪️መ. ሁሉም መልስ ነው
اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.