cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ASD AJ LAH

ካነበብኩት…

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
651
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+67 أيام
+5530 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

"ሰሞኑን እናት እናት ማለት አብዝተሀል አፍቅረህ ተከዳህ ወይ?" ብለህ የጠየቅከኝ ልጅ ግን አንጎሌን ነው የነካሀው
إظهار الكل...
ያለብርድ ልብስ ተኝተን ስንነቃ ራሳችንን ከአንድ ብርድ ልብስ ጋር እናገኘዋለን:: ማን አልብሶን? እናት:: አንድ ዳቦ አዘን ሁለት ሆኖ ይመጣል:: ከየት? ከእናት ቤት:: አራት ሆነን 3 ዳቦ ብቻ ካለ እኔኮ በልቻለሁ ብላ ተነስታ ትሄዳለች:: ማን? ኡሚ:: ወደ ሩቅ ሀገር ስትሄድ በቦርሳህ ሙሉ ምግብ አሸክማ ትልካለች:: ማን? ማማ:: ቆይተህ ስትመለስ ከመግባትህ ግባ ራት ብላ ብላ ትጋብዝሃለች:: ማን? ሀርሜ:: ማንም ቢሆን የእርሷን ቦታ አይሸፍንም:: ማንም:: ማን እንደ እናት?!😍 Mohammadammin
إظهار الكل...
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን! 📌 11 ከፍተኛ ኮሚሽነሮች ሲኖሩት ከእነሱ መካከል 1 ሙስሊም ብቻ ነው የተካተተው:: 📌 እስካሁን በተደረገ የተሳታፊ ልየታ 12ሺህ ሰዎች የተለዩ ሲሆን ከእነዚያ መካከል 216 (1.8%) ብቻ ሙስሊም ይገኛል:: 📌 ተሳታፊ ተብለው ከተለዩት ውስጥ እንኳ ኮሚሽኑ ጎንደር ላይ ባደረገው ስብሰባ እንዳይሳተፉ እንደተደረጉ ሚዲያዎች ዘግበዋል:: 📌 የፌደራል መጅሊስ ሙስሊሙ በቁጥሩ ልክ እንዳልተወከለ በመግለፅ ኮሚሽኑ እየሄደበት ያለውን መንገድ ዳግም እንዲያጤነው አቤቱታ ቢያቀርብም እስካሁን ድረስ ጆሮ ዳባ ልበስ እንዳለ ነው:: 📌 የአማራ ክልል መጅሊስ የኮሚሽኑ አካሄድ በዚሁ ከቀጠለና ማስተካከያዎች ካልተደረጉ የሚመጡ ውሳኔዎችን እንደማይቀበል ከወዲሁ አሳውቋል:: 🔺 ሙስሊሙ ለምን ተዘነጋ? ውክልናውን በቁጥሩ ልክ ለመስጠት ለምን አሻፈረኝ አሉ? ቅሬታዎቹንስ ለማዳመጥ ለምን አመነቱ? ወይንስ የእርሱ አጀንዳዎች የሀገር አጀንዳ አይደሉም? ወይንስ የእርሱ ችግሮች ከሀገሪቱ ችግር 1% ብቻ ነው? ወይንስ የእርሱ መቸገር ማንንም አያሳስብም? እነዚህን ጥያቄዎች ራሳችንን እንጠይቅ:: 🔺 ከዚያ ባሻገር ስለ ሀገራዊ ምክክሩ በያለንበት እንወያይ:: ሀሳብ እናንሸራሽር:: ሀሳብ እንለዋወጥ:: ድምፃችን ከቢሯቸው ደርሶ እስኪሰማቸው ድረስ እንጩህ:: @MohammadamminKassaw
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
የሀገራዊ ምክክር! የሀገራዊ ምክክር ማለት ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ ላልሆነላችሁ ከአንበሳ ባስ ጀርባ ላይ ያለው "ምክክራችን ለነገዋ ኢትዮጵያችን!" የሚለው የኮሚሽኑ መፈክር በመጠኑም ቢሆን ይገልፀዋል:: "ኮሚሽኑ የነገዋ ኢትዮጵያ ምን መምሰል እንዳለባት መላው የኢትዮጵያ ህዝብን ባሳተፈ መልኩ ይወያያል:: ተወያይቶም አንድም ኢትዮጵያዊ ቢሆን እንኳ በሀገሩ ጉዳይ ቅር የማይሰኝበትንና ለወደፊቷ ኢትዮጵያ መፃኢ እድል የሚሰራበትን ከባቢ ይፈጥራል::" ተብሎም ይታሰባል:: በዚህ ረገድ "የሀገሪቱ ታሪክ ምን ይምሰል? ባንዲራዋ እንዴት ይሁን? ብሔራዊ መዝሙሯ ምንን ያካት? የስልጣን ክፍፍሉ ምን ይምሰል? ህዝቦች የሀገራቸውን ሀብት እንዴት ይጠቀሙ? በመንግስት ተቋማት ውስጥ ምን አይነት ቦታ ይኑራቸው..." የሚሉና ሌሎች ጥያቄዎች መልስ ያገኛሉ:: በዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ ኮሚሽኑ አካታችነት: ግልፀኝነት: ታማኝነት መርሆዎቹ ናቸው:: አካታችነት ሲባል በሰላማዊ መንገድ ፓርቲ አቋቁመው ከሚታገሉት ጀምሮ ነፍጥ አንግበው ጫካ ያሉትን ጭምር ከግምት ያስገባ ነው:: በተቋም ደረጃም ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጭምር የሃይማኖት ተቋማት: እድሮች እንዲሁም ሌሎች ሲቪል ማህበራት ይካተታሉ:: ከእነዚህ አካላት የተውጣጣ ተሳታፊ ከተለየም ቡሃላ እንደ አጠቃላይ በሚቀርቡ አጀንዳዎች ዙሪያ ተሳታፊዎች ድምፅ ሰጥተው ይወስናሉ ማለት ነው:: ስለምን ካላችሁኝ ስለ ነገዋ ኢትዮጵያ ነው:: ስለ እኔ ስለ አንተ ስተ አንቺ ማለት ነው:: 📌በአጭሩ ይህን ይመስላል:: አፅንዖት እንስጠው:: በዚህ ሰዓት እንደ ሙስሊም ከሀገራዊ ምክክሩ በላይ የሚያስጨንቀን አጀንዳ ሊኖረን አይገባም:: ዝም ብለን ሳንጠይቅ ዛሬን ካለፍን ነገ ላይ ወደ ዳግም ለቅሶና ልመና መግባታችን አይቀሬ ነው:: @MohammadamminKassaw
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰#አልዓርቢዓዐ 1️⃣4️⃣ #ዙልቀዓዳ 1️⃣4️⃣4️⃣5️⃣ ሂ
إظهار الكل...
የምንፈራት ስለምትመታን አልያም ዱላዋ ስለሚያሳምመን አይደለም ፣ ትዕዛዟን የምናከብረው ስለምትሰጠን ፍራንካ አይደለም ። እጅግ በጣም ስለምንወዳት ነው ። የእውነት ከልባዊ ፍቅር የመነጨ ቁጣዋ ያስተካክለናል ፣ መሻቷን ለመሙላት የምንወጥነው ፣ የምንደክመው የሻታቺው ሲሆን ያለመቺው ሲደርስ ፊቷ በደስታ ሲፈካ የሚወጣውን ብርሃን ለማየት ከመጓጓት ነው ። ስለምትወደን ፣ ስለምትረዳን በሚል ድንበሯን ልንጥስ ፣ የከለከለችንን ልንደፍር ሀያእ ይይዘናላ። ለሰከንድም እንድትከፋብን አንሻማ ። ሀም ገማችን ስትደሳብን ብቻ ነዋ ማየት የምንሻ ። ከእርሷና እርሷ ካስገኘችልንም በላይ የምንወደው የሚወደን ከሆነው ጌታችን ፣ ተንከባካቢያችን ከሆነው ከአላህስ ጋር ? አላህ ሆይ የቀደሙንን ለጀንናህ ያሉትን በዐፊያ በዒማን አቆይልን ። አብዱረዛቅ
إظهار الكل...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
👍 1👎 1
╭── ••™ 🍂"سبحان الله وبحمده عدد خلقهِ ورِضَا نفسِهِ وزِنُة عَرشِهِ ومِداد كلماته" أسعد الله صباحكم..🤍 ‏ ╰───➤ #صباح_الخير ‏
إظهار الكل...
#ከዚክሪኩም_አባኣኩም #ወቀፈትኒል_አያህ ቤት ውስጥ ያሉት ልጆችህ በቀን ምን ያህል ጊዜ እንደሚጠሩህ አስተውለህ ታውቃለህ?! ሕጻናት ገና በወራት ዕድሜ ላይ ሳሉ ለወላጆቻቸው በተለይም ለአባታቸው ብዙ ስሞችን ያወጣሉ። ከዚያም በየቀኑና በየሰአቱ ስሙን ይጠራሉ። «አባ፣ አባቴ፣ ባባዬ ...» አባት ሲጠራ ያለው ደስታ ልዩ ነው፤ ልጅም የአባትን ምላሽ ሲሰማ ይፈነጥዛል። ይህን አልበቀራ ምዕራፍ ጌታችን አላህ (ሱወ) ሲገለጸው እንዲህ ይላል፦ « የሐጅ ሥራዎቻችሁንም በፈጸማችሁ ጊዜ አባቶቻችሁን እንደምታወሱ ወይም ይበልጥ የበረታን ማውሳት አላህን አውሱ፡፡» ጌታችን አላህ ልጆች ያለመታከት አባታቸውን በሚጠሩበት ልክ መወሳትን ይፈልጋል። ከሕጻናት ብዙ የምንወስደው ነገር አልለ። የልብ ጽዳትን፣ እውነተኛ መኾንን፣ ነጻ ዐለምን፣ እንዲሁም በአላህ የመወከልን ትርጉም እናገኛለን። ከሱረቱል በቀራህ 199 ቁጥር ላይ የተማርኩት ዐሳብ ነው። አላህ ያስረዳና ♥
إظهار الكل...
👍 4
Photo unavailableShow in Telegram
📆#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ ⏰ #አሱለሳዒ 1⃣3⃣ #ዙልቀዓዳ  1⃣4⃣4⃣5⃣ ሂ
إظهار الكل...