Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 069
المشتركون
+224 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
+230 أيام
أرشيف المشاركات
በአካታች የሥራ ዕድል ፈጠራና በከተማ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ዙሪያ ያተኮረ አውደ ጥናት ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ተሞክሮ ቀረበ፤
የኢትዮጵያ ከተሞች የትብብር መድረክ ከኔዘርላንድ የከተሞች ትብብር መድረክ (VNGI) “ዊ አር ኤብል” ከተሰኘው ፕሮግራም ጋር በመተባበር የአካል ጉዳተኞች በከተማ ሴፍቲኔት ፕሮጀክቶች አካታችነትና ተጠቃሚነት፣ በከተሞች የአፈጻጸም ተሞክሮ ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና ዘላቂ መፍትሄዎች ዙሪያ ላይ ያተኮረ የአንድ ቀን የልምድ ልውውጥ አውደጥናት በአዳማ ከተማ አካሂዷል፡፡
በዚህም መድረክ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደርን ተሞክሮ የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ያቀረቡ ሲሆን በአጠቃላይ አካታች የሆነ የሥራ ዕድል ፈጠራ ተደራሽነትና ጥራትን ከማረጋገጥ አኳያ እንደማሳያም ከቢሮው ጀምሮ በተመሳሳይ ተቋማት በቅጥር እንዲሁም ተደራጅተው ሥራ እንዲፈጥሩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ በመስራት የአካል ጉዳተኞች አካታችነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አስቻይ የሆኑ የተሰሩ ሁሉ አቀፍ ስራዎች መኖራቸውን አብራርተዋል፡፡
በተያያዘ “ዊ አር ኤብል” ፕሮግራም ከሌሎች መሰል ድርጅቶች ጋር በመተባበር የኢትዮጵያ ከተሞችን የምግብ ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡና ከተሞች የልማት ስራዎቻቸውን በሚያከናውኑበት ወቅት ለአካል ጉዳተኞች ልዩ ትኩረት እንዲሰጡ እንዲሁም ለነዋሪዎቻቸው ደግሞ የስራ ዕድል እንዲፈጥሩ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ በዚህ አውደጥናት ተጠቅሷል፡፡
(መጋቢት16፣ 2017 ዓ.ም፣ አዳማ)
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
#ዜና | ከኮሌጆች ጋር በጋራ መስራት እና ተመሳሳይ አቅም መገንባት የኢንዱስትሪውን የሰው ኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባሻገር የስራ እድል በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚ ያደረግ ተገለፀ ::
የኢትዮ -ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከምዕራብ እና ምስራቅ አጎራባች ክልሎች ከተውጣጡ የኮሌጅ አመራሮች ጋር የልምድ ልውውጥ እና በጋራ ለመስራት
የሚስችላቸውን የስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል ።
በወቅቱ የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሞያ ኤጀንሲ ዋና ዳሬክተር ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ኮሌጁ ከኢትዮጵያ የተሰማሚነት ድርጅት
የጥራት ደረጃ እውቅና ( ISO) ያገኘና ትልቅ አቅም የሚፈጥር ኮሌጅ መሆኑን ጠቅሰው ይሄ አቅም ድሬዳዋ ላይ ብቻ ተወስኖ እንዳይቀር ከሌሎች አጎራባች ክልሎች
የቴክኒክ እና ሞያ ኮሌጅ አመራሮች ጋር በጋራ በመስራት በቴክኒክም በክህሎትም ተመሳሳይ አቅም
በመገንባት የኢንዲስትሪውን የሰው ኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባሻገር የስራ እድል በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያደረግ ነው የገለፁት።
ወ/ሮ ፈጡም አያይዘውም በየአካባቢያችን ያለውን ሀብት እንዴት መጠቀም እንዳለብን ጭምር የጋራ እውቀት አቅም እንዲኖረን የሚያደርግ የልምድ ልውውጥ
ነዉ ብለዋል። ይህ የተሞክሮ ልውውጥ በዛሬ ብቻም አያበቃም ይቀጥላልም ነው ያሉት ::
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ኮሌጁ
( EASE)ኘሮጀክትን በመተግበር ላይ እንደሚገኝ ገልጸው ፕሮጀክቱ በተለዩ ስምንት (8) የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ይሰራል ብለዋል። ይህም የዛሬው የመጀመሪያው ዙር የድሬዳዋ አጎራባች ክልሎች የቴክኒክ እና ሞያ ኮሌጅ አመራሮች ጋር ያደረግነው የልምድ ለውውጥ እና በጋራ ለመስራት የተስማማንበት መድረክ አንዱ የፕሮጀክቱ ትግበራ አካል ነው ብለዋል ::
አያይዘውም ፕሮጀክቱ በቴክኒክም በክህሎትም ጥራት ያለው መምህር በመፍጠር ገበያው የሚፈልገውን
የሰው ኃይል በማቅረብ በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን የሞያተኛ የብቃት ችግር ለመቅረፍ ብሎም
የስራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ የሚረዳ ፕሮጀክት ነው ብለዋል፡ :
ከአጎራባች ክልሎች የመጡት የቴክኒክ እና ሞያ ኮሌጅ ዲኖች በበኩላቸው የወሰድነው የልምድ ልውውጥ በየኮሌጃችን ለመተግበር የሚያስችል ተሞክሮ ቀስመናል ያሉ ሲሆን በተከታታይነትም ለመስራት የሚያስችለንን ስምምነት ላይ ደርሰናል ነው ያሉት ::
ኮሌጁ በቀጣይ በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮችላይ የስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል :: በመጨረሻም ከአጎራባች ክልሎች የመጡት እንግዶች
ኮሌጁን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
#Dire tv አማርኛ መጋቢት 13/2047
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሃሳብ በ2017 ዓ.ም የሚካሄደውን 4ኛ ዙር የክህሎት ውድድርን አስመልክቶ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የተለያዩ ኢንደስትሪዎችና ተቋማት ለተወጣጡ ውድድሩን በዳኝነት ለሚመሩ ዳኞች የኦረንቴሽን መድረክ አዘጋጀ፡፡
በዚህም ግልጽ የዳኝነት አሰራር ማስረጽና ቅሬታዎችን መቀነስ ብሎም እንዳይኖሩ መስራት የውድድሩ ዋንኛ ተግባርና ኃላፊነት በመሆኑ የዳኞች መመልመያ ተግባርና ኃላፊነት መመሪያ ለክህሎት ውድድሩ በማዘጋጀት በውድድሩ ሂደት ቅሬታዎች እንዳይፈጠሩ በመስራት ለተወዳዳሪዎች የዳኝነት አሰጣጥ ላይ የሚከናወኑ ሂደቶችን በማሳወቅና ግንዛቤ በመፍጠር በጥብቅ ዲሲፒሊን የሚመራ የዳኝነት ክትትልና ግምገማ ስርዓት በመዘርጋት መረጃዎችን በተደራጀ ሁኔታ ለውሳኔ አሰጣጥ በሚያመች ሁኔታ ከማወዳደሪያ ሰነዱ ጋር በማያያዝ በየደረጃው ለሚገኙ አካላት ውጤቱን በማደራጀት ማስረከብ እንዲሁም በዳኝነት ስራቸው ላይ ለሚነሱ ቅሬታዎች ከአስፈላጊው መረጃ ጋር እንደ አስፈላጊነቱ ለቅሬታ ኮሚቴ ምላሽ መስጠት በሚያስችላቸው አግባብነት ላይ ተገቢ የሆነ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ተደርጓል፡፡
በመሆኑም ውድድሩ ከፊታችን መጋቢት 16/2017 ዓ.ም ጀምሮ የኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎችን በማሳተፍ በክላስተር ደረጃ የሚካሄድ ሲሆን በተለይም መሰል ውድድሮችን ማካሄድ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች ያሉት በመሆኑ በውድድር ከማሸነፍ በላይ የክህሎት እና እውቀት ሽግግሩ ወሳኝ መሆኑን የቢሮው ም/ኃላፊና የኤጀንሲው ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 13/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ለድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በየሳምንቱ ሀሙስ ቀን በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ በተከታታይ እያካሄደ የሚገኘውን ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በማጠናከር በድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚገኙ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዘርፉን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል::
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ ተማሪዎች ስለ ቴክኒክና ሙያ ተገቢውን ግንዛቤ እንዲያገኙ ከማደረግ አኳያና እንደ ሀገር ከተያዘው የትኩረት አቅጣጫም አንፃር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ለወጣቱ በተለይም ከዚህ በኃላ ወደ ዘርፉ ለሚቀላቀሉ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ብዙ መልካም እድሎችን የያዘ ዘርፍ መሆኑን በማስገንዘብ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ መስራት ተችሏል::
የግንዛቤ ማስጨበጫውን ለተማሪዎች የሰጡት የኮሌጁ ዲኖች እንዲሁም አሰልጣኝ መምህራን ሲሆኑ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋም ከመቀላቀላቸው አስቀድሞ ከወዲሁ በአስተሳሰብም ሆነ ለዘርፉ ባላቸው አረዳድ ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያደርጋቸውን ምክረ ሀሳብና በኮሌጁ ያለውን ምቹ አጋጣሚ ለተማሪዎች በዝርዝር ያስረዱ ሲሆን የህይወት ልምዳቸውንም አካፍለዋል::
በቀጣይም ተማሪዎች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶቻቸውን እንዲያዳብሩ የሚረዳቸውን የቴክኒክና ሙያ (STEM) ክበብ በየትምህርት ቤቶቹ በመቋቋም ላይ እንደሚገኙ የተገለፀ ሲሆን ይህም የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ቀደም ብለው ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር ትስስር እንዲፈጥሩና በሲስተም ውስጥ እንዲያልፉ እድል እንደሚፈጥርላቸውም ተገልፇል::
በተጨማሪም በአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሴት ተማሪዎች ቁጥር አብላጫውን እንደሚይዝና ነገር ግን የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ የሴቶች ተሳትፎ ውስን በመሆኑ ሴቶች በዘርፉ በስፋት እንዲሳተፉ ማበረታታትና መደገፍም እንደሚገባ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
መጋቢት 12/2017 ዓ.ም
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+5
#ዜና| የአሰልጣኞችን የክህሎት ክፍተት በየጊዜው መሙላት ጥራት ያለው ትምህርትና ስልጠና ከመስጠት በዘለለ ለሚሰሩት ቴክኖሎጂዎች ጥራትና ያላቸውና ውጤታማ የሆነ የፈጠራ ስራ እንዲኖራቸው ያስችላል ተባለ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከተለያዩ የትምህርት ክፍል ለተውጣጡ መምህራን በAutocad እና በsolid work ላይ ትኩረቱን ያደረገ ለ15 ቀናት ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና አጠናቀቀ፡፡
ስልጠናው በዋናነት በተለየው የክህሎት ክፍተት መሰረት የአሰልጣኝ መምህራኑን የዲዛይን ክህሎት ለማዳበር የታለመ እንደሆነ የገለጹት የኮሌጁ ም/ዲንና የኢ/ኤ/ቴ/ሽግግር ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ አያይዘውም በየጊዜው ለአሰልጣኝ መምህሩ የሚደረጉ ስልጠናዎች በትምህርትና ስልጠናው ላይ ብቻ ሳይሆን በሚሰሩ ቴክኖሎጂዎች ላይ ለውጥ እያሳየ እንዳለ ገልጸዋል፡፡ም/ዲኗ በመቀጠልም በዚህ ስልጠና በተገኘው ግብአት መሰረት በቀጣይ በእጅ ከሚሰራው የዲዛይን ስራ ወደ ኮምፒዩተራይዝድ የዲዛይን ስራ ለማሳደግ እንዲሁም ኮሌጁ በቀጣይ የቴክኖሎጂ ማእከል እንደመሆኑ መጠን የተለያዩ ምርቶችን እያመረተ ለማህበረሰቡ ብሎም ለኢንዱስትሪዎች የሚያቀርብ ስለሆነ የሚሰሩት ስራዎች በሙሉ በኮምፒውተር በተደገፈ አይነት መልኩ መሆን ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡
ለተከታታይ 15 ቀኛት የተሰጠው ይህ ስልጠና በAutocad 2D ፣3D Drawing እንዲሁም በsolid work ላይ ትኩረቱን አድርጎ ሲሰጥ እንደነበረ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 13/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+8
#ዜና| በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ ለሚካሄደው የክህሎት ውድድር የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሚወክሉ ተወዳዳሪዎችን ለምረጥ የታለመ የክህሎት ውድድር ማከናወን ጀመረ፡፡
በዘንድሮ በጀት ዓመት ለ4ኛ ጊዜ ‹‹ ብሩህ አዕምሮዎች ፣በክህሎት የበቁ እጆች!››በሚል መሪ ሀሳብ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ብቁ የሆኑ ተወዳዳሪዎችን ለመምረጥ ያለመ ከኮሌጅ ጀምሮ እስከ ክልል ድረስ የሚሄድ የተለያዩ የምዘና ስራዎች በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየተሰሩ ሲሆን በዚህም በICT ፣በTextile and Garment በElectrical Electronics፣በ Automotive ፣በManufacturing ፣በHotel Truism ትምህርት ክፍሎች ለበርካታ ሰልጣኝ ተማሪዎች ምዘናዎች ተደርገዋል፡፡
ይህ የክህሎት ውድድር ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን ወደ ተግባር በመለወጥ ሂደት የበቁ ዜጎችን ለመፍጠር የሚያስችልና የፈጠራ ሃሳባቸውን ወደ መሬት አውርደው ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ ውድድር እንደሆነ በውድድሩ ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡
በትናንትናው እለት የተጀመረው ይህ ውድድር በኮሌጅ ደረጃ የተደረገ ሲሆን በቀጣይ ደግሞ በክላስተር ደረጃ የተለያዩ ውድድሮች የሚደረጉ ይሆናል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከ3 ሚሊየን በላይ የስራ ዕድሎችን መፈጠራቸውን ገለጹ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት 8 ወራት ከ3 ሚሊየን በላይ የስራ ዕድሎችን መፍጠር መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ባለፉት 8 ወራት በተመዘገበ መረጃ በሀገር ውስጥ 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ዜጎች የስራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ከ300 ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎች ደግሞ በውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ዕድል ማግኘታቸውን ገልጸው፤ ከ45 ሺህ በላይ ዜጎች በሪሞት ጆብ ወይም በዲጂታል መንገድ ስራ ማግኘት መቻላቸውን ገልጸዋል፡፡
የግብርናው ዘርፍ 40 በመቶ፣ ኢንዱስትሪ 20 በመቶ፣ ሰርቪስ 38 በመቶ የስራ ዕድሎች የተገኙባቸው ዘርፎች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ከሴክተሮች በተጨማሪ በኮሪደር ስራዎች እና ልዩ ልዩ ኢኒሼቲቮች በርካታ የስራ ዕድሎችን ፈጥረናል ብለዋል፡፡
ካለው አምራች ሀይል አንፃር አሁን ያለው የስራ ዕድል በቂ አለመሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በቀጣይም ያለውን የስራ ፍላጎት በሚመጥን መልኩ ዜጎችን የስራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ አመላክተዋል፡፡
FBC
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ምንድን ናቸው?
*****
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል
. በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ታጥቀው ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት ምን እየተሠራ ነው?
. የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም በምን ደረጃ ላይ ይገኛል? ፤ በትግራይ ዳግም ጦርነት እንዳይነሳስ ምን እየተሠራ ነው?
. የፍትሕ ተደራሽነት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከመሰረቱ ለመፍታት መንግሥት በቀጣይ ምን ለመስራት አስቧል?
. በሰላም እጦት ሳቢያ በበርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች በሕዝብ ላይ የሚደርሰውን እንግልት ከመሰረቱ ለመፍታት ምን እየተሠራ ነው?
. በአምራች ዘርፉ ያለውን የጥሬ ዕቃ እና የሌሎች የአቅርቦት ችግሮ ለመፍታት መንግሥት ምን እየሠራ ይገኛል?
. የ10 ዓመቱን ስትራቴጂክ ዕቅድ ማሳካት መቻላችንን የሚያመላክቱ መስፈሪያዎች ምንድን ናቸው? ፤ ሴክተሮችስ ከዚህ ዕቅድ ጋር ምን ያህል ተናበው እየሰሩ ነው?
. መንግሥት በድጎማ የሚያቀርበው ነዳጅ በሕገ-ወጥ መንገድ እንዳይሸጥ ምን አይነት ጠንካራ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው?
. በአሁኑ ሰዓት የመንግሥት ሠራተኛን ጨምሮ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች በኑሮ ውድነት እየተቸገሩ ባሉበት ሁኔታ እንዴት የዋጋ ግሽበት ቀንሷል ሊባል ይችላል?
. የቁጥጥር ተቋማት ነጻ ሆነው በትክክል ኃላፊታቸውን እንዲወጡ ምን አይነት ሥራዎች እየተሰሩ ነው?
. የባሕር በር ለማግኘት ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተደረጉ ዲፕሎማሲያዊ ስምምነቶች በምን ደረጃ ላይ ይገኛሉ?
. ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ያላቸውን የቤት ፍላጎት እና አቅርቦት ለማጣጣም ምን እየተሰራ ነው?
. የኮሪደር ልማትን ተከትሎ የሚነሱ የአፈጻጸም ችግሮችን እና ቅሬታዎችን ለመፍታት እየተወሰዱ ያሉ ርምጃዎች ምን ይመስላሉ?
. የአፈር ማዳበሪያ ስርጭት ላይ መዘግየት እንዳይፈጠር ምን እየተሰራ ነው?
. የመሬት አቀማመጣቸው ወጣ ገባ በሆኑ እና ለሜካናይዜሽን በማይመቹ አካባቢዎች ምርታማነት ለማሳደግ ምን እየተሠራ ነው?
. እስካሁን የተፈጠረው የሥራ ዕድል ካለው ፍላጎት ጋር ምን ያክል የተመጣጠነ ነው?
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
