Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 063
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-77 أيام
+230 أيام
أرشيف المشاركات
+1
ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም፣ የመረዳዳትና የመተጋገዝ እንዲሆን እመኛለሁ።
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
✨ አዲስ ተስፋ፣ አዲስ ዓመት፣ አዲስ ዕድል፣ አዲስ ክህሎት! 🚀
⏰ ይህ ወቅት የነገ ዕድልዎን በራስዎ የመወሰን አቅም ያጎናፅፎታል።
🛠️ ቴክኒክና ሙያ ከዕውቀት ገበያ ወደ ሥራው ዓለም የሚያሻግርዎ አስተማማኝ ድልድይ ነው።
👩🏭 በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በመሄድ፣ የሙያ ባለቤት ይሁኑ!
🔥 ነገዎን ዛሬ መስራት ይጀምሩ! 🚀
መስከረም 16/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከግራንድ ግሩፕ ጋር በመቀናጀት በE - Money ላይ ስራ ፈላጊ እና ወጣቶችን ስራ ለማስጀመር የተዘጋጀ መድረክ ተካሄደ።
ግራንድ ግሩፕ የተባለ በድሬዳዋ የመጀመሪያው የሆነ በዲጂታል ማርኬቲንግ እና የበቃ የሰው ሀይል ለኢንዱስትሪዎች አቅራቢ ኢንተርፕራይዝ ሲሆን በለይም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ስራ ፈላጊ ወጣቶች በኢ መኒ ዘርፍ ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረግ ተችሏል።
በቢሮው የስራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከላት ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እንደገለጹት ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ማስቀጠር ላይ የሚቆም አለመሆኑና ዘላቂ የሆነ የሥራ ዕድል መፍጠር ላይ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራና ለዚህም መሰል ኢንተርፕራይዞች በአስተዳደሩ መፈጠራቸውና ወደ ስራ መግባታቸው ትልቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑና በቀጣይም በይበልጥ ተቀራርበው የሚሰሩና አስፈላጊውን ድጋፍ ቢሮው የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 15/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
✨ እንደ እንቁ የሚፈለጉ የሙያተኛ እጆች ✨
🔍 ዙሪያችንን በትኩረት እናስተውል
🏛 በግርማ ሞገሳቸው የሚያስደምሙን ህንፃዎች
🛋 አስደማሚ የቤት ቁሳቁሶች
⚙️ ህይወታችንን የሚያቀሉ ማምረቻ ማሽኖች
👗👞 በውበታቸው የሚያማልሉ አልባሳትና መጫሚያዎች
✋🎨 እነዚህ በጥበበኛ እጅ የሚሠሩ፣ የሚቀረፁ፣ የሚዋቡና የሚዘጋጁ ቁሶች ሁሉ የሙያተኛ እጆች በእጅጉ ይፈልጋሉ
💡 የዕለት ፍላጎታቸውን ለመሙላት፣ ሕይወታቸውን የተሻለ ለማድረግ፣ ጥበብና ውበት የሚለግሰውን ደስታ ለማጣጣም የሚሹ መላ የሰው ዘሮች ፍላጎት ምላሽ የሚያገኘው በጥበበኛ✋ባለእጆች ነው።
• 📚 ሙያ ይሰልጥኑ፣
• 🎭 ጥበብን ይቅሰሙ፣
•🚀 ድንበርና ወሰን ሳያግድዎት እንደ እንቁ ተፈላጊ ይሁኑ! አድራሻችን ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ወደ ኤርፖርት በሚወስደው አስፓልት መንገድ 150 ሜትር ላይ እንገኛለን
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
🚫 የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አቋራጭ መንገድ የለውም❗
✈️ ማንኛውም የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት የሚሰጠው በመንግስት ብቻ ነው። ሥራው በማንኛውም ግለሰብም ሆነ ድርጅት በውክልና አይሰራም።
💻 አገልግሎቱ በቴክኖሎጂ ታግዞ ቀልጣፋ፣ ምቹ፣ ፈጣን፣ ፍትሃዊ እና ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን ተደርጓል።
✅ በስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን፦
1️⃣ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (lmis.gov.et) ላይ በነፃ መመዝገብ፣
2️⃣ የሚሰጠውን ስልጠና መውሰድ እና
3️⃣ አስፈላጊውን መረጃ ማሟላት ያስፈልጋል።
⚠️ ከዚህ ውጪ የትኛውም የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አማራጭም ሆነ አቋራጭ መንገድ የለውም።
🛡️ ራስዎን ከአጭበርባሪዎችና ህገወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች ይጠብቁ!
✈️ ህጋዊና ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት፣ ለሁለንተናዊ ተጠቃሚነት!
መስከረም 15/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+7
‹‹ሁሉም የኮሌጁ ፈጻሚ አካላት ጥራት ባለው እቅድ በመመራት፣ የተቋሙን የስራ ባህል በማሳደግና በማጠናከር በሁሉም ዘርፍ ኮሌጁ ላስቀመጠው ራዕይና ተልዕኮ መሳካት በኃላፊነትና በትጋት መስራት ይጠበቅበታል።››
ወ/ሮ ትግስት በዙ
የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽ ም/ዲን
#ዜና|በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ውስጥ ለሚገኙ ፈጻሚ አካላት ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበው ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቀቀ፡፡
በስልጠናው ማጠቃለያ ወቅት በመገኘት መድረኩን የዘጉት የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽ ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ እንዳሉት ኮሌጃችን እንደ ምስራቅ ኢትዮጵያ የLeadership development and certification center ለማቋቋም መመረጡ ትልቅ ስኬት ነው።
ስለዚህ ሁሉም የኮሌጁ ፈጻሚ አካላት ጥራት ባለው እቅድ በመመራት፣ የተቋሙን የስራ ባህል በማሳደግና በማጠናከር በሁሉም ዘርፍ ኮሌጁ ላስቀመጠው ራዕይና ተልዕኮ መሳካት በኃላፊነትና በትጋት መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
ለሁለት ቀናት ለፈጻሚ አካላት ሲሰጥ የነበው ይህ ስልጠና በዋናነት Organizational culture and planning፣Cooperative management ፣Change management፣ Institutional leadership and ፣Resources management በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠና በመስጠት የኮሌጁን ፈጻሚ አካላት አቅም መገንባት እንደተቻለ በስልጠና ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መስከረም 14/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
🌟 #የሙያ_ስልጠና_ለምን?
📚 ለሥራው ዓለም የሚያዘጋጁዎትን የንድፈ ሀሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ ስልጠና ሙሉና ተፈላጊ ሆነው መውጣት ስለሚያስችልዎ፣
📚 የሥራ ገበያውና ወቅቱ ከሚፈልገው ሙያ ጋር የተጣጣመ እና በከፍተኛ ደረጃ ተፈላጊ የሚያደርግዎትን ስልጠና ስለሚያገኙ፣
📚 ተቀጣሪ ሳሆን ቀጣሪ የመሆን ዕድል ስለሚያጎናጽፍዎ፤
📌 #ማን_ሊሰልጥን_ይችላል?
🎓 ሙያ ራሳቸውን፣ ቤተሰባቸውንም ሆነ ሀገራቸውን መቀየሪያ ዋነኛው መሳሪያ እንደሆነ የገባቸው እና ሙያን ምርጫቸው ያደረጉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት አጠናቃቂዎች፣
🎓 ሙያ ሰልጥነው የራሳቸውን ሥራ ለመጀመር የወሰኑ ሥራ ፈጣሪዎችና የመጪው ዘመን ባለሀብቶች እንዲሁም
🎓 ተጨማሪ ሙያና ክህሎት አግኝተው ሥራቸውን ለማሳደግ፣ ገቢያቸውን ለማስፋት እና መጪውን ዘመን እየዋጁ ራሳቸውን መቀየር ያቀዱ ዜጎች በተለያዩ መርሃ ግብሮች መሰልጠን ይችላሉ፡፡
👉 #ዕድሉ_እንዳያመልጥዎ!
🌠በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ጎራ ይበሉ!በአዲሱ የስለጠና ዘመን መጪውን ዘመን በሙያ ለመዋጀት ቀድመው ይመዝገቡ!
አስቸኳይ ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ (ሜፖ ኮንትራክቲንግ ኤንድ ማኔጅመንት ሰርቪስስ ኃ.የተ.የግ.ማህበር) በ2018 ዓ.ም የፋይናንስ እና የአስተዳደር ኃላፊ እና ካሸር የሥራ መደቦች ላይ በኮንትራት፣ ከሶስት አመት እስከ ስምንት ዓመት የስራ ልምድ ያላቸውን ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
በዚህም መሰረት በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የለማውን የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (E-LMIS) በመጠቀም ከመላ የሀገሪቱ ክፍሎች መስፈርቱን የሚያሟሉ ብቁ ሰራተኞች ይፈለጋሉ።
ስለሆነም የዚህ የሥራ እድል ተጠቃሚ ለመሆን lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ ወረዳ/ቀበሌ የአንድ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር/ labor ID/ ይዛችሁ ከዚህ በታች በተቀመጠው ማስፈንጠሪያ በመግባት ትክክለኛ የትምህርት፣ የስራ እና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎቻችሁን በማሰገባት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
https://forms.lmis.gov.et/midroc/
አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከመስከረም 14 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት ውስጥ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
✨ እንደ እንቁ የሚፈለጉ የሙያተኛ እጆች ✨
🔍 ዙሪያችንን በትኩረት እናስተውል
🏛 በግርማ ሞገሳቸው የሚያስደምሙን ህንፃዎች
🛋 አስደማሚ የቤት ቁሳቁሶች
⚙️ ህይወታችንን የሚያቀሉ ማምረቻ ማሽኖች
👗👞 በውበታቸው የሚያማልሉ አልባሳትና መጫሚያዎች
💍 የመዋቢያ ጌጣጌጦች………..
✋🎨 እነዚህ በጥበበኛ እጅ የሚሠሩ፣ የሚቀረፁ፣ የሚዋቡና የሚዘጋጁ ቁሶች ሁሉ የሙያተኛ እጆች በእጅጉ ይፈልጋሉ
💡 የዕለት ፍላጎታቸውን ለመሙላት፣ ሕይወታቸውን የተሻለ ለማድረግ፣ ጥበብና ውበት የሚለግሰውን ደስታ ለማጣጣም የሚሹ መላ የሰው ዘሮች ፍላጎት ምላሽ የሚያገኘው በጥበበኛ✋ባለእጆች ነው።
• 📚 ሙያ ይሰልጥኑ፣
• 🎭 ጥበብን ይቅሰሙ፣
•🚀 ድንበርና ወሰን ሳያግድዎት እንደ እንቁ ተፈላጊ ይሁኑ!
መስከረም 14/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
💡 ክህሎት የ21ኛው ክፍለ ዘመን መገበያያ ገንዘብ! 💡
🌍 ውድድር በበዛበት ዓለም ስኬት በክህሎት ለተዋቡ እጆች ቅርብ ናት።
🏫 የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እውቀትን ከክህሎት ጋር አሰናስለው እጀ- ወርቅ ባለሙያ እንዲሆኑ ያግዝዎታል።
💼 ይህም በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም የሥራ ገበያ ላይ ስኬታማ ለመሆን በራስ መተማመንን ያጎናፅፋል።
📚✨እውቀትና ክህሎት የማይነጥፍ ፀጋ ነው!
🔧 ሙያ ይሰልጥኑ!
🌟 ነገዎን ብሩህ ያድርጉ!
👉 ወደ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመሄድ ነገዎን ዛሬ ይጀምሩ። 🚀
"የሚደገም ድል፣ የሚጨበጥ ብስራት፣ ህዳሴ ግድብ!"
"ግድባችን ተጠናቅቋል፣ የጠላቶቻችን ሴራ በኢትዮጵያዊ አርበኝነት እሳት ተቃጥሎ ከስሟል!"
ዛሬ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አጠቃላይ ሰራተኞች ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ የድጋፍና ደስታቸውን የገለጡበትን ሰልፍ አካሄዱ።
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
🎉 #የሙያ_ባለቤት_ሆነው_ነገገዎን_ብሩህ_ለማድረግ_አቅደዋል? ✨
በአዲሱ የስልጠና ዘመን በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት ነባርና አዳዲስ ሰልጣኞችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል። 🚀
ይህም ለወጣቶች፣ ለሙያ ስልጠና ፈላጊዎች እና ወቅቱ በሚፈልጋቸው ሙያዎች ተክነው ነጋቸውን ብሩህ ለማድረግ ላቀዱ ባለራዕዮች ወርቃማ ዕድል ነው።🌟
🌟 #የሙያ_ስልጠና_ለምን?
📚 ለሥራው ዓለም የሚያዘጋጁዎትን የንድፈ ሀሳብ ብቻ ሳይሆን በተግባራዊ ስልጠና ሙሉና ተፈላጊ ሆነው መውጣት ስለሚያስችልዎ፣
📚 የሥራ ገበያውና ወቅቱ ከሚፈልገው ሙያ ጋር የተጣጣመ እና በከፍተኛ ደረጃ ተፈላጊ የሚያደርግዎትን ስልጠና ስለሚያገኙ፣
📚 ተቀጣሪ ሳሆን ቀጣሪ የመሆን ዕድል ስለሚያጎናጽፍዎ፤
📌 #ማን_ሊሰልጥን_ይችላል?
🎓 ሙያ ራሳቸውን፣ ቤተሰባቸውንም ሆነ ሀገራቸውን መቀየሪያ ዋነኛው መሳሪያ እንደሆነ የገባቸው እና ሙያን ምርጫቸው ያደረጉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት አጠናቃቂዎች፣
🎓 ሙያ ሰልጥነው የራሳቸውን ሥራ ለመጀመር የወሰኑ ሥራ ፈጣሪዎችና የመጪው ዘመን ባለሀብቶች እንዲሁም
🎓 ተጨማሪ ሙያና ክህሎት አግኝተው ሥራቸውን ለማሳደግ፣ ገቢያቸውን ለማስፋት እና መጪውን ዘመን እየዋጁ ራሳቸውን መቀየር ያቀዱ ዜጎች በተለያዩ መርሃ ግብሮች መሰልጠን ይችላሉ፡፡
👉 #ዕድሉ_እንዳያመልጥዎ!
🌠በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ጎራ ይበሉ!በአዲሱ የስለጠና ዘመን መጪውን ዘመን በሙያ ለመዋጀት ቀድመው ይመዝገቡ!
መስከረም 11/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 በጀት አመት የአፈፃፀም ሪፖርት እና የ2018 በጀት አመት መሪ እቅድ ለተቋሙ ሰራተኞች ቀርቦ ውይይት ተካሄደ::
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት በቅድሚያ ለ2018 ዓ.ም የስራ ዘመን እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን ይህ የተዘጋጀው የሪፖርትና እቅድ መድረክ ኮሌጁ ባሳለፍነው በጀት አመት የነበረውን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ ለሰራተኛው ቀርቦ እንዲገመገም ከማድረግ በተጨማሪም የ2018 በጀት አመት የተቋሙን መሪ እቅድ ለአጠቃላይ ሰራተኛው ለማስተዋወቅና ሁሉም ፈፃሚ ከተቋሙ መሪ እቅድ አኳያ ተግባርና ሀላፊበቱን እዲከውን ለማስቻል እንደሆነም ገልፀዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም በቀጣይ የዝግጁነት ምዕራፍ ቀናት የተቋሙ መሪ እቅድ ወደታች እስከ ፈፃሚዎች ድረስ ካስኬድ የሚደረግ መሆኑን ገልፀው መሪ እቅዱ አንዴ ተዘጋጅቶ የሚቀመጥ ሳይሆን እንደ አስፈላጊቱ ማሻሻዎች የሚደረጉበት አግባቡ እንደሚኖርም ጠቅሰዋል::
የተቋሙ የአፈፃፀም ሪፖርት እንዲሁም የ2018 በጀት አመት መሪ እቅዱን ለሰራተኛው ያቀረቡት የኮሌጁ የእቅድና በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ስራ ክፍል ሀላፊ አቶ አለማየሁ ብርሃኑ ሲሆኑ ባሳለፍነው በጀት አመት በኮሌጁ በእቅድ ተይዘው የተከናወኑ ቁልፍ ቁልፍ ተግባራትን ለመድረኩ ተሳታፊዎች በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም በ2018 በጀት አመት ኮሌጁ አዲሱን የዘርፉ እሳቤን ጨምሮ ነባራዊ ሁኔታዎችን መነሻ በማድረግ ያዘጋጀውን መሪ እቅድ ለተቋሙ ሰራተኞች አስተዋውቀዋል::
በመድረኩ በቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርትና መሪ እቅድ ላይ በተሳታፊዎች ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን በቀጣይ እንደ ተቋም ለሚኖረው እንቅስቃሴ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦች የተኘበት መድረክም ነበር::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
መስከረም 9/2018 ዓ.ም
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
