ar
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 068
المشتركون
+424 ساعات
-27 أيام
+230 أيام
أرشيف المشاركات
ዛሬ በተጀመረው 4ኛው ሀገር ዓቀፍ የክህሎት ውድድር ላይ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች የቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፣ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እና በቢሮው የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ዳይሬክተር አቶ አሚን አብዱላሂ ውድድሩ በሚካሄድ በት ስፍራ በመገኘት ተወዳዳሪዎችን አበረታተዋል። በዚህ ውድድር በአስር የክህሎት ተወዳዳሪ ሰልጣኝ ተማሪዎች፤ በሁለት አሰልጣኝ መምህራን የተዘጋጀ አንድ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር፤ በአንድ አሰልጣኝ መምህር እና በአንድ ኢንተርፕራይዝ የተዘጋጁ ቴክኖሎጂዎች የድሬዳዋ አስተዳደርን ወክለው የሚወዳደሩ ይሆናል። ቢሮው ለተወዳዳሪዎች መልካም እድል ይመኛል! የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 27/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ

photo content
+4

#አሁን #Happening_Now 4ኛው ሀገር ዓቀፍ የክህሎት ውድድር የመክፈቻ ፕሮግራም
+7
#አሁን #Happening_Now 4ኛው ሀገር ዓቀፍ የክህሎት ውድድር የመክፈቻ ፕሮግራም

#አሁን #Happening_Now 4ኛው ሀገር ዓቀፍ የክህሎት ውድድር የመክፈቻ ፕሮግራም
+5
#አሁን #Happening_Now 4ኛው ሀገር ዓቀፍ የክህሎት ውድድር የመክፈቻ ፕሮግራም

እንኳን ለ84ኛው የዐርበኞች (የድል) በዓል አደረሳችሁ። ቀደምት እናትና አባቶቻችን ነጻነትን በደም አስከብረው ሀገር አውርሰውናል። በዚህም እንኮራለን። እነዚህ ቀደምት ዐርበኞች በከፈሉት ዋጋ ዛሬ ቀ
እንኳን ለ84ኛው የዐርበኞች (የድል) በዓል አደረሳችሁ። ቀደምት እናትና አባቶቻችን ነጻነትን በደም አስከብረው ሀገር አውርሰውናል። በዚህም እንኮራለን። እነዚህ ቀደምት ዐርበኞች በከፈሉት ዋጋ ዛሬ ቀና ብለን በነጻነት ዐደባባይ እንድንራመድ አድርገውናል። በድህነታችንና በኋላ ቀርነታችን ምክንያት ግን ነጻነታችን ሙሉ ሊሆን አልቻለም። ነጻነታችን የተሟላ እንዲሆን ዛሬ ኢትዮጵያ የሁለተኛውን ዘመን ዐርበኞች ትፈልጋለች። የሁለተኛው ዘመን ዐርበኞች ኢትዮጵያን ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና በማድረስ ነጻነቷን ሙሉ የሚያደርጉ ናቸው። በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በማኅበራዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መስኮች በሚኖረው ሰላማዊ ጦርነት፣ ድህነትንና ኋላ ቀርነትን ታግለው የሚያሸንፉ ዐርበኞች ናቸው። የዚህ ዘመን ዐርበኝነት ትጥቁ ዕውቀት፣ ክህሎት እና ዲሲፕሊን ነው። ወኔው የሀገር ፍቅር፣ ቆራጥነት እና ንጽሕና ነው። ግቡ የኢትዮጵያ ብልጽግና ነው። ኢትዮጵያን ታላቅ ለማድረግ ሁለቱም ዓይነት ዐርበኞች ያስፈልጋሉ። ይህ ዘመን ደግሞ ይበልጥ ሁለተኛውን አርበኝነት ይሻል። ይሄ ቀን የመጀመሪያውን ዐርበኝነት መዘከሪያ፤ ለሁለተኛው ዐርበኝነት ደግሞ መሰረት ማፅኛ እንደሚሆን ተስፋዬ የላቀ ነው። መልካም በዓል ይሁን! ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!! ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ! ሚያዝያ 27 ቀን 2017 ዓ.ም

የገጠር ስራ እድል ፈጠራ ዘርፉን ለማጠናከር በአስተዳደሩ ገጠር ቀበሌዎች ተደራጅተው የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻል ፕሮጀክት(LLRP) ድጋፍ ሊደረግላቸው የተለዩ ስራ ፈጣሪ በሴቶችና በወጣቶች የተደራጁ ኢንተርፕራይዞችን ሁኔታ የሚመለከት የመስክ ጉብኝት ተካሄደ፡፡ ይህ የመስክ ጉብኝት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ከዚህ ቀደም በአጠቃላይ የሥራና ክህሎት ስራዎች ተደራሽነት ጋር በተያያዘ ተቀናጅቶ እና ተናብቦ የገጠሩን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች በሚሰሩበት አግባብ ላይ ከገጠር ወረዳ አመራሮች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ተከትሎ የተደረገ ሆኗል። በተለይም በገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ትኩረት በመስጠት  የገጠር ስራ ዕድልን ስርዓትን ከዚህ በፊት የነበሩ ክፍተቶችን ማረምና መለወጥ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መወያየታቸው ይታወሳል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 25/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+2

የኢንዱስትሪዎችን ፍላጎት መነሻ አድርገው የሚሰጡ የሙያ ስልጠናዎች የሚስተዋለውን የሰለጠነ የሰው ሀይል እጥረት መቅረፍ እንደሚያስችሉ ተገለፀ:: ሚያዚያ 25/2017 ዓ.ም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት በኢንዱስትሪው የሙያ ፍላጎትን አስመልክቶ በተዘጋጀው የዳሰሳ ጥናት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ:: መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት "በቀጣይ እንደ ተቋም በሚኖረን ትግበራና ፕሮጀክቱም ትኩረት ከሚሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ አንደኛው የኢንዱስትሪውን ፍላጎት ምንነትን ተገንዝቦ ስልጠናዎችን በዛ አግባብ መስጠት በመሆኑ ይህን የፍላጎት ደሰሳ እዲዘጋጅ እድርገናል" ያሉ ሲሆን አክለውም በቀጣይ እንደ ተቋም በምናዘጋጀው የ10 አመት እስራቴጂክ እቅድ ላይ መሰል ጥናቶች እንደ ግብዓት የምናካትት ይሆናልም ብለዋል:: በኢንዱስትሪዎች ላይ የፍላጎት ዳሰሳ ከተደረገባቸው ነጥቦች አንፃር የተገኙ ውጤቶች፣ የተለዩ ክፍተቶችን በአጭር ጊዜና በረጅም ጊዜ ለመሙላት በሚያችል መልኩ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ መዘጋጀቱን የገለፁት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አክለውም ይህን ጥናት እንደ መነሻ መሆኑን እና በቀጣይም የትኩረት ማዕከል በሆኑት ዘርፎች ላይ በልዩነትና በጥልቀት መሰል ጥናቶችን በማካሄድ ከኢንዱስትሪዎች ጋር ውጤታማ ስራዎችን ለማከናወን በእቅድ መያዙን ገልፀው በዚህ የፍላጎት ዳሰሳ ላይ ለተሳተፉ በሙሉ በኮሌጁ ስም ላቅ ያለ ምስጋናም አቅርበዋል:: በእለቱ የተዘጋጀው የኢንዱስትሪዎች የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሰነድ በአሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ እና እሰልጣኝ መ/ር ነዋይ ይልማ አማካኝነት በመድረኩ ተሳታፊ ለነበሩ ባለድርሻ አካላት የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሰነድም በኢንዱስትሪዎች ውስጥ የሚገኙ ባለሙያዎች ካላቸው የትምህርት ዝግጅት አንስቶ ከሚሰሩት ስራ አኳያ ያላቸው ተዛማችነት በዝርዝር የዳሰሰ ሲሆን በርካታ መሰል የተለዩ ክፍተቶችም በቀረበው ሰነድ ላይ ተመላክተዋል:: በመድረኩ በቀረበው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናትን መነሻ በምድረግም ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ገንቢ የሆነ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ለሰነዱ ተጨማሪ ግብአቶችም የተገኙበት መድረክ ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን

የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሚገኙ ሰራተኞች እና አመራሮችን በማሳተፍ ትግበራው በንቅናቄ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ። በዚህም ከሚያዚያ 21/2017 ዓ.ም ጀምሮ የቢሮው አመራሮች እና ሰራተኞች ምዝገባ በማድረግ የዲጂታል ኢትዮጵያ ቤተሰብነታቸውን ማረጋገጥ ችለዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 24/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

በአገር አቀፍ ደረጃ በተመረጡ አስፈፃሚ ተቋማት ላይ ተግባራዊ ለማድረግ በታሰበው የፕሮግራም በጀት አዘገጃጀትና አተገባበር ዙሪያ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ለሚገኙ የቡድን መሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ። የስልጠና መድረኩ በቢሮው የዕቅድ በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት አማካኝነት ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን በዚህም በቀጣይ የጀት አጠቃቀም ውጤታማነት ለማረጋገጥ የሚያስችል አቅም የሚፈጥሩ ሰፊ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 24/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

በድሬዳዋ አስተዳደር እየተካሄደ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ቀጥሎ የአውቶሞቲቭ አሰልጣኝ መምህራን በደረጃ አምስት አውቶሜካኒክስ ሙያ በመመዘን ላይ መሆናቸው ተገለጸ።

photo content
+7

#ዜና| በአስተዳደሩ የሚታየውን የስራ  አጥ ቁጥር ለመቀነስ የድርጅት ባለቤቶች ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ተገለፀ :: #Diretv አማርኛ ሚያዚያ 24/2017 ከፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በአለም ባንክ ድጋፍ በአስተዳደሩ የሚተገበረው ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የ3ተኛው ዙር  ትግበራ  በፕሮጀክቱ  ስር  የታቀፉትን ወጣቶች ከድርጅት ባለቤቶች ጋር  ለማስተሳሰር በሚያስችል ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሂዷል :: የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው  በወቅቱ  ሲናገሩ  ፕሮጀክቱ  ለሦስተኛ ዙር እየተተገበረ እንዳለ ጠቅሰው  ከዚህ በፊት በአንደኛውና በሁለተኛው  ዙር  በብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ በርካታ ወጣቶች ከስራ አጥነት ተላቀው የስራ ባለቤት እንደሆኑ አንስተዋል ::  አክለውም  አሁንም በዚህ ሦስተኛው ዙር ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ከዘጠኝ መቶ ( ከ 900 ) በላይ ወጣቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና ወስደው ወደ ተግባር ልምምድ ለማሰማራት ዝግጅት ጨርሰናል ብለው አሁን ከእናንተ የድርጅት ባለቤቶች ጋር  ልምምድ እንዲያደርጉና ሞያ ቀስመው  ወይ እናንተው  ጋር ተቀጥረው እንዲሰሩ  አለያም ሌላ ቦታ ተቀጥረው የስራ ባለቤት ለማድረግ የተመቻቸ የውይይት መድረክ መሆኑን ለመድረኩ ተሳታፊ ባለሀብቶች ተናግረዋል። ስለሆነም በአስተዳደሩ የሚታየውን የስራ አጥ ቁጥር ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ የእናንተ የድርጅት ባለቤቶች ሚና ከፍተኛ ነው በማለት ሀላፊው ጨምረው ገልፀዋል፡፡ በወቅቱም  ወጣቶቹ  የተግባር ልምምድ በሚያደርጉበት ድርጅት ሲሄዱ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ከድርጅቱ ምን ይጠበቃል ፤ ከወጣቶችስ ምን ያስፈልጋል የሚሉና አጠቃላይ ይህ ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ምንነት እና አስፈላጊነት ለመድረኩ  ፅሁፍ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። በመጨረሻም  የአስተዳደሩ  የስራና ክህሎት ቢሮ  በሦስቱም ዙር የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ  ፕሮጀክት ሲተገበር  በራቸውን ከፍተው ወጣቶቹ  የተግባር  ስራ  ልምምድ እንዲያደርጉ  ትብብር  ላደረጉ  ባለሀብቶች ምስጋና  አቅርቧል :: ዘጋቢ ፦ ነጃት ተገኔ ምስል:- ከቢሮው የህዝብ ግንኙነት

photo content
+9

ለንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር ተወዳዳሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የስራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት በ2017 ዓ.ም ለሚደረገው ብሩህ የንግድ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር መወዳደር የሚፈልጉ እንዲመዘገቡ በማስታወቂያ አሳውቆ መመዝገቡ ይታወሳል በዚህም ለውድድሩ የሚያስፈልጉ መመሪያዎችን እና አሰራሮችን በማዘጋጀት የተወዳዳሪዎችን ሰነድ በመመርመርና በመለየት ስልጠና ሰጥቷል፤ ውድድሩ የሀሳብ  ስለሆነ ተወዳዳሪዎች ከሀሳብ ደረጃ ወጥተው ዕውን የሚያደርጉበትን ብቃት እንዲያገኙ ድጋፍ የሚደረግላቸው ሲሆን ድጋፉም ማሰልጠን፣  መሸለምና  ማብቃት በሚል ሶስት ደረጃዎችን ያልፋል፤ በመሆኑም በዋናነት በየዘርፉ የሚታዩ ዋና ዋና ተግዳሮቶችን መቅረፍ ላይ ያተኮሩ አዳዲስ የንግድ ፈጠራ ሀሳቦችን ማመንጨት የሚችሉበትን እና የአካባቢያቸውን ጸጋዎች ለይተው በፈጠራ ሀሳብ በመደገፍ ጥቅም ላይ ማዋልን እንዲያዳብሩ ስልጠናው መሰጠቱን የስራ ዕድል ፈጠራ ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ ቤተልሔም ድንበሩ ተናግረዋል፡፡ በዚህም ውድድሩ ተወዳዳሪዎች ከሀሳብ ደረጃ ወጥተው ዕውን የሚያደርጉበትን ብቃት እንዲያገኙ ድጋፍ የሚያገኙበትን ሁኔታ የሚያመቻች በመሆኑ አሸናፊ የሚሆኑ በቀጣይ በመሸለምና በማብቃት ሂደት ውስጥ የሚበረታቱ እንደሚሆን ገልጸዋል፤ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

በአገራችን ለ50ኛ ጊዜና በዓለማችን ለ136ኛ ጊዜ ለሚከበረው ዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን ክብረ በዓል የሠራተኛና አሰሪዎች ማህበራት፣ ፌደሬሽን እና ኮንፌደሬሽን አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው አካላት በተገኙበት ተከበረ፡፡ በመድረኩ የኢሰማኮ የምስራቅ ኢትዮጵያ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ እንዳለ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ለዜጎቿ ማህበራዊ ፍትህ ቅድሚያ በመስጠት ኢኮኖሚያዊ ደረጃቸው ምንም ይሁን ምን ሁሉም ሰራተኞች የተከበረ እና አስተማማኝ ህይወት እንዲኖራቸው ማድረግ ትችላለች፤ መንግስት ከዚህ በፊ ያነሳናቸውን ጥያቄዎቻችንን ተገቢነት ተቀብሎ ለሚመለከታቸው አካላት አቅጣጫ ሰጥቶ እንደነበር አስታውሰው ምላሽ ያገኙ ጉዳዮች መኖራቸው የሚያስመሰግነው ሆኖ ምላሽ ያላገኙ ጥያቄዎች ታይተው ምላሽ ይሰጠን ዘንድ እንጠይቃለን ብለዋል፡፡ አክለውም አለም ዓቀፍ የሰራተኞች ቀን ሜይ ዴይ በሚከበርበት ዕለት ለመንግስት ምላሽ እንዲሰጥባቸው ከኑሮ ውድነቱ ጋር በተያያዘ የሥራ ግብር ምጣኔ እንዲስተካከል፤ ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል የሚወስን የደመወዝ ቦርድ እንዲቋቋም፤ በተቋማት የስራ ደህንነትና ጤንነትን በተመለከተ ክትትሉ እና ቁጥጥሩ ሊጠናከር እንደሚገባ በማሳሰብ አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ለዘመናት ሲንከባለሉ የቆዩትን ችግሮቻችንን በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሠላም ለማምጣት እያደረገ ያለውን ጥረት መላው ሰራተኛ እንዲደግፍ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ  አቶ ሮቤል ጌታቸው የዘንድሮው ሜይዴይ የሚከበረው በዓለም አቀፍ ደረጃ “በአምራች ኢንዱስትሪዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምቹ  የሥራ ሁኔታ ለማህበራዊ ፍትህ” በሚል መሪ ቃል ቢሮው ሰላማዊ እንዱስትሪና የኢንዱስትሪ ባህል ግንባታ እንዲረጋገጥ፣ ምቹ የስራ ቦታ እንዲፈጠርና ሠራተኛው እና አሰሪው በነጻነት የመደራጀት መብት በማረጋገጥ ሰራተኛው ከአሰሪው ጋር የመመካከር እንዲሁም እንዲደራደርና ግዴታውን እየተወጣ መብትና ጥቅሙ እንዲከበር የምክክር ባህል እንዲጎለብት ከምስራቅ ኢትዮጵያ ኢሠማኮ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ጋር በጋራ በማቀድ እና ሰራዎችን በመገምገም እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በተለይ በአስተዳደሩ በሚገኙ የማምረቻ እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሚገኙ ሠራተኞች በማህበር እንዲደራጁ ቢሮው ከምስራቅ ኢትዮጵያ ኢሠማኮ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልና ከዚሁ ጎን ለጎን የሥራ ቦታ ደህንነትና ጤንነትን በማስጠበቅ ረገድ የወጡ የሕግ ማዕቀፎችን ተግባራዊነት ለማረጋገጥ በሁሉም እንዱስትሪዎችና ድርጅቶች ጥምር የሙያ ድህንነት እና ጤንነት ኮሚቴ እንዲደራጅ ከማድረግ ጅምሮ በዘርፉ የባለሙያ እጥረትን ለመቅርፍ ባለፈው አንድ ዓመት በአጫጭር ስልጠና 31 የሚሆኑ ባለሙያዎችን ማፍራት መቻሉን አስታውሰው በትብብር ለመሠራት የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል በድሬዳዋ አስተዳደር የተጀመሩ የከተማዋን ሁለንተናዊ ብልፅግና የማረጋገጥ ተግባራት እንዲሳኩ ሠራተኛው ተገቢውን አስተዋጽኦ እንዲያደረግ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የሥራና ክህሎት  ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ