cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

አዲስ መረጃ ሰበር ዜና Addis Mereja

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
3 677
المشتركون
-1524 ساعات
-377 أيام
+1 10130 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ወቀሳ ቀረበበት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት፣ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን በክልሉ ያካሄደው የመጀመሪያ ዙር የምክክር ተሳታፊዎች ልየታ ሂደት "ሙስሊሙን ያገለለ" እና "የክልሉን እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከግምት ውስጥ ያላስገባ" ነው በማለት ወቅሷል። ከፍተኛ ምክር ቤቱ ይህንኑ ቅሬታውን ለኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በደብዳቤ ማሳወቁን ገልጧል። የክልሉ አብዛኛው ሕዝብ ሙስሊም መኾኑ ይታወቃል ያለው ከፍተኛ ምክር ቤቱ፣ ኮሚሽኑ አሠራሩን አስተካክሎ ምክር ቤቱ በአገራዊ ምክክሩ የሚሳተፉትን ሰዎች መልምሎ እንዲያቀርብና ሙስሊሙን ኅብረተሰብ ያሳተፈ ምክክር እንዲኾን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለኮሚሽኑ ጥያቄውን እንዲያቀርብለት ጠይቋል። የክልሉ ከፍተኛ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት፣ የኮሚሽኑ አሠራር ሳይስተካከል ኹኔታው ከቀጠለ ግን ለአገራዊ ምክክሩ እውቅና አልሰጥም በማለት አስጠንቅቋል።
إظهار الكل...
👍 2
በቁጥጥር ስር ውሏል! አየር መንገድ አካባቢ የተነሳው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል! በአዲስ አበባ ቦሌ ኤርፖርት አካባቢ ዛሬ ከቀኑ 9፡41 ላይ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል። የእሳት አደጋው በኮሚሽን ባለሞያዎች፣ በአየር መንገዱ የእሳት አደጋ ሰራተኞች እና ሌሎች የፀጥታ ኃይሎች ባደረጉት ርብርብ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሞያ አቶ ንጋቱ ማሞ በተለይ ለኢቢሲ ሳይበር ገልፀዋል። አደጋው ከአየር መንገድ ግቢው ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የለውም ያሉት አቶ ንጋቱ  በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገፆች እና ሚዲያዎች የእሳት አደጋው በአየር መንገዱ ውስጥ እንደተከሰተ አድርገው የሚያሰራጩት ዘገባ ፍፁም ከእውነት የራቀ መሆኑን አረጋግጠዋል። አደጋው በአንድ የድንገተኛ እሳት አደጋ ባለሞያ ላይ ቀላል ጉዳት ማድረሱን አቶ ንጋቱ ጠቁመዋል።
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
ላሊበላ ተኩስ‼️ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ላሊበላ ከተማ ዙሪያ ዛሬ ጠዋት ጀምሮ ከባድ የተባለ የተኩስ ልውውጥ መካሄዱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀውልኛል። በተለይ በአየር ማረፊያው አቅጣጫ ከባድ የተኩስ ልውውጥ ነበር ብለዋል። በተኩሱ ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰ አይታወቅም ብለዋል።
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
በመዲናዋ የድምጽ ብክለት ፅንስ እስከማጨናገፍ ድረስ ጉዳት እያስከተለ ነው ተባለ‼️ በአዲስ አበባ ከተማ የድምጽ ብክለት በማህበረሰቡ ላይ ጉዳት እያስከተለ መሆኑን የአዲስ አበባ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ። ባለስልጣኑ ከብዙ ምንጮች የሚነሱ ከቁጥጥር ውጭ የሆኑ ከፍተኛ ድምጾች በህብረተሰቡ ላይ አለመረጋጋት፣ ደስታ ማጣትና እና ሌሎች የጤና እክሎችን እያስከተሉ መሆኑን ለአራዳ ገልጿል። ብክለቱ የመስማት ችግርን፣ አለመግባባትን፣ የደም ግፊት፣ የአዕምሮ ህመም፣ በእርጉዝ ሴቶች ላይ ደግሞ ፅንስ ማስወረድ ችግርና የጤና እክል እያስከተለ እደሚገኝ ጠቁሟል። ከመገበያያ ስፍራዎች፣ ከሆቴሎች፣ ከሃይማኖት ተቋማት፣ ከስፖርት ሜዳዎች፣ ከሙዚቃ ማጫዎቻና ሌሎች ስፍራዎች የሚወጡ ድምጾች ለድምጽ ብክለት መንስኤ ናቸው ነው የተባለው። ደካማ የሆነው የመዲናዋ የግንባታ ዲዛይንም ለድምጽ ብክለት ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውም አንስቷል።
إظهار الكل...
👍 3
በቁጥጥር ስር ውሏል! የአሶሳ ዩኒቨርስቲ ተማሪ በነበረችው ደራርቱ ለሜሳ ግድያ ወንጀል የተጠረጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ። የወረዳ አንድ  ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር በላቸው ፈረደ እንደገለጹት የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸው በአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ልዩ ቦታው ሰላም ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ዕለቱ ረቡዕ ግንቦት 07/2016 ዓ/ም ከጧቱ በግምት 2:45 ላይ በሟች እና በተጠርጣሪው መካከል በተፈጠረው በሀሳብ ያለመግባባት ምክንያት በአሰቃቂ ሁኔታ ጀርባዋ ላይ  በጩቤ በመውጋት የተማሪዋ ህይወት ሊያልፍ ችሏል ሲሉ ተናግረዋል። ምክትል ኮማንደሩ አክለውም ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ወንጀሉን የፈጸመውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ የሚገኝ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ የምርመራ ውጤቱን በአጭር ጊዜ ለህዝብ እንደሚገለጽም ተናግረዋል። በመጨረሻም የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ከዩኒቨርስቲው ግቢ ውጪ እና ተጠርጣሪው ከአዲስ አበባ ዱከም ከተማ አቋርጦ ወደ አሶሳ ከተማ ለስራ ጉዳይ በመምጣት የወንጀል ድርጊት የፈፀመ ሲሆን ነገር ግን በአንዳንድ ማህበራዊ ሚድያዎች ድርጊቱ የተፈጸመው በግቢ ውስጥ ነው በሚል የሚሰራጨው እና የብሔር ግጭት አስመስለው የሚወራው ፍጹም ከእውነት የራቀ እና ሁለቱም የአንድ ብሔር ተወላጅ እንዲሁም በጓደኝነት አብረው እየኖሩ የነበሩ መሆኑን ኃላፊው ገልጸዋል። አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 ማስታወቂያና ጥቆማ 👇መቀበያ https://t.me/wasumohammed
إظهار الكل...
👍 16👏 4🔥 3
Photo unavailableShow in Telegram
ቢጂአይ-ኢትዮጵያ ለፐርፐዝ ብላክ የተከፈለውን የቀብድ ክፍያ በመመለስ በፍርድ ቤት የጀመረው ክስ እንዲቋረጥ መደረጉ አስታወቀ ቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና ፐርፐዝ ብላክ በፍርድ ቤት መር አስማሚ በኩል አለመግባባታቸውን በስምምነት መፍታታቸው ታዉቋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሁለቱ ወገኖች መካከል የተፈፀመውን ስምምነት አፅድቆ ክሱን በመዝጋት እግዱም እንዲነሳ ማዘዙ ለማወቅ ተችሏል። በስምምነቱ መሰረት ቢጂአይ-ኢትዮጵያ የተከፈለውን የቀብድ ክፍያ ለፐርፐዝ ብላክ መመለሱን ያስታወቀ ሲሆን ፐርፐዝ ብላክ በፍርድ ቤት የጀመረው ክስም ተቋረጦ እግዱ መነሳቱን ገልጿል። via:—Capital አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 ቤተሰብ❤ በቅንነት ሰብስክራይብ👇       https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g ማስታወቂያና ጥቆማ 👇መቀበያ https://t.me/wasumohammed
إظهار الكل...
👍 8 2🔥 1🤯 1💩 1
Photo unavailableShow in Telegram
በጋምቤላ ክልል ግንቦት 3/2016 በኢታንግ ወረዳ ማኮት ቀበሌ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ የጀመረው  ግጭት እስካሁን 7 ስውች ሲገደሉ 11 ስዎች ቆስለው ጋምቤላ ሆስፒታል ገብተዋል። 3 የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት መገደላቸውን ተከትሎ አሁን ግጭቱ ከሯል ብለዋሌ። የክልሉ መንግስትም ሁኔታወችን ከማየት የዘለለ ምንም አይነት ስራ እየስራ አይደለም ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል(አዩዘሀበሻ)። =================== For more upcoming news Join now and invite to others👇👇👇 https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s የውስጥ መስመር👉  t.me/ayulaw
إظهار الكل...
👍 7 3
Photo unavailableShow in Telegram
ድሮን❗ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ ጎሎ በምትባል ቀበሌ ትናንት ከሰዓት አካባቢ ሁለት ጊዜ የድሮን ጥቃት መፈፀሙ ተሰምቷል። እስካሁን የተረጋገጠ ነገር ባይኖርም ከ15 በላይ የሆኑ ሰዎች በጥቃቱ ሳይሞቱ አይቀርም ብለዋል(አዩዘሀበሻ)። =================== For more upcoming news Join now and invite to others👇👇👇 https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s የውስጥ መስመር👉  t.me/ayulaw
إظهار الكل...
👍 6
Photo unavailableShow in Telegram
ትናንት በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ እና በኦሮሞ ብሄርሰብ ልዩ ዞን ጋር በሚዋስንበት ቦታ በአንፆኪያ በ08 ቀበሌ እና በኦሮሞ ብሄርሰብ በአርጡማ ፉርሲ በሚዋስኑ ቀበሌ ልዩ ስሙ ፌጮ በሚባል ቦታ ለስአታት የዘለቀ ውጊያ እንደነበር የአዩዘሀበሻ ምንጮች ገለፁ። በዚህ ግጭት ከአንፆኪያ በኩል  አምስት ሰው ሞቷል 3ሰው ቆስሏል ብለዋል፣ከኦሮሞ ብሄርሰብ በኩል ያለው ጉዳት በውል ባይታወቅም ጉዳት ሳይደርስ አይቀርም ብለዋል። አሁን ተኩሱ ቆሟል ብለዋል። በዚህ አካባቢ በተደጋጋሚ የሚፈጠሩ ግጭቶች በየጊዜው በርካታ የሰው እየጠፋ ይገኛል[አዩዘሀበሻ]። =================== For more upcoming news Join now and invite to others👇👇👇 https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s የውስጥ መስመር👉  t.me/ayulaw
إظهار الكل...
👍 6😢 2🤯 1
Photo unavailableShow in Telegram
በራያ ኦፍላ ኮረም እንዲሁም በራያ አላማጣ ወረዳ የትግራይ ታጣቂዎች ወደ አካባቢው መንቀሳቀሳቸውን ተከትሎ በእነዚህ አካባቢዎች ትምህርት ከተቋረጠ ሳምንታት ተቆጥረዋል። አሁን ላይ የደረሰኝ መረጃ እንደሚያሳየው የ12ኛ ተፈታኝ የሆኑ ተማሪዎች ወልዲያ ዩኒቨርስቲ ገብተው ቀሪውን ትምህታቸወን እንዲያጠናቀቁ ሊደረግ መሆኑን የአዩዘበሀሻ ምንጮች ገልፀዋል(አዩዘሀበሻ)። =================== For more upcoming news Join now and invite to others👇👇👇 https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s የውስጥ መስመር👉  t.me/ayulaw
إظهار الكل...
👍 5🔥 2🤯 2