ar
Feedback
የወሎ ድምፅ/Voice Of Wollo

የወሎ ድምፅ/Voice Of Wollo

الذهاب إلى القناة على Telegram

በዚህ የቴሌግራም ቻናል ትክክለኛና ጠቃሚ የሆኑ አጠቃላይ በወሎ ፖለቲካዊ፣ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁነቶችንን እናቀርባለን። የቻናላችን አባል ይሁኑ

إظهار المزيد
5 803
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
የአማራ ክልላዊ መንግስት 2 የፀጥታ ሀላፊዎችን አሰናበተ። ____ የአማራ ክልል መንግስት የክልሉን የፀጥታ ሁኔታ ከገመገመ በኋላ ሀላፊነታቸውን ትተው ከፅንፈኞች ጋር በመሆን ቃለ ማሃላቸውን ክደው ሀ
+2
የአማራ ክልላዊ መንግስት 2 የፀጥታ ሀላፊዎችን አሰናበተ። ____ የአማራ ክልል መንግስት የክልሉን የፀጥታ ሁኔታ ከገመገመ በኋላ ሀላፊነታቸውን ትተው ከፅንፈኞች ጋር በመሆን ቃለ ማሃላቸውን ክደው ሀገር ሲያፈርሱ ህዝብን ከህዝብ ሲያተራምሱ በመገኘታቸው ሁለቱን ሀላፊወች አግዷል። 1. የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ኮማንደር መንገሻ አውራሪስና 2. የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የፀጥታ አማካሪ ከፋለ እሱባለው ከሃላፊነት ማንሳቱን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

#WOLLO|| በጦርነት ለወደሙ አካባቢወች ለመልሶ ግንባታ የተበጀተው 20 ቢሊዮን ብር የት ገባ❗❓ ______ «በጦርነት የወደሙ አካባቢዎችን ለመልሶ ግንባታ ተብሎ 20 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት መ
#WOLLO|| በጦርነት ለወደሙ አካባቢወች ለመልሶ ግንባታ የተበጀተው 20 ቢሊዮን ብር የት ገባ❗❓ ______ «በጦርነት የወደሙ አካባቢዎችን ለመልሶ ግንባታ ተብሎ 20 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት መፅደቁ ይታወቃል።በጦርነት ከወደሙት አካባቢዎች መካከል ደግሞ ወሎ በዋነኝነት ተጠቃሽ ነው።ነገር ግን እስካሁን ድረስ መልሶ ግንባታ የሚባል ነገር አልተጀመረም የለም።ስለዚህ ለመልሶ ግንባታው የተበጀተው ብር የት ደረሰ❗❓» የተከበሩ የህዝብ እንደራሴ አቶ ሰይድ መሀመድ በጀቱ የዋለው ጭራሽ ጦርነቱ ላላያቸውና ለማያውቁት አካባቢወች ነው‼ የት እና እንደት በእነ ማን አማካኝነት ይህ ገንዘብ ወደ ወሎ እንዳይደረወስ እንደተደረገ ሙሉ መረጃ አለን‼ @Musab Ibnu Umeyir

ባለፈው ሳምንት ኮንፈረንስ ላይ፦ "እናንተን መሸከም ሰለቸን።ከዚህ በኋላ እኛ ራሳችንን ችለን ለናንተ ሰብስበን የምንሰጠውን ግብር ራሳችንን እናለማበታለን!" __________________ ባለፈው ሳም
ባለፈው ሳምንት ኮንፈረንስ ላይ፦ "እናንተን መሸከም ሰለቸን።ከዚህ በኋላ እኛ ራሳችንን ችለን ለናንተ ሰብስበን የምንሰጠውን ግብር ራሳችንን እናለማበታለን!" __________________ ባለፈው ሳምንት የደቡብ ወሎ ዞንና የደሴ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በወቅታዊ ሁኔታዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ኮንፈረንስ አድርገው ነበር።ኮንፈረንሱ ላይ ብዙ ወቅታዊና ባለፉት 2 አመታት የተፈፀሙ ክስተቶች የተነሱና ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን አመራሩ በባለ 9 ነጥብ የአቋም መግለጫ ሰብሰባውን ጨርሷል። በዚህ ኮንፈረንስ ላይ ለተገኙት የክልል አመራሮች ከተሰብሳቢወቹ የወሎን ልማትና ከልማት መገለል ብዙ ጥያቄ የተነሳ ሲሆን ከተነሱት መካከልም "እናንተን መሸከም ሰለቸን።ከዚህ በኋላ እኛ ራሳችንን ችለን ለናንተ ሰብስበን የምንሰጠውን ግብር ራሳችንን እናለማበታለን!" የሚለውና ብዙ ያነጋገረው ይገኝበታል!! @Musab Ibn Umer

photo content
+4

ከደሴ ከተማ ባልታወቁ ሰዎች ተሰርቃ ለ11 ወራት ተሰውራ የነበረችው ታዳጊ በማህበራዊ ሚዲያ አማካኝነት ተገኘች ====== ባልታወቁ ሰዎች ተሰርቃ ለ11 ወራት ተሰውራ የነበረችው የሦስት ዓመቷ ታዳጊ ሕፃን በማህበራዊ ሚዲያ አማካኝነት ተገኝታለች፡፡ የሦስት ዓመቷ ታዳጊ ሕፃን ረድኤት ዘሩ ሰኔ 12 ቀን 2014 ዓ.ም በደሴ ከተማ ሆጤ ክፍለ ከተማ 07 ቀበሌ ከጓደኞቿ ጋር እየተጫወተች እያለች ነበር ባልታወቁ ሰዎች ተሰርቃ የተወሰደችው። በደሴ ከተማ አስተዳደር 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ የሴቶችና ሕፃናት ክፍል ኃላፊ ምክትል ኮማንደር የሆኑት የህጻኗ ወላጅ እናት ወ/ሮ ማንጠግቦሽ ደሴ ከሥራ ሲመለሱ ነበር የልጃቸውን መጥፋት የሰሙት። በሁኔታው የተደናገጡት የረድኤት ቤተሰቦች በፍለጋ ቢደክሙም ሕጻኗን ሊያገኟት አልቻሉም ነበር። በቀጣይ ቀናቶችም በራዲዮና በተለያዩ ማስታወቂያዎች ማፈላለጉን ቢቀጥሉም ሕፃን ረድኤትን አየሁ የሚል ጠፋ። የፀጥታ ኃይሉ እና የአካባቢው ነዋሪዎች ፍለጋውን ቢያጠናክሩም ሕጻን ረድኤት ሳትገኝ ወራት በወራት እየተተኩ ለአስራ አንድ ወር ያክል የውሃ ሽታ ሆና ቀረች። ጉዳዩ በከንቲባው ጽሕፈት ቤት ከተያዘ በኋላ እንደ አማራጭ በማኅበራዊ ሚዲያ ልጅቱን የማፈላለግ አማራጭ ተይዞ፣ በደሴ ከተማ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽንና በደሴ ብልጽግና ፓርቲ ይፋዊ የፌስቡክ ገጾች የአፋልጉኝ ማስታወቂያ ከሕፃኗ ፎቶ ጋር ተያይዞ ተለጠፈ። ማስታወቂያውን የተመለከቱ የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችም ለበርካታ ሰዎች ማጋራታቸውን ተከትሎ ግንቦት 12 ቀን 2015 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ልጅቱን አየሁ የሚል ጥቆማ ተሰማ። ለእናት ማንጠግቦሽ ደሴ የተደወለ ስልክ ልጅቱ አዲስ አበባ እንዳለችና በቦሌ ክፍለ ከተማ አካባቢ አንዲት ሴት ለወራት ያክል ለልመና እየተጠቀመችባት እንደኾነ ተነገራቸው። ቤተሰቦቿም አዲሰ አበባ ለሚያውቋቸው ሰዎች ስለጉዳዩ በማስረዳት ሕፃን ረድኤት ዘሩንና እየለመነችባት ነው ስለተባለችው ግለሰብ ጉዳይ ለፖሊስ እንዲያሳውቁ በማድረግ ግለሰቧ በቁጥጥር ስር ዋለች። አዲስ አበባ የሚገኙ ዘመዶቻቸውም የጠፋችው ትክክለኝ ልጃቸው መኾኗን ለማረጋገጥ የሕፃን ረድኤት ፎቶ ለወላጆቿ ላኩ። ስለ ሁኔታው ለደሴ ኮሚዩኒኬሽን የተናገሩት እናት ማንጠግቦሽ በእንግልትና ስቃይ ውስጥ የተነሳችውን "የልጄን ፎቶ ስመለከት ጥርጣሬ ገብቶኝ ነበር" ብለዋል። እናት "ልጄ ለወራት ያክል በደረሰባት እንግልትና ስቃይ መልኳና ሰውነቷ መቀየሯ ታውቆኛል" ሲሉ አስታውሰው፣ ነገር ግን በአካል ሄደው ማየትና ማረጋገጥ ስለፈለጉ ወደ አዲስ አበባ እንደመጡ ይናገራሉ። "ገና ከርቀት እንዳየኋት ራሴን መቆጣጠር አቃተኝ፤ ቹቹ ብየ ስሟን ጠርቼ እንዳቀፍኳት እንባዬም መፍሰስ ጀመረ፤ ሰውነቴ ተንቀጠቀጠ“ የሚሉት ወላጅ አባት ዘሩ ሰይድ “ፈጣሪ ዳግም እንደ ፈጠረኝ ነው የማምነው” ሲሉ ነበር ስሜታቸውን የገለጹት። የሕጻን ረድኤት ቤተሰቦች ግንቦት 16 ቀን 2015 ዓ.ም ደሴ ከተማ ሲገቡ በደሴ ከተማ አሥተዳደር የሥራ ኀላፊዎች፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በጎረቤቶቻቸውና ስለ ጉዳዩ በሰሙ በከተማይቱ ነዋሪዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በቤታቸው ተገኝተው እንኳን ደስ ያላችሁ ያሉት የደሴ ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ ማኅበራዊ ሚድያን በአግባቡ ከተጠቀምን እንዲህ ልጅን ከቤተሰብ ማገናኘት ይቻላል ብለዋል። ወንጀለኞችን ለመከላከል ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ኃላፊነቱን መወጣት አለበት ያሉት ከንቲባው ለወራት በልጃቸው መጥፋት ቅስማቸው ለተሰበረው ቤተሰብ ከተማ አሥተዳደሩ የቤት ስጦታ እንዳዘጋጀላቸውና በፈለጉት ጊዜ መረከብ እንደሚችሉ አስታውቀዋል። ከሕፃን ረድኤት ዘሩ ያለችበትን የጠቆመችው ምንታምር በለጠ የምትባል በአዲስ አበባ በሊስትሮ ሥራ የሚትተዳደር ሴት መሆኗን የሕጻኗ በተሰቦቿ ተናግረው፤ ለወሮታዋም የደሴ ከተማ አሥተዳደር የ50 ሺህ ብር ሽልማት እንደሚያደርግ ገልጸዋል። ሕፃን ረድኤት ዘሩን በመስረቅና ለልመና ስትጠቀምባት የነበረችው ወይንሽት መኮንን የተባለችው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተደረገባት ይገኛል።

#ወሎ|| #ደሴ| #ቦሩ_ሜዳ_ሆስፒታል🙏 __ በደሴ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል ከአንድ ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች ነጻ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ሕክምና በዘመቻ መስጠት መጀመሩን
+4
#ወሎ|| #ደሴ| #ቦሩ_ሜዳ_ሆስፒታል🙏 __ በደሴ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል ከአንድ ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች ነጻ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ሕክምና በዘመቻ መስጠት መጀመሩን አስታወቀ። የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ተበጀ እንደገለጹት በዓይን ሞራ ግርዶሽ የሚሰቃዩ ሰዎችን ችግር ለመፍታት ነጻ የቀዶ ሕክምና አገልግሎቱ ከትላንት ጀምሮ እየተሰጠ ነው። ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር መስጠት በተጀመረው የሕክምና አገልግሎት 6 የዘርፉ ስፔሻላይዝድ ዶክተሮችን ጨምሮ ሌሎች የዓይን ሐኪሞች እየተሳተፉ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ከደሴ፣ ከደቡብ ወሎ፣ ከሰሜን ወሎ እና ከኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞኖች ሕክምናውን እንዲወስዱ በባለሙያዎች ለተለዩ ሰዎች ሕክምናው እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዘመቻው ከሚያዚያ 30 እስከ ግንቦት 4/2015 ዓ/ም ለተከታታይ 5 ቀናት የሚቆይ ሲሆን እስካሁን ከ200 ለሚበልጡ ሰዎች ህክምናው መሰጠቱን አስታውቀዋል፡፡ ዘመቻው በሕክምና መዳን እየቻሉ በተለያየ ምክንያት መታከም ያልቻሉና በዓይን ሞራ ግርዶች እየተሰቃዩ ያሉ ወገኖችን ችግር ለመፍታት የሚያስችል ነው ብለዋል። በሆስፒታሉ የዓይን ሕክምና ክፍል ሃላፊና የዘመቻው አስተባባሪ አቶ እንዳልክ ያረጋሌ በበኩላቸው፤ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ብዙ ጊዜ ከዕድሜ ጋር ተያይዞ የሚከሰት ነው። የዓይን ሞራ ግርዶች በወቅቱ ከታከመ እንደሚድን ጠቁመው፣ ይህ ካልሆነ ሙሉ በሙሉ የዓይን ብርሃንን እስከማሳጣት የሚያደርስ መሆኑን ገልፀዋል። የቀዶ ሕክምና ዘመቻው ዓላማም በሆስፒታል ለመታከም እድሉን ያላገኙ ወገኖችን ለማገዝ መሆኑን አብራርተዋል። የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል ባለፉት አራት ዓመታት ከ8 ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች የዓይን ሕክምና መስጠት እንደቻለ ከሆስፒታሉ የተገኘ መረጃ ያመለክታል። (#ደሴ_ኮሙኒኬሺን)

ከሰውነት ውጭ ምንም አይነት ነገር የማያውቀው የወሎ ማሕበረሰብ እንኳ የዚህ ቫይረስ ተጠቂ ሆኗል!! __ «በዚህ 5 አመት የገጠመን ፅንፍ የረገጠ የዘውግ ፖለቲካ ደግሞ ይለያል።እናትና ልጅን፣ባልና ሚ
ከሰውነት ውጭ ምንም አይነት ነገር የማያውቀው የወሎ ማሕበረሰብ እንኳ የዚህ ቫይረስ ተጠቂ ሆኗል!! __ «በዚህ 5 አመት የገጠመን ፅንፍ የረገጠ የዘውግ ፖለቲካ ደግሞ ይለያል።እናትና ልጅን፣ባልና ሚስቲን፣እህትና ወንዲምን እስከማለያየትና ማገዳደል የሚደርስ ነው። የሚገርመው ነገር እስከ አሁን ድረስ ከሰውነት ውጭ ምንም አይነት የዘርና እምነት ልዩነቶችን የማያውቀው የወሎ ማህበረሰብን እንኳ ከዛ ከዚህ እያዋከቡ የዚህ መጥፎ ቫይረስ ተጠቂ አዲሆን አድርገውት እያየን ነው።ይህን ለማንም አይበጅም በተለይ የእምነት አባቶችና የሀገር ሽማግሌወች መታገል አለባቸው።ልጆቻቸውን በመቆጣትና በመምከር ከዚህ በሽታ ማከም አለባቸው!» (ዲ/ን ዳንኤል ክብረት)

photo content

ስልጣንንና ፍላጎትን በኀይልና በጉልበት ለመጫንና ለመንጠቅ የሚደረግን እንቅስቃሴ መታገል እንደሚገባ የኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር ገለጸ። ከሚሴ፡ ሚያዝያ 30/2015 ዓ.ም (አሚኮ) በኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር ከሚሴ ከተማ ግድያን የሚቃወም ሕዝባዊ ሰልፍ ተካሂዷል። ሰላማዊ ሰልፉ ላይ የከሚሴ ከተማና ደዋጨፋ ወረዳ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል። በሕዝባዊ ሰልፉ ላይ የህግ የበላይነት ይከበር፣ መሪን በመግደል የሚቆም ትግል የለም፣ እርስ በእርስ በመጋጨት የሚፈሰው ደም እንጂ የሚለወጥ ሀገር የለም፣ ፅንፈኝነት የወቅቱ ፈተና ነው እና ሌሎች መልዕክቶች ተላልፈዋል። የከሚሴ ከተማና ደዋጨፋ ወረዳ ነዋሪዎች ፅንፈኛ ኀይሎች በክልላችን እንቁ አመራሮች ላይ የሚያደርጉትን ግድያ እንቃወማለን በማለት መንግስት እነዚህ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ ሊወስድ ይገባል ብለዋል። የኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር ዋና አሥተዳዳሪ አህመድ አሊ በሰልፉ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ስልጣንንና ፍላጎትን በኀይልና በጉልበት ለመጫንና ለመንጠቅ የሚደረግን እንቅስቃሴ መታገል እንደሚገባ ገልጸዋል። በየአካባቢያችን አንድነታችንንና ሰላማችንን ለመንጠቅ የሚጥሩ ፅንፈኛ ኀይሎችን አጀንዳ በመረዳት ልናወግዝ ይገባል ብለዋል። #አሚኮ (ዘጋቢ፦ ይማም ኢብራሂም ) https://www.facebook.com/Voiceofwollo2019/

photo content
+5

#ሸዋ|| #ደብረብርሃን🙏 በትናንትናው ዕለት በደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ በባሶና ወራና ወረዳ ቀይት ምርጫ ክልል በወቅታዊ ሀገራዊ የሠላም ጉዳይ እንዲሁም በአቶ ግርማ የሺጥላ የግድያ ወንጀልን የፈጸሙ ኃይሎችን በማውገዝ መንግስት የጀመረውን የህግ ማስከበር ተግባር አጠናክሮ እንዲያስቀጥል በአደባባይ ድምጻቸውን አሰምተዋል። በአማራ ክልል ተደጋጋሚ መሪን መግደል የተለማመደ በሚመስል መልኩ በተደጋጋሚ የሚደረገው የመሪዎች መገደል መቆም እንደሚገባው ሰልፈኞቹ ገልጸዋል። በዚህ እኩይ ተግባር በተጠመዱ ሀይሎች ላይም መንግስት የማያዳግም አስተማሪ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባውና ነዋሪዎቹም ከመንግስት ጎን እንደሚቆሙ ነው ሰልፈኞቹ ድምጻቸውን በአደባባይ ያሠሙት የተደረገው ግድያ የአማራን ክልል መሪ አልባ ለማድረግ በጥናት ላይ የተመሠረተ ነው ስለሆነም መንግስት ወንጀሉን የፈጸሙትን አካላት እና የውጭና የውስጥ የእኩይ ተግባሩ ተባባሪ ፣ አቀናባሪ ኃይሎችን በየደረጃው ተጠያቂ እንዲሆኑ በማድረግ በኩል ክትትሉንና እርምጃውን አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት በአቶ ግርማ የሺጥላ የምርጫ ክልል የሚገኙ ነዋሪዎች አሳስበዋል። በባሶና ወራና ወረዳ ቀይት ምርጫ ክልል አቶ ግርማ የሺጥላ በተከታታይ 2 አመት የዚህን አካባቢ በመወከል ከፍተኛ የመሠረተ ልማት አውታሮች ለህዝብ በሚጠቅም መልኩ እንዲገነቡ ከፍተኛ የእድገት መሠረቶችን ያስቀመጡ እውነተኛ ፣ቆራጥ መሪ እንደነበሩም ነው የምርጫ ክልሉ ነዋሪዎች የገለጹት። አቶ ግርማ የሺጥላን እንዲሁም የክልሉን መሪዎች በመንቀፍም ሆነ በመግደል የሚረጋገጥ የአማራ ህዝብ ጥያቄ እንደሌለም ነው ሠልፈኞቹ ያወገዙት ለህግ የበላይነት መረጋገጥ ከመንግስት ጎን በመቆም እንደሚሠሩም ገልጸዋል። በነዚህ ቆራጥ ለሰሜን ሸዋ ለአማራ ክልል እንዲሁም ለሀገራቸው ማደግ ከፍተኛ እምነት ያላቸውን መሪ በማጣት የሚረጋገጥ እድገት ወይም የአማራ ህዝብ ተደጋጋሚ በደልና ረጅም ጊዜ የፈጁት ጥያቄዎች ምላሽ ለማግኘት የማይቻል እንዲሁም ህዝብን ለሌላ በደል መጋበዝ መሆኑን በማውገዝ በዚህ እኩይ ተግባር የተሠማሩ ሀይሎችን በህግ ተጠያቂ መሆን እንዳለባቸውም ነው በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ በባሶና ወራና ወረዳ ቀይት ምርጫ ክልል ነዋሪዎች ለመንግስት በአደባባይ ድጋፋቸውን ያሰሙት በሠልፉ ላይም የደብረብርሃን ከተማ ከፍተኛ አመራሮች፣ የክፍለ ከተማ አመራሮች እንዲሁም የባሶ ወረና ወረዳ አመራሮች የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተው በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተደረገውን የተቀነባበረ ግድያ በማውገዝና በሻማ ማብራት ስነስርአት አስበዋል።

#ወሎ|| #ቃሉ "ሀገር መከላከያ ሰራዊት ነው ዋስትናችን!" https://t.me/VoiceOfWollo
#ወሎ|| #ቃሉ "ሀገር መከላከያ ሰራዊት ነው ዋስትናችን!" https://t.me/VoiceOfWollo

photo content
+1

ከፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ተባብሮ በመሥራት የሽብር ተግባር ፈፅሟል በሚል ሲፈለግ የነበረው ጎበዜ ሲሳይ የተባለው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ!! ================ በአማራ ክልል ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማፍረስ ከፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ተባብሮ በመሥራት የሽብር ተግባር ፈፅሟል በሚል ሲፈለግ የነበረው ጎበዜ ሲሳይ የተባለው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል። ግለሰቡ አምልጦ ጅቡቲ ከገባ በኋላ ወደሌላ አገር ሊሻገር ሲል ከዓለም አቀፉ ፖሊስ እና ከጅቡቲ መንግሥት ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር እንዲውል እና ተላልፎ ለኢትዮጵያ እንዲሰጥ ተደርጎ ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ መግባቱን የፌዴራል ፖሊስ ገልጿል። በአማራ ክልል ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን በማፍረስ ክልላዊ ሥልጣንን በኃይል ለመያዝ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በህቡዕ ተደራጅተው እና ተቀናጅተው በሚንቀሳቀሱ ፅንፈኛ ኃይሎች ላይ የማያዳግም ሕጋዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል ሚያዚያ 22 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ ይታወሳል። በዚህ መሠረትም፦ 1. ሀብታሙ አያሌው፣ 2. ምንአላቸው ስማቸው 3. ብሩክ ይባስ እና 4. እየሩሳሌም ተ/ፃዲቅ 5. ዘመድኩን በቀለ 6. ልደቱ አያሌው 7. መሳይ መኮንን 8. ጎበዜ ሲሳይ 9. ምህረት ወዳጆ (ምሬ ወዳጆ) 10. በለጠ ጋሻው እና 11. ሙሉጌታ አንበርብር የተባሉት ተጠርጣሪዎች በፈፀሙት የሽብር ተግባር እንደሚፈለጉ እና ከዓለም አቀፉ የፖሊስ ድርጅት ኢንተርፖል ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር በማዋል ለሕግ እንደሚቀርቡ የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ማሳወቁ ይታወሳል። ከነዚህ ተጠርጣሪዎች መካከልም ጎበዜ ሲሳይ ዘገየ የተባለው ግለሰብ፣ በአማራ ክልል ቆቦ አካባቢ የፅንፈኛ ታጣቂ ኃይሎችን በማደራጀት፣ በቅርቡም በጽንፈኞች ግድያ የተፈጸመበትን የአቶ ግርማ የሺጥላን ግድያ በማስተባበር ሚና እንደነበረው፣ በመከላከያ እና በሕዝቡ ላይ ፅንፈኞች ጥቃት እንዲያደርሱ በማደራጀት እና ቃል አቀባይ ሆኖ በማስተባበር የሽብር ተግባር ውስጥ በመሳተፍ ተጠርጣሪ በመሆን ሲፈለግ ቆይቷል። ግለሰቡ አማራ ክልልን በማሸበር እና ሥልጣንን በኃይል በመቀማት በቀጣይም የፌዴራል መንግሥትን ለማፍረስ ሲንቀሳቀስ ከነበረ ፅንፈኛ አካል ጋር በመተባበር ሲሠራ እንደነበር በመጠርጠሩ፣ ግለሰቡን ጨምሮ ሌሎች በቁጥጥር ስር ያልዋሉ ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የጋራ ግብረ ኃይሉ ከኢንተርፖል ጋር ባለ ስምምነት መሠረት ሲሠራ መቆየቱን ገልፆ ነበር። በዚሁ መሠረትም አስፈላጊውን ፎርማሊቲ እና አግባብ ያላቸው መረጃዎችን በማደራጀት ጎበዜ ሲሳይ የተባለው ግለሰብ አምልጦ ጅቡቲ ከገባ በኋላ ወደሌላ አገር ሊሻገር ሲል ከዓለም አቀፉ ፖሊስ እና ከጅቡቲ መንግሥት ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር እንዲውል እና ተላልፎ ለኢትዮጵያ እንዲሰጥ ተደርጎ ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ ገብቷል። የፀጥታ እና የጋራ ግብረ ኃይል አሁንም ኢትዮጵያ ባላት ስምምነት መሠረት ሌሎች ያልተያዙ የሽብር ቡድኑ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል እየሠራ መሆኑን ለኢዜአ ገልጿል። #Ebc

#ወሎ|| #ኩታበር የደ/ወሎ ሕዝብ ጥይት "ሰውን እንጂ ሀሳቡን አይገድልም።ለዝርፊያና ምዝበራ እንድመቻችሁ መሪወቻችንን በመግደል ህዝብ እንድተራመስ፣ሀገር እንድፈርስ የምትሰሩ ፅንፈኛና የባንዳ ተላላኪ
+3
#ወሎ|| #ኩታበር የደ/ወሎ ሕዝብ ጥይት "ሰውን እንጂ ሀሳቡን አይገድልም።ለዝርፊያና ምዝበራ እንድመቻችሁ መሪወቻችንን በመግደል ህዝብ እንድተራመስ፣ሀገር እንድፈርስ የምትሰሩ ፅንፈኛና የባንዳ ተላላኪወች አደብ አድርጉ!" ብሏል። የወሎ ድምፅ Voice Of Wollo https://t.me/VoiceOfWollo

"ወሎ" ሲባል ማንጠስ፣ማስነጠስ…አይን ማሸት የጤና አይመስለኝም። አንዳንዶች የወሎን የክልልነት ጥያቄ በገፃቸው ሲያሰፍሩ ወባቸው የሚነሳ ሰዎች ግርም ይሉኛል።ለወሎ ያቀዱት ሴራ ሁሉ ስለከሸፈ አሁን ጭ
"ወሎ" ሲባል ማንጠስ፣ማስነጠስ…አይን ማሸት የጤና አይመስለኝም። አንዳንዶች የወሎን የክልልነት ጥያቄ በገፃቸው ሲያሰፍሩ ወባቸው የሚነሳ ሰዎች ግርም ይሉኛል።ለወሎ ያቀዱት ሴራ ሁሉ ስለከሸፈ አሁን ጭንቅ ላይ ወድቀዋል።ክልል መሆን እፈልጋለሁ ብሎ ጥያቄ የሚያቀርበው የወሎ አካባቢ ነዋሪ፣ድምፅ የሚሰጠው የወሎ ህዝብ ሌላ አያስፈልገውም።ነገር ግን በዚህ ወቅት ያላሰበውን አታሳስቡት፣ያላቀደበትን አታነሳሱት። ጥያቄውን ቢያነሳ ደግሞ መብቱ ነው።ነጠላ ዘቅዝቆ የሚያስለቅስ፣ያዙኝ ልቀቁኝ የሚያስብል ጉዳይ አይደለም።ከእኔ በላይ አዋቂ፣ከእኔ በላይ ተቆርቋሪ በማለት ራሳችሁን ቆልላችሁ የምትገኙ ተላላኪዎች ጅምራችሁ አያዋጣም ተውት‼የወሎ ህዝብ በአማራነቱም ሆነ በኢትዮጵያዊነቱ አይደራደርም‼አንድነቱን ለማጥፋት ፣ወግ ባህሉን ለመበረዝ፣እሴቱን ለመሸርሸር ሌት ከቀን የምትደክሙ ባለበጀቶች እባካችሁ ሌላ አጀንዳ ፈልጉ‼ @ዋሱ ሙሀመድ

አገራችን አውሳ፤ ቤታችን አፍዴራ፤ ርስታችን አሰብ፤ ሃድራችን አስመራ፤ ጠበቃ ዋሳችን ፤አፋር አሊ ሚራ፤ ቁርሳችን የጁ ላይ፤ ምሳችን ሰመራ፤ የአውሳ ዳር ጠንበለል፤የወሎ ገምሻራ፤ የወሎ ጃውሶች....
አገራችን አውሳ፤ ቤታችን አፍዴራ፤ ርስታችን አሰብ፤ ሃድራችን አስመራ፤ ጠበቃ ዋሳችን ፤አፋር አሊ ሚራ፤ ቁርሳችን የጁ ላይ፤ ምሳችን ሰመራ፤ የአውሳ ዳር ጠንበለል፤የወሎ ገምሻራ፤ የወሎ ጃውሶች.... ዘራችን ፍቅር ነው... ሰው ካለበት ምድር፤ የትም የሚዘራ። ሚሌ ወዲህ እንዲህ መጋሌ ስመራ፤ ቁመቱ ሚመስለው የአዋሽ ዳር ሸንኮራ፤ ሽርጥ አገልድሞ ተገማሸርበት ከሚሌ እስከ አፍዴራ፤ የነ ሸህየ ልጅ የደጋጎቹ ዘር የወሎው ቀብራራ። መጋሌ ስመራ.... (ጃኖ መንግስቱ ዘገየ)

photo content
+4

#ወሎ #አልብኮ_ወረዳ "ግጭት ጦርነት ይብቃ፣ሰላምን እናስፍን!!" በደቡብ ወሎ ዞን አልብኮ ወረዳ በቅርቡ በአቶ ግርማ የሺጥላ ላይ የተከሰተውን መሰዋእትነት የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ። መሪን በመግደል የሚቆም ምንም አይነት ትግል የለም፤ ፅንፈኝነት ለክልላችን እና ለሃገራችን ብልፅግና ሳንካ መሆኑን አዉቀን እንታገላለን፤ የሃገር መከላከያ ሰራዊት ዋስትናችን ነዉ፤ ለክብሩም ደጀን እንሆናለን፣ ህብረ ብሄራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነትን በማጎልበት ለኢትዮጵያ አንድነት መትጋት አለበት ሲሉ በሰልፉ ላይ ጠይቀዋል። በመጨረሻም ስልፈኞቹ የአቶ ግርማን እና የእነ ዶ/ር አምባቸዉን ህልም ለማሳካት ዘወትር እንተጋለን በቀጣይ መንግስትን ህግ የማስከበር ስራ አጠናክሮ እንዲቀጥል እንፈልጋለን፤ እኛም እናግዛለን በማለት ገልጸዋል።

photo content
+3