ar
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

الذهاب إلى القناة على Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

إظهار المزيد
3 503
المشتركون
-124 ساعات
+57 أيام
+7630 أيام
أرشيف المشاركات
#አስቸኳይ በጅማ ዞን ሰጠማ ወረዳ ጋትራ ከተማ ሐሙስ በ04/07/2017 ከሌሊቱ 9:00 ሰዓት ጥላችን አንግበው በተደራጁ ቡድኖች የኢትዮጵያ ወንጌላዊውት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ምዕመና፣ በንብረቶቻቸው እንዲሁም በቤተ ክርስቲያኒቱ የማምለኪ አዳራሽ ላይ አሰቃቂ ጥቃት ተፈፅሟል። ጥቃቱን አስመልክቶ በኦሮሚያ ክልል መንግሥት አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ፣ የጅማ ዞን እና የጋትራ ወረዳ የተፈፀመውን ህገ ወጥ ተግባር ተጣርቶ አፈጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ጥሪ አቅርባለች። ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ጥብቅ ፀሎት እንዲደረግ ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን አቅርባለች። የደብዳቤውም ዝርዝር ሀሳብ ከዚህ በታች እንደሚከተለው ቀርቧል። * * * * * * * * * * የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማህበራነ ምዕመናንና ምዕመናን በሙሉ፡፡ የእግዚአብሔር ጸጋና ሠላም ይብዛላችሁ፡፡ ሰሞኑን በጅማ ዞን፤ ሰጠማ ወረዳ ጋትራ ከተማ ባለው ማህበረ ምዕመናችንና በምዕመናኑ ላይ የደረሰውን ጉዳት አስመልክቶ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ከታች በተመለከተው መሠረት ጥያቄ ቀርቧል፡፡ ይህንና ከዚህ ጋር ተያይዘው ባሉት ጉዳዮች ላይ ብርቱ ጸሎት እንዲደረግ እንጠይቃለን፡፡ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በመላ ሀገሪቱ በሰላም ግንባታ፣ በተለያዩ በልማት እና የማህበራዊ አገልግሎት ስራዎችን ስትሰራ ቆይታለች ለወደፊትም አጠናክራ ትቀጥላለች። የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ከሌሎች የሀይማኖት ድርጅቶች ጋር በመሆን ለሀገር በሚጠቅሙ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ትልቅ ሚና እየተጫወተችም ትገኛለች። ነገር ግን ከዚህ በተቃራኒ ሐሙስ 04/07/2017 ከሌሊቱ 9፡00 ሰዓት ላይ በጅማ ዞን በሰጠማ ወረዳ በጋቲራ ከተማ ለእምነታችን ጥላቻ ያላቸው ግለሰቦች ራሳቸውን በማደራጀት በምዕመናኖቻችን እና በንብረታቸው ላይ ዘግናኝ ድርጊትን ፈጽመዋል። በተጨማሪም ምዕመናኖቻችን የሚያመልኩበትን የጸሎት ቤት አቃጥለው ከነሙሉ ንብረት አውድመውታል። በደረሰው ጉዳት 9 አባሎቻችን በእጃቸው፣በጭንቅላታቸው፣በአንገት እና በሌሎች የሰውነት ክፍሎቻቸው ላይ በተለያዩ ስለታማ መሳሪያዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የ14 ሰዎችን ቤት ሰብረው በመግባት ንብረታቸውን ሁሉ በሙሉ አውድመዋል። በጋቲራ ከተማ የሚገኘው የምእመናን የጸሎት ቤት በእሳት ተቃጥሏል። በጸሎት ቤቱ ውስጥ ያለው ንብረት በሙሉ ወድሟል። ይህ የለውጥ መንግስት በሀገሪቱ ውስጥ መሰረታዊ ስራዎችን እየሰራ ባለበት እና የሃይማኖት እኩልነት ተረጋግጦ ባለበት ሁኔታና ማንም ሰው የፈለገውን ማምለክ በሚችልበት በዚህ ወቅት ድርጊቱ መፈፀሙ የበለጠ አሳዝኖናል ። የእኛ እና የተጎዱ ምዕመናኖቻችን ሞራልም በእጅጉ ተነክትቷል፤ በጋቲራ ከተማ በሚገኙ ልጆች እና ሴቶች ላይ የደረሰው የስነ-ልቦና ጉዳትም እንዲሁ በቀላሉ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም፡፡ ለዚህ ለደረሰው አደጋ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት በጅማ ዞን አመራር በኩል እየተደረገ ያለውን ጥረት ሁሉ እያደነቅን፣ የኦሮሚያ ብሔራዉ ክልላዊ መንግስት አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ለዚህ ጉዳይ ትኩረት ሰጥቶ ጉዳዩን በቅርበት እንዲከታተል እና አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ፡ 1. የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ምእመናን አስፈላጊው የህክምና ድጋፍ በአስቸኳይ እንዲደረግላቸው፣ 2. በንብረታቸውና በመኖሪያ ቤታቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ምእመናን መኖሪያ ቤታቸው እንዲሰራና የወደሙ ንብረቶቻቸው እንዲተኩ ሊደረግ ይገባል። 3. የተፈናቀሉ ምዕመናኖቻችን ወደ ቤታቸው እንዲመለሱና ህጋዊ ከለላ እንዲደረግላቸው፣ 4. የምእመናን የጸሎት ቤት በእሳት በመቃጠሉ የጸሎት ቤቱና በውሰጡ የነበሩ የወደሙ ንብረቶች በሙሉ ወደ ቦታቸው እንዲመለሱ፣ 5. መንግስት ባለበት ሀገር የህግ የበላይነትንና የሃይማኖት እኩልነትን በመጣስ እነዚህን ድርጊቶችና ወንጀሎች በፈጽሙ አካላት ላይ ትምህርታዊ የሆነ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ፡፡ በአጠቃላይ ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስተዳደርና ፀጥታ ቢሮ ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች በአፋጣኝ አጣርቶ በተፈፀመ ህገወጥ ድርጊቶች ላይ አስፈላጊና አስተማሪ እርምጃ እንዲወስድ በትህትና እንጠይቃለን። ለሚደረግልን ድጋፍ እና ህጋዊ እርምጃ ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው። ከሰላምታ ጋር፡፡ ግልባጭ፡ - ለኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስተዳደርና ጸጥታ ቢሮ ፊንፊኔ - ለጅማ ዞን አስተዳደር ጅማ

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ሴቶችን ወደ ቅስና አገልግሎት የጠራችበትን 25ኛ ዓመት በደማቅ ክብረ በዓል አከበረች * * * * * * * ቤተ ክርስቲያንኒቱ እ.ኤ.አ ግንቦት 16 ቀን 2000 ዓ.ም የመጀመሪዋን ሴት ቄስ ፡ ቄስ ዶ/ር በኩሬ ዳባን ለቃሉ እና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት ወደ ቅስና አገልግሎት ከጠራች ድፍን 25 ዓመታት ተቆጥረዋል። ይህንንም የአገልግሎት ጉዞ ምክንያት ያደረገ ልዩ የምስጋና በዓል በቤተ ክርስቲያኒቱ የሴቶች አገልግሎት መምሪያ አዘጋጅነት በጉዲና ቱምሳ ሁለገብ ሥልጠና ማዕከል ተካሂዳል። ለዚህም በዓል ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ ሴት ቀሳውስት ከቤተክርስቲያኗ ሲኖዶሶች ለበዓሉ የተገኙ ሲሆን በዓሉን ምክንያት በማድረግ በፀሎት፣ በዝማሬ፣ በምክክር እና በተለያዩ አርዕስቶች ዙሪያ የቀረቡ ፅሁፏችን በመካፈል ከትላንትና ጀምረው ልዩ የህብረት እና የአንድነት ጊዜ አሳልፈዋል። በዛሬውም አለት የካቲት 27 ቀን 2017 የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ፣ የሲኖዶስ መሪዎች፣ የመጀመሪያ የቤተክርስቲያኒቱ ሴት ቀሳውስት፣ የቤተክርስቲያኒቱን የሴቶች አገልግሎትን በተለያዩ ዘመናት የመሩ መሪዎች፣ ከኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት የሴቶች ዘርፍ አስተባባሪዎች፣ ከሀገር ውስጥና ከውጪ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተካሂዷል። በመርሃ ግብሩም ላይ የ25 ዓመታት ጉዞን የሚያውስ ፅሁፍ ቀርቧል። በቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ፣ የሴቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ታገሰች ደግነው እና ጥሪ በተደረገላቸው እንግዶች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቶች ተላልፈዋል። ቀኑንም ምክንያት በማድረግ በዋናው ጽሕፈት ቤት ለቀድም የሴቶች አገልግሎት መምሪያ አስተባቢሪዎችና ዳይሬክተሮች፣ ለመጀመሪያዎቹ የቤተክርስቲያኒቱ ሴት ቀሳውስት እና አጋር ድርጅቶች እውቅና ተሰጥቷል። - - - - - - - - - The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus celebrated the 25th year anniversary of the church's call for the women's ministry of priesthood. * * * * * * * Since the church called the first female pastor, Rev. Dr. Bekure Daba for the Service of the Word and Sacrament 25 years are counted. Because of this ministry milestone, the Church's Department of Women's Ministry organized a thanksgiving celebration at the Gudina Tumsa Wholistic Training Center. A large number of female pastors gathered from the Church's Synod across Ethiopia to partake in the celebration, and the female pastors had a wonderful fellowship time praying, singing, consulting and attending presentation on various topics since yesterday. Today, 6th of March 2025, in the presence of the president of the church, Rev. Dr Yonas Yigezu, Synod presidents, senior female pastors of the church, coordinators of women's affair at the Interreligious Council of Ethiopian, and invited guests from within the country and abroad the grand celebration was held. On the program, a paper was presented on the 25 years Journey. President of the church, director of the Women's Ministry Department, Rev. Tagesech Dagnew and invited guests on the program passed congratulations message. Sinor female pastors of the church, former Women's Ministry directors and coordinators, and active partner organization are recognized on the event.

EECMY 43rd CMCR Meeting started this evening with Holly Communion service and fellowship time. The meeting will keep on holding for the coming three days under the overarching theme of "One Spirit, One Mission, From Local and Global Perspectives".

Wangeela Maarqoosi fi Seerri Ba’uu Piroojektii Kaaraamaatiin gara afaan naannoo sanaatti hiikaman eebbifamaniiru. Wangeela Maarqoosi fi Seerri Ba’uu Piroojektii Kaaraamaa Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Itoophiyaa, Kutaa Hiika Macaafa Qulqulluu fi Kutaa Tajaajila fayyadama Caaffata Qulqullaa’oo keessaa jiraan keessaa tokko kan ta’e Piroojektii Kaaraamaatiin kan hiikamee fi maxxanfamee, Aanaa Fantaalle Matahaaraatti Waldaa Kiristaanaa Dabre Selaam Qale-Hiwoot keessatti eebbifamee amantootaaf raabsamuuf qophaa’eeraa. Macaafonni kuniis namoota afaanicha dubbatanii; dubbisuu hin dandeenyeef waraabbi sagaleedhaan qophaa’eeraa. Sirna eebbaa kana kan gaggeessan kutaa Ergamaa fi Ti'ooloojii keessatti qindeessaa kutaa Tajaajila Ti'ooloojii waldaa kiristaanaa kan ta'an Luba Balinaa Eebbaa yoo ta'u, qindeessaan tajaajila hiikkaa waldaa kiristaanaa biyyaalessaa kan ta’aan Luba Solomoon Haayilee ergaa dabarsaniiru. Sagantaa kana irratti warri afaanichatti hiikaani, gamaaggamtoonni, koreewwan, dubbattoonni, akkasumas bakka bu’oonni waldoota, hojjettoonni Waajjira Hiikaa biyyaalessaa fi keessummoonni affeeraman argamaniiru. Amantoonni Macaafonni kun maxxanfamuu isaaniitti gammachuu isaanii ibsaniiru, sagalee Waaqayyoo afaan garaa isaaniitiin fudhachuun guddina hafuuraa isaanii fi babal’ina wangeelaaf gumaacha guddaa akka qabu amantaa qaban ibsaniiru. Guyyichaattis Macaafonni eebbifamaani raabsaaf dhiyaatan kun qaama guutuu hojii hiikaa Macaafa Qulqulluu yoo ta’u, toora tooran Macaafoota hiikamanii xumuraman amantoonni akka dubbisaniif dhiyeessin kan itti fufu ta’a.