The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
الذهاب إلى القناة على Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
إظهار المزيد3 291
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+147 أيام
+9930 أيام
أرشيف المشاركات
በጋሞ ዞን የተከሰተውን የመሬት መንሸራተት አደጋ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አመራሮች በህዝባዊ ክብረ በዓል አውድ ላይ ለምዕመናን ባስተላለፉት መልዕክት ሀዘናቸውን ገለፁ።
በያዝነው ሳምንታት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ የጣለውን ከፍተኛ ዝናብ ተከትሎ በደሰረው አደጋ በዜጎች ህልፈተ ህይወት መሪዎቹ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀዋል። በአደጋውም ምክንያት ቤተሰቦቻቸውን ላጡ እና ከመኖሪያ አከባቢያቸው ለተፈናቀሉ የማህበረሰብ ክፍሎች መሪዎቹ ፀሎት አድርገዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱም ፕሬዘዳንት ቄስ ዶ/ር ዩናስ ይገዙ የአደጋው ተጎጂዎች በአሁኑ ሰዓት አፋጣኝ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የገለፁ ሲሆን ቤተ ክርስቲያኒቱም አደጋው በደረሰበት አከባቢ አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙት ከደቡብ ምዕራብ እና ከደቡብ ኢትዮጵያ ርሆቦት ሲኖዶሶች ጋር በቅርበት በመስራት ምዕመናንን ያሳተፈ ድጋፍ እንደሚደረግ ገልፀዋል። ምዕመናንም በበኩላቸው በፀሎት እና አስፈላጊ በሆኑ የነፍስ አድን ድጋፎች ከአከባቢው ማህበረሰብ ጎን እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ደቡብ ሲኖዶስ 25ኛ ዓመት የምስረታ እና ወንጌል በጌዴኦ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰበከበት 77ኛ አመት ክብረ በዓል ለመካፈል የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ዛሬ ማለዳ ዲላ ከተማ ገብተዋል።
የዲላ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር መስፍን ደምሴ፣ የሲኖዶሱ ፕሬዚዳንት ቄስ ወልዴ አየለ እና የሲኖዶሱ ማኔጅመን እንግዶችን በድምቀት ተቀብለዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም እና የቅዱሳት መጻሕፍት አጠቃቀም አመታዊ ኮንፍረንስ ተካሄደ
የ6ተኛው ዙር ኮንፍረንስ ከሁሉም የቋንቋ ትርጉም ቢሮዎች የመጡ ተርጓሚዎች እና ድጋፍ ሰጪዎች ባሳተፈ መልኩ “ትርጉም ለሁለንተናዊ ለውጥ” በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት 1-3 ቀን 2018 ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም አገልግሎት ክፍል በሃገር አቀፍ ደረጃ 19 በሚሆኑ ቋንቋዎች የትርጉም አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ የአገልግሎቱ ብሔራዊ አስተባባሪ ቄስ ሰለሞን ሀይሌ ገልጸዋል። የትርጉሙም ሥራዎቹ በጽሁፍ፣ በቃል፣ በትረካ እና በሌሎች መንገዶች እየተሰሩ ለአገልግሎት እንደሚቀርቡ አስተባባሪው ጨምረው ገልጸዋል።
መርሃ ግብሩን በኦፊሴል በከፈቱበት ወቅት መጽሐፍ ቅዱስ የሚስዮን አገልግሎት መሳሪያ እንደሆነ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሚስዮን እና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ጥላዬ ከበደ የተናገሩ ሲሆን ለወንጌል መስፋፋት የትርጉም አገልግሎት አስተዋጽኦን በማስታወስ ተርጓሚዎች አገልግሎታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አበረታተዋል።
ለሶስት ተከታታይ ቀናት በቆየው ኮንፍረንስ "ትርጉም እና ሚስዮን"፣ " የትርጉም አገልግሎት እና አጋርነት"፣ "አርቲፊሻል ኢንተለደንስ እና የትርጉም አገልግሎት" በሚሉ እና በርካታ አርዕስቶች ዙሪያ ፅሁፎች የቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎች በውይይት ሀሳቦችን አዳብረዋል።
የኮንፍረንሱም ተሳታፊዎች ያሳለፏቸው የትምህርት፣ የምክክር እና የአንድነት ጊዜዎች በብዙ እንደጠቀማቸው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የካምፖስ አገልግሎት መሪዎች አውደ ጥናት ተካሄደ።
በቤተ ክርስቲያኒቱ የካምፓስ አገልግሎት በተዋቀሩ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ህብረት ከሚካሄድባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ከመጡ የአገልግሎቱ መሪዎች ጋር ከጥር 20-21/20218 የሁለት ቀናት አውደ ጥናት በጉዲና ቱምሳ ሁለገብ የሥልጠና ማዕከል ተካሂዷል።
በአውደ ጥናቱም ላይ በተለያዩ አርዕስቶች ዙሪያ ጽሑፎች ቀርበዋል። ከተማሪ ህብረት መሪዎችም ጋር ባጋጠሟቸው ተግዳሮቶች፤ ከተቀባይ ማኀበራነ ምዕመናን ጋር ባሉ ግንኙነቶች እና ቀጣይ የአገልግሎቱ አቅጣጫዎች ዙሪያ ምክክር መካሄዱን የካምፖስ አገልግሎትና የከተማ ወንጌል ማዳረስ ዋና ክፍል አስተባባሪ ቄስ ወርቁ ኤባ ገልጸዋል።
በማጠቃለያውም የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልዕኮ እና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር የሆኑት ቄስ ጥላዬ ከበደ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ወጣቶችን እና ልጆችን አቅፋ የማታገለግል ቤተ ክርስቲያን ውጤታ መሆን እንደማትችል ገልጸዋል። አክለውም በአውደ ጥናቱ የተካፈሉ የህብረቶቹ መሪዎች ብዙ ሺህ ወጣቶችን ወክለው በዚህ እንደተገኙ በማስገንዘብ በስልጠና እና በውይይት ያዳበሯቸውን ሀሳቦች ተግባራዊ ለማድረግ እንዲተጉ አሳስበዋል።
አገልግሎቱ በዋነኛነት የሚመለከተው መምሪያም አስፈላጊ በሆኑ ጉዲዮች ሁሉ ድጋፍ ለማድረግ ዳይሬክተሩ ቃል የገቡ ሲሆን ተለታሳታፊ መሪዎች የመጽሐፍ ስጦታ አበርክተዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሉተራን አስተምህሮ ዙሪያ ያላቸውን ግንዛቤ ለማጎልበት የሚረዱ ሥልጠናዎችን በአካል እና በርቀት መስጠት የሚያስችሉ ፕሮራሞቻቸውን ከሉተራን ሀወር ሚኒስትሪ የመጡ አገልጋዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
#ተዘጋጅተናል?
ዓመታዊው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሚስዩን ቀን በሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ማኀበራነ ምዕመናን በነገው ዕለት ጥር 17 ቀን 2018 በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድምቀት ይከበራል።
"ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ መሥራት ይገባኛል" ዮሐንስ 9፥4
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
