Addis Ababa Health Bureau / አዲስ አበባ ጤና ቢሮ / AACAHB /
الذهاب إلى القناة على Telegram
ጤና ለሁሉም !! ይህ ቻናል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ ጤና ጣቢያ ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የጤና መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡
إظهار المزيد7 125
المشتركون
+124 ساعات
+277 أيام
+6730 أيام
أرشيف المشاركات
ዛሬ በምርጫ ሥራዎቻችን አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ሥራዎቻችን በውጤታማነት በመከወን የያዝናቸውን ግቦች በተሟላ መልኩ ከማሳካት አንፃር የተገኙ ዉጤቶችን ከመላው የከተማችን አመራሮች ጋር ገምግመናል ።
7ኛውን ጠቅላላ ሃገራዊ ምርጫ በስኬት እንዳይጠናቀቅ ለማደናቀፍ በውጭም በውስጥም በጋራ በማበር በሚደያ ዘመቻዎች እና በተለያዩ ቅስቀሳዎች ሰላም የማደፍረስ ዝግጅቶችና ትንኮሳዎች ተደርገው ሳይሳካላቸው በኢትዮዽያ ታሪክ ትልቅ እድገት የታየበት ዴሞክራስያዊ፥ ሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ በማካሄድ ኢትዮዽያዊን በፅናት አዲስ ታሪክ ፅፈዉ ኢትዮጲያ መርጣለች፥ ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
እንደሃገር ያሳካነው እጅግ ውጤታማ እና ታሪካዊ ምርጫ የህዝባችን ፣የአመራራችን፣ የአባሎቻችን ፣የደጋፊዎቻችን፣የሲቭክ ማህበራት ፣ የሚድያዎቻችን፣ ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም በገለልተኝነትና በከፍተኛ ዲሲፕሊን ትልቅ ሃገራዊ ሃላፊነታቸዉን የተወጡት የፀጥታ አካላትና የምርጫ ቦርድ በጥቅሉ ሁሉም ባለድርሻ አካል እንደ ሀገር ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላንን ቁርጠኝነትና በጋራ ያሳካነው ግብ መሆኑን ተግባብተናል ። ለዚህም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት እናመሰግናለን።
የድህረ ምርጫ ስራዎቻችን በውጤታማነት በመፈፀም ይህንን ፅኑ ህዝብ ለመካስ ያስቀመጥናቸዉን ግቦች በተሟላ መልኩ ለማሳካት ከመላው አመራራችን ጋር ተግባብተናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዛሬ በምርጫ ሥራዎቻችን አፈጻፀምና የድህረ ምርጫ ሥራዎቻችን በውጤታማነት በመከወን የያዝናቸውን ግቦች በተሟላ መልኩ ከማሳካት አንፃር የተገኙ ዉጤቶችን ከመላው የከተማችን አመራሮች ጋር ገምግመናል ።
7ኛውን ጠቅላላ ሃገራዊ ምርጫ በስኬት እንዳይጠናቀቅ ለማደናቀፍ በውጭም በውስጥም በጋራ በማበር በሚደያ ዘመቻዎች እና በተለያዩ ቅስቀሳዎች ሰላም የማደፍረስ ዝግጅቶችና ትንኮሳዎች ተደርገው ሳይሳካላቸው በኢትዮዽያ ታሪክ ትልቅ እድገት የታየበት ዴሞክራስያዊ፥ ሰላማዊና ተዓማኒ ምርጫ በማካሄድ ኢትዮዽያዊን በፅናት አዲስ ታሪክ ፅፈዉ ኢትዮጲያ መርጣለች፥ ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
እንደሃገር ያሳካነው እጅግ ውጤታማ እና ታሪካዊ ምርጫ የህዝባችን ፣የአመራራችን፣ የአባሎቻችን ፣የደጋፊዎቻችን፣የሲቭክ ማህበራት ፣ የሚድያዎቻችን፣ ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም በገለልተኝነትና በከፍተኛ ዲሲፕሊን ትልቅ ሃገራዊ ሃላፊነታቸዉን የተወጡት የፀጥታ አካላትና የምርጫ ቦርድ በጥቅሉ ሁሉም ባለድርሻ አካል እንደ ሀገር ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላንን ቁርጠኝነትና በጋራ ያሳካነው ግብ መሆኑን ተግባብተናል ። ለዚህም ሁሉንም ባለድርሻ አካላት እናመሰግናለን።
የድህረ ምርጫ ስራዎቻችን በውጤታማነት በመፈፀም ይህንን ፅኑ ህዝብ ለመካስ ያስቀመጥናቸዉን ግቦች በተሟላ መልኩ ለማሳካት ከመላው አመራራችን ጋር ተግባብተናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ መጋቢት እና ሚያዚያ ዜና መፅሔት
2018 ዓ.ም
ከሀገር በቀል ጥበብ እስከ መዲናዋ ውበት
አዲስ አበባን ከተፈጥሮ ጋር ያስታረቀው አረንጓዴ ልማት
አዲስ አበባ የተመሰረተችው ከተራራ እና ከውኃ ጋር በተያያዘ የሕይወት ዑደት ውስጥ ነው። እንጦጦ ለአዲስ አበባ የተፈጥሮ ውበቷና ከነፋስ መከላከያ መከታዋ ሲሆን፤ ቀጨኔ፣ ቀበና፣ ግንፍሌ፣ ቡልቡላ እና ሌሎችም ወንዞች ደግሞ የከተማዋ ዋነኛ የሕይወት መስመሮች ነበሩ።
ይህንን የቆየና የልማት አቅጣጫ በአዲስ እሳቤ ለመቀየር፣ አዲስ አበባ አረንጓዴ እና ተፈጥሮን ማዕከል ያደረገ መንገድ መያዝ ግድ ስላላት፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሪነት ይፋ የሆነውን ከተማዋን የማስዋብ ፕሮጀክት በመቅረጽ በ2011 ዓ.ም ወደ ተግባራዊ ስራ ተገብቷል።
በዚህ አዲስ መዋቅር ከተሰሩ በርካታ ስኬታማ ተግባራት መካከል የሚጠቀሰው የእንጦጦ-ቀጨኔ መድኃኔዓለም የወንዝ ዳርቻ ልማት፤ የተራራ፣ የሸለቆ፣ የባህል፣ የሥራ ፈጠራ እና የአካባቢ ጥበቃ ታላቅ ድምር ውጤት ሆኗል።
ይህ ልማት ሀገር በቀል ማንነትንና እውቀትን ያከበረ መሆኑን ያሳየበት፣ የኮንሶዎችን የዘመናት ጎርፍ የመከላከል ጥበብ የእርከን ሥራ በተግባር የተገበረበት ነው፡
አረንጓዴ ልማት ውበት ብቻ ሳይሆን የጠንካራ ኢኮኖሚ መሰረትም ጭምር ነው። በእንጦጦ-ቀጨኔ እና በመላው አዲስ አበባ የሚገኙ የወንዝ ዳርቻ የልማት ሥፍራዎች አሁን ላይ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድልን መፍጠር ችለዋል።
ካፌዎች፣ የብስክሌት ሽያጭና ኪራዮች፣ እንዲሁም የቱሪስት አገልግሎቶች ለነዋሪው አዲስ የገቢ ምንጭ የፈጠሩ ሲሆን፤ በሌላ በኩል የሚፈጠሩት የባህል እና የገበያ ትስስሮች ለአካባቢው ልዩ ድባብ መፈጠሪያ እና ለማኅበረሰቡ ማንነትን መግለጫ መንገድ ሆነዋል።
በተለይም ቀጨኔን በሸክላ ሥራዋ፣ ሽሮሜዳን ደግሞ በሸማ ጥበቧ የምናውቃቸውን የእጅ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ምርቶቻቸውን ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ለጎብኚዎች በቀላሉ በሚደርስ እና ንጽህናው በተጠበቀ የሕዝብ ገበያ ለማቅረብ ሰፊ ዕድል አግኝተዋል።
ፅዱ ከተማ ማለት ውብ መንገድ ብቻ ሳይሆን ጤናማ ነዋሪ፣ የተጠበቀ ተፈጥሮ፣ የተነቃቃ ኢኮኖሚ እና ለትውልድ የሚተርፍ ማለት ነው።
በተደራሽነትም ሆነ በተገልጋይ እርካታ ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገቡ የሚገኙት የአዲስ መሶብ ማዕከላት
የ"አዲስ መሶብ" አንድ ማዕከላት ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት፡ ስራ ከጀመሩበት አጭር ጊዜ ጀምሮ ከ230 ሺህ በላይ ህዝብን በማስተናገድ 99 በመቶ የተገልጋዮች እርካታን አስመዝግበዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን እና ለአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የተወጠነው "አዲስ መሶብ" ፕሮጀክት ታላቅ ስኬት እያስመዘገበ ይገኛል።
እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 11 ማዕከላትን ለመክፈት ታቅዶ እየተሰራ ሲሆን፣ እስከ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 9ኙ ማለትም አራዳ፣ ቦሌ፣ ልደታ፣ ቂርቆስ፣ አዲስ ከተማ፣ ጉለሌ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ፣ ኮልፌ ቀራኒዮ እና የካ ሙሉ በሙሉ ወደ አገልግሎት ማስገባት ተችሏል።
የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ደሳለኝ ተረፈ (ኢ/ር) እንደገለጹት፣ ቀሪዎቹ የአቃቂ እና የለሚ ኩራ ማዕከላት የግንባታ አፈጻጸማቸው ከ99.5 በመቶ በላይ በመሆኑ በቀጣይ ቀናት ተመርቀው አገልግሎት መጀመር የሚያስችላቸው ዝግጅት ተጠናቋል።
ማዕከላቱ ስራ ከጀመሩበት አጭር ጊዜ ጀምሮ ከ230 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ያስተናገዱ ሲሆን፣ በተደረገው ዳሰሳም የተገልጋዮች እርካታ 99 በመቶ መድረስ መቻሉን ገልጸዋል።
ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በከተማ አስተዳደሩ ልዩ ድጋፍ የባለሙያ ቅጥር፣ ስልጠና እና መሰረታዊ ግብዓቶች ቀድመው በመሟላታቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል።
#Ethiopia
#addisababa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በሕንድ ታሪክ ለረጅም ጊዜ ያገለገሉ መሪ በመሆናቸውን የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ዛሬ ማለዳ በሶስተኛው ዙር የጀመርናቸውን 13.4 ኪሜ የሚሸፍነውን የኮሪደር ልማት ስራዎችን አፈፃፀም ገምግመናል።
የኮሪደሮቹ ልማት በአምስት የኮሪደር መስመሮች ተከፋፍለዉ እየተሰሩ ሲሆን እነርሱም:-
1- ከቦሌ መድሃኔዓለም እስከ ጎላጎል ( የቦሌ አትላስን መንገድ ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ) ፣
2- ከጎላጎል እስከ እንግሊዝ ኤምባሲ ( የቀበና መገናኛ መንገድን ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ) ፣
3- ከቦሌ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በሞኤኮ እስከ ቦሌ መገናኛ መንገድ ( የቦሌ አትላስን መንገድ ከቦሌ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ)፣
4- ከኢምፔሪያል በአደይ አበባ ስቴድዮም እስከ ሻላ መናፈሻ ፣
5-ከውሃ ልማት በአትላስ ያለውን እና ከአትላስ እስከ ቦሌ ሩዋንዳ ( የቦሌ አትላስ መንገድን ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ) በከፍተኛ ደረጃ የመንገድ ኔትወርኩን የሚያሰፋ፣ የንግድ ተቋማን፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገድ፣ የሳይክል መንገድ እና ለትራንስፖርት አገልግሎት ምቹ እንዲሆኑ ተደርገው እየተገነቡም ናቸው።
በተጨማሪም በርካታ የህዝብ አገልግሎት መስጫ ግንባታዎችን የያዘ ሲሆን የግንባታውም ሂደትም በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል።
በአደይ አበባ ስታዲየም ዙሪያ አስቀድመው የተጀመሩ የኮሪደርና ሌሎች መሠረተ ልማት ግንባታዎች
በፍጥነትና በጥራት እንዲከናወኑ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ከኮሪደሩ በተጨማሪም ለብዙ ዘመናት ተረስቶ የኖረ፣ ከሕዝብ ተወስዶ በግለሰቦች ያለአግባብ ተወሮ ለብዙ ብልሽት ተዳርጎ የኖረውን ቦታ ለህዝብ አገልግሎት እንዲውል ተደርጎ በመሰራት ላይ ይገኛል።
ፕሮጀክቶቹን እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ለማዋል በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ለህዝብ የገባነውን ቃል በተግባር መፈፀም መለያችን ነው!!
ዛሬ 9ኛውን አዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በየካ ክፍለ ከተማ አስጀምረናል።
የመንግስት አገልግሎት አሰጣጣችንን ቀልጣፋ፣ ፈጣን፣ ግልፅ እና ተደራሽ ለማድረግ በሁሉም ክፍለ ከተሞች መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ስራ በ2018 በሁሉም ክፍለ ከተሞች ስራ ለማስጀመር አቅደን ለህዝቡ ቃል በገባነው መሰረት እነሆ የዛሬውን ጨምሮ 9 ማዕከላትን ወደ ስራ አስገብተናል።
የአገልግሎት እንግልትን፣ እዚህም እዝያም ጉቦ የመጠየቅ ችግርን ለመቅርፍ፣ ተጠያቂነትን እና የህዝባችንን በክብር የመገልገል መብት ለማረጋገጥ፣ ህዝባችን ለአገልግሎት ፍለጋ ጊዜውንና ገንዘቡን ሳያባክን ያለውን ሃብት ለልማት እንዲያውለው ለማድረግ ያቀድነውን ግብ በማሳካት የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ አጠናክረን እንቀጥላለን ።
የየካ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ አዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል የመንግስት አገልግሎት በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የሰራችሁትን ሁሉ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
አዲስ አበባ፥ የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል!
የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎች እና የቀድሞው የክለቡ ተጫዋች አዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የተለያዩ ታሪካዊ መስህቦችን ጎበኙ።
መንግስት የስፖርት ቱሪዝም ለማሳደግ፣ የተለያዩ የስፖርት ማዕከላትን ከመገንባት ባሻገር፥ ሀገራዊ፣ ዓለማቀፉዊና አህጉራዊ ስፖርታዊ ፌስቲቫሎችን እንዲዘጋጁ በማድረግ ህብረተሰቡ እየተዝናና ጤናውን እንዲጠብቅ ምቹ ሁኔታን ተፈጥሯል።
የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በከተማችን የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የስፖርት ማዕከላትን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል።
የጤና መረጃ ስርዓት መጠናከር ለጤናው ዘርፍ መሻሻል ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ።
አ/አ/ጤና ቢሮ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ውጤታማ የመረጃ አያያዝ ስርዓትን ለመዘርጋት በርካታ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል።
ቢሮው ከJSI /DUP ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በጤና ተቋማት ላይ ባከናወነው የመረጃ አያያዝ ስርዓት መሻሻል ውጤቶች መመዝገብ ችለዋል።
በተመረጡ የጤና ፕሮግራሞች በተለይም በእናቶችና ህፃናት ጤና ፣ በጤና ማጎልበትና በሽታ መከላከል እንዲሁም በህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር እየተከናወኑ የሚገኙ የመረጃ አያያዝ ስርዓት ትንተና እና ማረጋገጥ ላይ ውይይት ተካሂዷል።
የጤና ተቋማት የመረጃ አያያዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱ በውይይቱ የተነገረ ሲሆን መረጃዎችን ከአመዘጋገብ ጀምሮ የአያያዝ እና ሪፖርት የማድረግ ስርዓታቸውን ይበልጥ ማዘመን እንደሚገባቸው ተመላክቷል።
በመርሐ-ግብሩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሐንጋቱ መሐመድ መረጃ ትልቅ ሃብት መሆኑን ገልፀው በአግባቡ በመያዝና በማደራጀት እንዲሁም ትክክለኝነቱን በማረጋገጥ ለውሳኔ ሰጪነት ሚናው ከፍተኛ እንዲሆን መስራት ይገባል ብለዋል።
የመረጃ አያያዝ ስርዓቱን ዲጂታላይዝ በማድረግ ፣ በማዘመን እና በማጠናከር የጤና አገልግሎት አሰጣጡን ማሻሻል እንደሚገባ የገለፁት ወይዘሮ ሐንጋቱ መሐመድ ለውጤታማነቱ የአቅም ግንባታ እና ቅንጅታዊ አሰራሩን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
በመርሐ-ግብሩ ላይ የቢሮው አመራሮችና ዳይሬክተሮች ፣ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የፌዴራልና የከተማ አስተዳደሩ ሆስፒታሎች እንዲሁም የክፍለ ከተማ የጤና መረጃ ባለሞያዎች ተገኝተዋል።
በአንተነህ ጋሻው
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
