Roha Tv/ሮሃ ቴቪ
الذهاب إلى القناة على Telegram
7 905
المشتركون
+724 ساعات
-77 أيام
-6330 أيام
جاري تحميل البيانات...
القنوات المماثلة
سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يونيو '26
يونيو '26
+86
في 0 قنوات
مايو '26
+77
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+62
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+76
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+75
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+109
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+81
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+141
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+246
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+213
في 1 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+102
في 3 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+119
في 1 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+143
في 1 قنوات
Get PRO
مايو '25
+183
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+449
في 1 قنوات
Get PRO
مارس '25
+691
في 1 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+353
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '25
+1 041
في 13 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+1 100
في 5 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+1 536
في 3 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+837
في 3 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+627
في 3 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+1 102
في 5 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+497
في 3 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+217
في 2 قنوات
Get PRO
مايو '24
+129
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+440
في 3 قنوات
Get PRO
مارس '24
+187
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+185
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '24
+112
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+220
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+129
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+1 558
في 0 قنوات
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 18 يونيو | 0 | |||
| 17 يونيو | +10 | |||
| 16 يونيو | +3 | |||
| 15 يونيو | +4 | |||
| 14 يونيو | +3 | |||
| 13 يونيو | +2 | |||
| 12 يونيو | +4 | |||
| 11 يونيو | +1 | |||
| 10 يونيو | +1 | |||
| 09 يونيو | +5 | |||
| 08 يونيو | +2 | |||
| 07 يونيو | +4 | |||
| 06 يونيو | +6 | |||
| 05 يونيو | +3 | |||
| 04 يونيو | +8 | |||
| 03 يونيو | +4 | |||
| 02 يونيو | +11 | |||
| 01 يونيو | +15 |
منشورات القناة
ተጠናክሮ በቀጠለው ፍልሰት አራት የብልፅግናው መከላከያ መሀንዲስ ክፍለጦር አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ጀግናው የራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦርን ተቀላቀሉ!
አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ
ተጠናክሮ በቀጠለው የአገዛዙ ሰራዊት ፍስልሰት በዛሬው ዕለት ግንቦት 20 ቀን 2018ዓ.ም መነሻቸውን ከሸዋ ጠቅለይ ግዛት ግራርያ (ፍቸ ሰላሌ) አውራጃ ያደረጉ የመከላከያ መሀንዲስ ክፍለጦር አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር የራስ አበበ አረጋይ ክፍለጦርን መቀላቀላቸውን ኮሩ በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል።
ፋኖን ከተቀላቀሉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት መካከል:-
1ኛ. አንሙት ሽመልስ
2ኛ. አወቀ ሞላ
3ኛ. አዱኛ አይሸሽም እና
4ኛ. ሀብታሙ አማረ የተባሉ የአገዛዙ ሰራዊት ፋኖን ሲቀላቀላ:-
✅ 4 ዘመናዊ ክላሽንኮቭ መሳሪያ
✅ 12 ካዝና
✅ ከ 500 በላይ የክላሽ ተተኳሽ
✅ ትጥቅን ጨምሮ የተለያዩ ወታደራዊ ሰነዶችን በመያዝ ጀግናው የአማራ ፋኖን ተቀላቅለዋል ሳል ኮሩ ገልጿል።
''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 20/2018ዓ.ም
| 2 | ጀግናው አቤ ደርሶ አምሳ አለቃ ቢሻውን ጨምሮ 8 የአገዛዙ ወታደሮችን በመግደል በጀግንነት ተሰዋ!
ግንቦት 19/2018
በአማራ ህዝብ ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ እየፈፀመ የሚገኘው አገዛዙ በትናንትናው ዕለትበአነደድ ወረዳ ዝንቅር ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን የግል ታጣቂ ጀግናው አቤ ደርሶን ለማፈን ከአምበር ከተማና ከሉማሜ ከተማ በርካታ የጠላት ሀይል ወደ ዝንቅር ቀበሌ በማምራት የጀግናው አቤ ደርሶን ቤት በመክበብ በቁጥጥር ስር ለማዋል ሙከራ ቢያደርጉም እንዳሰቡት ቀላል አልሆነም።
በአገዛዙ ወታደሮች አፈና እንደተፈፀመበት የተረዳው አቤ ደርሶ አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍ ቀድሞ የተረዳ ስለነበር መኗሪያ ቤቱ ላይ ያዘጋጀው ምሽግ ላይ በመሆን አምሳ አለቃ ቢሻው የተባለውን ፖሊስ እና ብሬን ተኳሽ ግምባር ላይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት የመጀመሪያ ጥይቱን አሳረፈ። ከዚያ በኋላ ጦርነቱ በይፋ ተጀመረ ቤቱን ዙሪያውን የከበበውን ሚኒሻ ፦ፖሊስና አድማብተናን ያዝረከርከው ጀመር
ከዚህ በኋላ ጀግናው አቤን መያዝ እንደማይችል የተረዳው የጠላት ሀይል የሚስቱን ወንድም እጅ እንድሰጥ ሽማግሌ አድርገው ይልኩታል ነገር ግን ጀግንነትን ከአባቱ በላይ ዘለቀ ተምራልና እጀን አልሰጥም በማለት እና የመጠውን አማላጅ ቦታ እንድይዝ በማድረግ መታኮሱን በመቀጠል ጠላትን አስጨንቆት አረፈደ
ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገደው አገዛዝ በቤንዚል እና ቦምብ ቤቱን ማቃጠል ሲጀምሩ እየተታኮሰ ቤቱን ለቆ በመውጣት አና 3 ክላሽንኮቭ በመማረክ ተጋድሎውን ይቀጥላል ይህን የሰሙት የ34ኛ ክ/ጦር አካል የሆኑት መብረቁ ሻለቃ እንድሁም ተድላ ጓሉ ሻለቃ እሱን ለማውጣት ከአገዛዙ ወታደሮች ጋር በአደረጉት ውጊያ ጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሰዋል።
ከንጋቱ 11:00 ሰዓት የጀመረው ውጊያ እስከ ቀን 11 ሰዓት ቆይቶ ጀግናው አቤ ደርሶ አምሳ አለቃ ቢሻው የተባለ የፖሊስ ብሬን ተኳሽ እና ቀሬ እጅግ የተባለ ሚሊሻን ጨምሮ በድምሩ8 የአገዛዙ ወታደሮችን እስከወዳኛው ሸኝቶ በክብር የወደቀ ሲሆን በዚህ የተበሳጨው የጠላት ሀይል ለእርሻ ስራ ይጠቀምበት የነበረ በሬውን በጥይት ደብድበው የገደሉ ሲሆን በጀግናው አቤ ደርሶ እና በ34ኛ ክ/ጦር ፋኖዎች ባደረጉት እልህ አስጨራሽ ውጊያ 11 አስከሬን እንድሁም በርካታ ቁስለኛ በመያዝ ወደመጣበት ፈርጥጧል።
ጀግናው አቤ ደርሶ ከኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ለሀገሩ ኢትዮጵያዊ ያገለገለ ሲሆን አብይ አህመድ በአማራ ህዝብ ላይ የሚያደርሰውን ግፍ በመረዳት ለወገኑ ሲል የጫካ ኑሮን በመምረጥ በአነደድ ወረዳ በማደራጀትና አቢዮቱን በመቀላቀል ጉልህ አሻራውን ያስቀመጠ ጀግና ነበር።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር ህ/ግንኙነት
| 2 431 |
| 3 | 81ኛ ክፍለ ጦር በአፓርታይዱ የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ ላይ ድል ተቀዳጀ!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር 81ኛ ክፍለጦር የጨረባ ምርጫ አስፈፅማለሁ ብሎ በቀን ቅዠት ውስጥ በሚደናበረው የአፓርታይዱ የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ ሰራዊት ላይ በሰሜን ወሎ ዞን ገረገራ ግንባር በተጠና ኦፕሬሽን መብረቃዊ ጥቃት ሲፈፀምበት ወደ አግሪት የተንቀሳቀሰው ደመነፍሳዊ ኃይል እግሬ አውጭኝ ብሎ ወደ ተመለደው የአይጥ ጎድጓዱ ገብቷል።
ግንቦት 19/2018 ዓ/ም ረፋዱን በተሰራው ኦፕሬሽን 12 ሲደመሰስ 17 ቁስለኛ ሁኗል። በጦር ጠበብቶቹ የ81ኛ ክፍለጦር አመራሮች የተመራዊ ኦፕሬሽን በኃይል የምርጫ ድጋፍ ውጡ እያለ ንፁሃንን ሲያሰቃይ የነበረውን የብልፅግና ስርዓት አቀንቃኞች ቅስም የሰበረ እንደነበር ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመላክታል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል!
ትግላችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 19/ 2018 ዓ.ም | 1 894 |
| 4 | የእንኳን ለ1447ኛው ሂጅሪያ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ውድ የተከበራችሁ የአማራ ህዝብ፣ የድርጅታችን አፋብን አባላት፣ ደጋፊዎችና መላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፤ በመጀመሪያ በአፋብን ምኒልክ ዕዝ ወታደራዊ አስተዳደር እና በራሴ ስም፣ ይህንን ታላቅና ቅዱስ የሆነውን የ1447ኛውን የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ምክንያት በማድረግ ከልብ የመነጨ ሞቅ ያለ አብዮታዊና ወንድማማችነታዊ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ።
የዒድ አል-አድሃ በዓል ፍጹም ለአላህ የመታዘዝ፣ የፅናት፣ የራስን ጥቅም አሳልፎ የመስጠትና የመስዋዕትነት ተምሳሌት ነው። ነቢዩ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) ለአላህ ትዕዛዝ ያሳዩት ፍጹም ታማኝነትና ታላቅ መስዋዕትነት፣ ዛሬም ድረስ ለእኛ ለሰው ልጆች ሁሉ በትግል፣ በፅናትና በታማኝነት ጎዳና ላይ ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ነው።
ክቡራትና ክቡራን!
ይህንን ታላቅ በዓል ስናከብር፣ ሕዝባችን ያለፈባቸውንና አሁንም እየተጋፈጣቸው ያሉትን ዘርፈ-ብዙ ፈተናዎች እያስታወስን ሊሆን ይገባል። የአማራ ሕዝብ በታሪኩ የአንድነቱን፣ የጀግንነቱንና የማንነቱን ክብር ለማስጠበቅ እጅግ ውድ የሆኑ መስዋዕትነቶችን ከፍሏል፤ ዛሬም እየከፈለ ይገኛል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ የሕዝባችንን መብት፣ ክብርና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ የጀመረውን ህጋዊና ፍትሃዊ ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል። ይህ በዓል እርስ በእርሳችን የምንደጋገፍበት፣ ለአካባቢያችን ሰላምና ደህንነት ዘብ የምንቆምበት እንዲሁም በትግል ጉዟችን ውስጥ ይበልጥ የምንጠናከርበት ሊሆን ይገባል።
በዚህ በተባረከ ቀን በተለይም፡-
አቅም የሌላቸውንና የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመጠየቅና በማካፈል ደስታቸውን ልናጋራቸው ይገባል።
ለሕዝባቸውና ለሀገራቸው ሲሉ በየድንበሩና በየቀበሌው መስዋዕትነት እየከፈሉ ያሉትን ጀግኖቻችንን ልናስባቸውና ልናከብራቸው ይገባል። የአማራን ህዝብ ዘላቂ አንድነትና ጥንካሬ ይበልጥ ለማጠናከር ቃል የምንገባበት ወቅት ሊሆን ይገባል።
ውድ ወገኖቼ!
አንድነታችን መከታችን፣ ፅናታችን ደግሞ የነፃነታችንና የዕድገታችን መሰረት ነው። ይህ የዒድ ለአማራ ሕዝብ እንዲሁም ለመላው የሰው ልጅ ሰላምን፣ ፍቅርን፣ አንድነትንና ድልን ይዞ እንዲመጣ እንመኛለሁ። አላህ ትግላችንን በድል፣ ምድራችንን በሰላምና በበረከት እንዲሞላልን እንማጸናለን።
በድጋሚ ለተከበረው የአማራ ፋኖ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የዒድ አል-አድሃ በዓል ይሁንላችሁ!
ኩሉ ዓም ወአንቱም ቢኸይር!
ዒድ ሙባረክ
አርበኛ ትዝታ በዛብህ
አፋብን ምኒልክ ዕዝ ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ሀላፊ | 1 793 |
| 5 | لا يوجد نص... | 1 544 |
| 6 | 🌙 እንኳን ለ1447ኛው የዒድ ዓል‐ዓድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ሮሃ ቴቪ በኢትዮጵያም እና በዓለም ዙሪያ ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል‐አድሃ (አረፋ) እንኳን አደረሳችሁ ይላል!
ይህ በዓል የመስዋዕትነት፣ የመተሳሰብ እና የሰብአዊነት እሴቶችን የሚያስታውስ በመሆኑ፣ የሀገራችን ሰላም፣ የሕዝባችን ፍትሕ እና እኩልነት የሚረጋገጥበት እንዲሆን እንመኛለን!
عيد أضحى مبارك
تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال
ኢድ ሙባረክ!
ሮሃ ቴቪ የሃገሬው! | 1 530 |
| 7 | 🌙 እንኳን ለ1447ኛው የዒድ ዓል‐ዓድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ሮሃ ቴቪ በኢትዮጵያም እና በዓለም ዙሪያ ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል‐አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም፣ በጤና እና በፍቅር አደረሳችሁ ይላል!
ይህ በዓል የመስዋዕትነት፣ የመተሳሰብ እና የሰብአዊነት እሴቶችን የሚያስታውስ በመሆኑ፣ የሀገራችን ሰላም፣ የሕዝባችን ፍትሕ እና እኩልነት የሚረጋገጥበት እንዲሆን እንመኛለን!
عيد أضحى مبارك
تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال
ኢድ ሙባረክ!
ሮሃ ቴቪ የሃገሬው! | 1 |
| 8 | 📢 አስቸኳይ ጥሪ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ቤተሰቦች!
የሕዝብ ድምፅ የሆነው ሚዲያችን በአገዛዙ የሳይበር ሚሊሻዎች የተቀናጀ ሪፖርት ምክንያት በድጋሚ ተዘግቷል። ነገር ግን የእውነት ድምፅ በአገዛዙ የተቀናጀ ዘመቻ አይታፈንም!
የነፃነት አንደበት የሆነው ኢትዮ 251 ሚዲያ በአዲስ ቻናል ተመልሷ ።
ሁላችሁም የሚከተሉትን በማድረግ አጋርነታችሁን እንድታሳዩ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡
1. ሰብስክራይብ ያድርጉ፦ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን አዲሱን ቻናል ይቀላቀሉ።
2. ለሌሎች ያጋሩ (Share)፦ መልዕክቱን ለወዳጅ ዘመድዎ በመላክ የሚዲያውን ተደራሽነት ያግዙ።
3. አስተያየት ይስጡ፦ በቪዲዮዎቹ ላይ አስተያየት በመስጠትና ላይክ በማድረግ ቻናሉ በሪፖርት እንዳይዘጋ ይከላከሉ።
አዲሱ የዩቲዩብ ቻናላችን ሊንክ፦
👉 https://youtube.com/@ethiomedia-v7p9p?si=T9nNjmqL5n4Jkt7N
ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት! | 2 420 |
| 9 | መጽሔተ አማራ (Journal of Amhara)
2ኛው ዓመታዊ ዓለም አቀፍ ሳይንሳዊ ጉባኤ ከግንቦት 23–24፣ 2026 በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት ሲልቨር ስፕሪንግ እየተካሄደ ነው።
ጉባኤው “የአማራን ጽናት ጽንሰ ሃሳብ አመክንዮ ዳግም መመልከት፦ ከህልውና ትግል ጉዞ ወደ ፖለቲካ መር መጻኢ አሳቤ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ ሲሆን፣ በአማራ ሕዝብ የህልውና ትግል፣ የጽናት ስልቶች እና የወደፊት ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮሩ ውይይቶች እየተካሄዱ ናቸው።
በመክፈቻ ንግግሩ፣ የመጽሔተ አማራ አመራር ተቋሙ የመጀመሪያ የምርምር ዕትሙን (Inaugural Issue) በይፋ ለንባብ ማብቃቱን እና ይህም በታዋቂው የአሜሪካ የኮንግረስ ቤተ-መጻሕፍት (Library of Congress) መመዝገቡን ገልጿል። ይህም መጽሔቱ በዓለም አቀፍ የምሁራን ዓለም ውስጥ እውቅናና ቋሚ አሻራ ለማሳረፍ የወሰደው ጠቃሚ እርምጃ መሆኑ ተጠቁሟል።
እንዲሁም በጉባኤው ላይ ከ12 በላይ በተለያዩ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ የምርምር ጥናቶች በአንጋፋና በወጣት ምሁራን ለውይይት እየቀረቡ መሆኑ ተገልጿል። | 2 387 |
| 10 | ትናንት በቤተ አማራ ምድር በከባድ መሣሪያ የተጨፈጨፉት ልጆቻችን እጣ ፈንታ ልብን ያደማል። የእነሱ ንጹህ ሕይወት በዚህ መልክ እየረገፈ፣ አረመኔዎቹ ግን 'ምረጡን' እያሉ በቁስላችን ላይ ጨው ይነሰንሳሉ።
ወገን ሆይ፣ ልብ እንበል!
'ጥይት በሚዘንብበት ምድር ላይ የዲሞክራሲ ድራማ ሊሠራ አይችልም፤ የቆሰለ ሕዝብ የሚፈልገው የምርጫ ሳጥን ሳይሆን የህልውና ጋሻ ነው!' >
ልጆቻችን እየታረዱ ዝምታን የመረጥን ዕለት የሕሊና ሞት ሙተናል። ይህንን በሕዝባችን ላይ እየተቀለደ ያለውን የፖለቲካ ሥላቅና ክህደት በአንድነት እንቃወም! ለተበደሉት ወገኖቻችን ድምፅ፣ ለተጨፈጨፉት ሕፃናት ደግሞ ፍትህ እንሁን! | 2 342 |
| 11 | لا يوجد نص... | 2 133 |
| 12 | የሸዋውና የወሎው ተጋድሎና የፋኖ ድል! እነ ጌታቸውና ጻድቃን ወደ ትግራይ! ብናልፍ አንዷለም ምን ገጠማቸው?
https://rumble.com/v79zjhs-440038000.html | 3 008 |
| 13 | በካናዳ ኦታዋ በአማራ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋትና የይስሙላ ምርጫ የሚቃወም ታላቅ ሰልፍ እየተካሄደ ነው!
በአማራ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት ወንጀል ለማውገዝ እና በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሊካሄድ የታሰበውን የይስሙላ ምርጫ ለመቃወም የተጠራ ታላቅ ሰልፍ ዛሬ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም (እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ሜይ 16 ቀን 2026) እየተካሄደ ይገኛል።
የአማራ ማህበራት ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ ሰልፍ ላይ፣ በመገኘት ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።
በስፍራው ከሚገኙ መረጃዎች መረዳት እንደሚቻለው፣ ሰልፈኞቹ "ሰላም በሌለበት ሕጋዊ ምርጫ ሊኖር አይችልም" እና "የጦርነት ቀጠናዎች የድምፅ መስጫ ቀጠናዎች አይደሉም" የሚሉ ጠንካራ መልዕክቶችን እያስተላለፉ ይገኛሉ። ሰልፉ በዋናነት በጦርነትና አለመረጋጋት ውስጥ ምርጫ ሊካሄድ እንደማይችል፣ ከምርጫው በፊት የጥይት ድምፅ መቆም እንዳለበትና ለሰላም ቅድሚያ እንዲሰጥ ይጠይቃል።
በተጨማሪም ምርጫን ሽፋን በማድረግ በአማራ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጥፋትና የደም መፋሰስ እንዲቆም፣ እንዲሁም ከድምፅ መስጠት በፊት የሰው ሕይወት ጥበቃ ቅድሚያ እንዲሰጠው ግፊት እየተደረገ ነው። ነጻነት በሌለበት ነጻ ምርጫ እንደማይኖርና ሕዝብ በጭቆና ሥር ሆኖ ድምፅ ሊሰጥ እንደማይችል ያሳሰቡት ሰልፈኞቹ፣ ለትክክለኛ ዴሞክራሲ የሽግግር ፍትሕ እንዲሰፍን፣ ከምርጫው በፊት መተማመን እንዲገነባና ለሀገር ቅድሚያ እንዲሰጥ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
"STOP AMHARA GENOCIDE!" (የአማራ የዘር ማጥፋት ይቁም!) የሚለው መሪ ቃል በጉልህ የሚታይበት ይህ ሰልፍ፣ በኢትዮጵያ ያለውን ወቅታዊ ቀውስ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅና ፍትሕን ለመጠየቅ የታለመ መሆኑ ተገልጿል። | 2 979 |
| 14 | لا يوجد نص... | 2 379 |
| 15 | በአማራ ህዝብ ጥላቻ ያበደው አገዛዝ፣ ዛሬም የዘመናችን ጨካኙ ጥቁር ሂትለር የንፁሀን አርሶ አደር መኖሪያ ቤትን ሙሉ በሙሉ በድሮን አውድሟል።
አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ
ግንቦት 08/2018ዓ.ም
የኢተዮጵያ ህዝብ የመከራ ቋት የሆነው የ21ኛው ክፍለዘመን የፋሽስታዊ አገዛዝ ዛሬም እንደለመደው የአማራን ህዝብ በከፍተኛ የወለድ ብድር በገዛው ድሮን ህዝብን የመጨፍጨፍ መደበኛ ስራው ያደረገው አገዛዝ የንፁሀን አርሶ አደሮችን መኖሪያ ቤት ሙሉ በሙሉ ሲያወድም፣ በወስጡ የነበሩ የቤት እንስሳቶችን ጨምሮ የቤት ንብረቶች በተፈፀመው የድሮን ጥቃት ወደ አመድነት ተቀይረዋል።
ትላንት ግንቦት 07 ቀን 2018ዓ.ም በአማራ ህዝብ ጥላቻ ያበደው የኦሆዴድ መራሹ ብልፅግና አገዛዝ በሸዋ ጠቅለይ ግዛት ተጉለትና ቡልጋ አውሩጃ በሞጃና ወደራ ወረዳ በሳሲት ክላስተር ስር በሚገኘው በጋውና ቀበሌ ከምሽቱ 3:30 ላይ በፈፀመው የድሮን ጥቃት የአቶ በቀለ ሸዋአበረ የተባሉ የጋውና ቀበሌ ነዋሪ የግል መኖሪያ ቤትን ሙሉ በሙሉ ማውደሙን ዕዙ አረጋግጧል።
"ትረፊ ያላት ነፍስ፣መከራ አያጠፋትም!" እንዲሉ አበው ጥቃቱ በተፈፀመበት ወቅት አቶ በቀለ ሸዋአበረ እና ቤተሰባቸው ለግል ማህበራዊ ጉዳይ ወደ ሌላ አካባቢ በመሄዳቸው የሰው ህይዎት ባይጠፋም፤ ነገር ግን ሀብትና ንብረታቸው በተፈፀመው የድሮን ጥቃት ሙሉ በሙሉ ወድሟል።
የአማራ ህዝብ መገልገያ ተቋማትን የጥቃት ኢላማ በማድረግ፣ ሀብትና ንብረቱን በመዝረፍ፣ የህዝባችንን የግል መኖሪያ ቤት በማውደም፣በአማራ ህዝብ ላይ ጅምላ ጭፍጨፋ በመፈፀም የሚታወቀው አረመኔው የብልፅግናው አገዛዝ ተጨማሪ የመጨፍጨፊያ የአገዛዝ ጊዜ ለማግኘት የይስሙላ የጨረባ ምርጫ ለማድረግ በድሮን እየጨፈጨፈ ያለውን ህዝብ "የይምረጡኝና ልግደላችሁ" ድምፅ እየጠየቀ ይገኛል።
በመሆኑም እንደ ህዝብ አማራ በመሆናችን ብቻ ሊያጠፋን የመጣውን ጨካኝ አገዛዝ ከጀግናው የአማራ ፋኖ ጋር በመቀናጀት በህዝባዊ ማዕበል እንቢተኝነት የጨፍጫፊውን አገዛዝ ዕድሜ ለማሳጠር ለሁለንተናዊ ትግል አማራዊ ግዴታህን ትወጣ ዘንድ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ለተከበረው ህዝባችን መልዕክቱን ማስተላለፍ ይወዳል።
ይህ በእንዲሕ እንዳለ የአገዛዙ ዙፋን አሥጠባቂ ሰራዊት በአሳግርት ወረዳ የማህበረሰብ የቁም እንስሳ መዝረፉን ነዋሪዎች ገለፁ። በአሳግርት ወረዳ ከጊናገር ከተማ ሜጢ ቀበሌ ልዩ ቦታው ጓላገር ጎጥ ተብሎ ከሚጠራው ስፋራ የአገዛዙ ሰራዊት የሁል ጊዜ የዘረፋ ተግባሩን በማህበረሰብ ላይ አድርሷል።
የተዘረፈባቸው የቀበሌው ነዋሪዎች:-
1ኛ. ጎሳ ልዑል ሰገድ ከ45 በላየ ከብትና ፍየሎች
2ኛ. ደመላሽ ሽመልሥ 36 ፍየሎችና 4 ከብቶች
3ኛ. ተገኝ ልሳነ 29 በጎችና ፍየሎች
4ኛ. ወንድዬ በለጠ 23 በግና ፍየል (5) ከብቶች
5ኛ. ልዩ ነች ወሰኔ ከ12 በላይ ፍየሎች እንደተዘረፉባቸው ተበዳዮች ገልፀዋል።
''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 08/2018ዓ.ም | 2 472 |
| 16 | لا يوجد نص... | 1 955 |
| 17 | ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ በምዕራብ ወሎ ግንባር በዘረ-ፈጁ እና ጨፍጫፊው የአገዛዙ ሰራዊት ላይ ድልን ተቀዳጀ!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክፍለጦር አትሮንስ ሻለቃ ከአማራ ሳይንት(አጅባር) ከተማና ከመሃል ሳይንት(ደንሳ) ከተማ ከወርቅ ማውጫ እስከ መሃል ሳይንት ትምህርት ቤት የጠላት ጥምር ጦርን ማለትም መከላከያ ሰራዊት፣ አድማ ብተና፣ ሚኒሻ እና የፓሊስ ሀይሎች ላይ በእነ አልሞ አይስቴ የቀኝአዝማች ይታገሱ አራጋው ልጆች ለወሬ ነጋሪት ሳይተርፍ ሙት እና ቁስለኛ አድርገውታል።
የአትሮንስ ሻለቃ አናብስቶች የጠላትን እንቅስቃሴ ቀድመው በማንበብና የጠራ መረጃ በመስራት ለማጥቃት የመጣውን ወኔውንም ጥበቡንም የተነጠቀውን የብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ደፈጣ ውስጥ በማስገባት አይቀጡ ቅጣት ቀጥተውታል። በዚህ አውደ ውጊያ የተገኙ ድሎች ሰብዓዊ ጉዳት፦
✅ የተደመሰሰ 45 የጥምር ጦር አባላት
✅ 38 ቁስለኛ
ከጠላት የተገኘ (የተማረከ) መሳሪያ፦
✅ ክላሽንኮቭ =9
✅አብራራው=3
✅ ፋል=1
✅የብሬን ተተኳሽ=1700
✅የክላሽ ተተኳሽ=812
✅ቦንብ=18
✅የወገብ ትጥቅ=18
ከዚህ በተጨማሪም ዙ-23 ከጥቅም ውጭ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ጠላት ሲጠቀምበት የነበረ ሶስት(3) መኪኖች ከጥቅም ውጭ ማድረግ ተችሏል ሲል የክፍለጦሯ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ኋላፊ አርበኛ እዮብ አሸናፊ አስታውቋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 06/2018 ዓ.ም | 1 611 |
| 18 | ከላሊበላ ወደ ሰቆጣ ይጓዝ የነበረ የብልፅግና ሰራዊት በደፈጣ ተመታ!
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር አካል የሆነው 30ኛ ክፍለ ጦር ቃኝዎች ባደረጉት የደፈጣ ጥቃት ከላሊበላ ወደ ሰቆጣ ይጓዝ የነበረውን የብልፅግና ሰራዊት ሰኞ ገበያ ከምትባል ቦታ ደፈጣ በመጣል ከባድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ እንዲያስተናግድ ተደርጓል።
ጥቃቱ የተፈፀመው ግንቦት 06/2018 ዓ/ም ከንጋቱ 12:30 ሰዓት እስከ ጧቱ 3:00 ሰዓት ገደማ ሲሆን ሁለት መድፍ፣ አምስት ኦራል፣ ሁለት ሲኖትራክ፣ ስድስት አይሱዙ፣ ሶስት ፓትሮል ከነሙሉ ቁሳቁሱ ግራና ቀኝ አጅቦ ለማሳለፍ በተንቀሳቀሰበት ጊዜ ፋኖዎቹ ገዥ ቦታና ደፈጣ በመያዝ የጠላትን ኃይል ሲያራግፉት አርፍደዋል።
በተደረገው የደፈጣ ጥቃት ኦፕሬሽን 16 የተደመሰሰና 11 የቆሰለ ሲሆን በደረሰበት መብረቃዊ የደፈጣ ጥቃት የተደናገጠው የብልፅግና አገዛዝ ጦር ዙ-23 መሳሪያን በመጠቀም በዘፈቀደ በመተኮስ የሁለት(2) አርሶ አደሮችን ቤትና ንብረት ማቃጠሉ ታውቋል።
መዳረሻዉ ድል እና ነፃነት የሆነዉ የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል።
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 06/2018 ዓ/ም | 1 338 |
| 19 | "የቆሻሻ ጽዳት" በሚል ሽፋን ሰላዮች በገጠር ከተሞች መሰማራታቸው ተጋለጠ!
የአብይ አህመድ አገዛዝ የሕዝቡን የትግል እንቅስቃሴ ለመሰለልና መረጃዎችን ለማሰባሰብ አዲስና ረቂቅ ስልት በመንደፍ ሰላዮቹን "የቆሻሻ ማጽዳት" በሚል ሽፋን እስከ ገጠር ትንንሽ ከተሞች ድረስ ማሰማራቱ ታውቋል።
ከውስጥ ምንጮች በተገኘ መረጃ መሠረት አገዛዙ ለእነዚህ ሰላዮች ከፍተኛ በጀት በመመደብ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሰላዮቹ በወር 30,000 ብር ቋሚ ደሞዝ የሚከፈላቸው ከመሆኑም በላይ በቀን 8,000 ብር የአበል ክፍያ እየተከናወነላቸው ልዩ ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ስምሪት ገብተዋል።
እነዚህ ሰላዮች በገጠር ከተሞች ቆሻሻን እንደሚያጸዱ ሠራተኞች በመምሰል በቡድንና በተናጠል ተሰማርተው የፋኖን እንቅስቃሴ፣ የደጋፊዎችን ሁኔታ እና የሕዝቡን የውስጥ ውይይቶች በቅርበት የመከታተል ተልዕኮ ተሰጥቷቸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በሕዝቡ መካከል በመቀላቀል የተሳሳቱ መረጃዎችን በመንዛትና ጥርጣሬን በመፍጠር ትግሉን ለማዳከም እየሠሩ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ ከፍተኛ ክፍያ የሚፈጸምበት የስለላ መዋቅር አገዛዙ የሕዝቡን ሕይወት ለማሻሻል ሳይሆን በገንዘብ ኃይል የሕዝብን የነፃነት ፍላጎት ለመጨፍለቅ ያለውን ጽኑ ፍላጎት የሚያሳይ በመሆኑ ሕዝቡና የትግሉ መሪዎች በእንደዚህ ዓይነት የሽፋን ሥራዎች እንዳይታለሉና አካባቢያቸውን በንቃት እንዲጠብቁ ጥሪ ቀርቧል። | 1 059 |
| 20 | ሰበር ዜና!
አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ 102ኛ ኮር የ12ኛ ክፍለጦርን ለማጥቃት የመጣውን የጥላት ሀይል በመልሶ ማጥቃት ድባቅ ተመታ!
ጠላት ግንቦት 07/2018ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ከተማ በቅርብ ርቀት በአድስ አለም በርና በስንደዶ በር የ12ኛ ክፍለጦርን ከበባ ውስጥ ለማስገባት በሁለት(2) አቅጣጫ ሙከራ ቢያደርግም ሳይሳካለት ውርደትን ተከናንቦ ተቀጥቅጦ ተመልሷል።
የቀድሞው የዞብል አምባ ክፍለጦር የሰራዊት አባላት የአሁኑ የ12ኛ ክፍለጦር ልማደኞቹ በሁሉም አቅጣጫ የመጣውን የአብይ አህመድ ቅልብተኛ ወታደር በመከላከልና በመልሶ ማጥቃት መጠነ ሰፊ ኪሳራ አድርሰውበታል።
በአርበኛ ሀብተማሪያም መንበሩ የሚመራው የ12ኛ ክፍለጦር በሻለቃ በመከፋፈል በሁሉም አቅጣጫ የመጣውን የጥላት ቅጥረኛና ወራሪ ሀይል ላይ ቀድሞ ገዥ ቦታዎችን በመያዝ በሞርተርና በድሽቃ እንዲሁም በመትረየስና በስናይፐር አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰውበታል።
ስግብግቡ፣ በእውር ድንብር የሚመራውና ስሌት የሌለው የብልፅግና ጨፍጫፊ አገዛዝ በአቀደውና በአለመው ልክ ሳይሳካለት ሙትና ቁስለኛውን ሳያነሳ እያንጠባጠበ ክንደ ብርቱዎቹን 12ኛ ክፍለጦር መቋቋም አቅቶት ወደ መጣበት በሽንፈት መመለስ ተችሏል።
የ102ኛ ኮር የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጆች የ12ኛ ክፍለጦር የሰራዊት አባላት የጦር ሰፈራቸውን ሳያስደፍሩ ዛሬም እንደትናንቱ ክብራቸውን በማስጠበቅ የሀይል የበላይነት ወስደውበታል። ጥላት የ12ኛ ክፍለጦር አሀድ የሆኑት በ1ኛ ሻለቃ፣በ2ኛ ሻለቃና በ3ኛ ሻለቃ ብርቱ ምት በመፍረክረኩና አስከሬን ለማንሳት ባለመቻሉ የአየር ሀይል ቢጠቀምም ክንደ ነበልባሎችን ማቆም ተስኖት ውሏል።
በመጨረሻም የአማራ ፋኖን ጥቃት መቋቋም ያቃተውና ቤተ-ክርስቲያን በማውደም የሚታወቀው አገዛዝ ሆርማት ሆኖ በግምት ባስወነጨፈው መዲፍ በዋጃ ከተማ የቅርብ ርቀት በተለምዶ ዋልካ መንደር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሁለት ሲቪልና ስድስት ከብቶችን ገድሏል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የ102ኛ ኮር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ምስራቅ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት 07/2018 ዓ.ም | 1 379 |
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
