cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍ📚

مشاركات الإعلانات
3 254
المشتركون
-124 ساعات
-207 أيام
-3930 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

📚⛪️የብርሃን እናት📚⛪️ ጸሐፊ ፦ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ አቅራቢ ፦ ✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት📚 ይህ መጽሐፍ በግሩም አጻጻፍ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ስለ እናታችን ስለ ድኅነታችን ምክንያት ድንግል ማርያም የብርሃን እናትነት የተጻፈና በዕንባ እየታጀቡ የሚያነቡት መጽሐፍ ነው ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊያን አድርሱ!!   #ሼር_ሼር_ሼር 🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒 https://youtube.com/channel/UCbuXpsXU7hDaFWELjzHlxdg     👆🏾𝙎𝙐𝘽𝙎𝘾𝙍𝙄𝘽𝙀 𝙉𝙊𝙒👆🏾 ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻  @Orthodox_Addis_mezmur @orthodox_spiritual_poems @Eotc_Books_By_Pdf @Lesangeez128    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺
إظهار الكل...
👍 2
💠ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ💠
🎧የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር🎶
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ግጥም📜
🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒
የሰሙነ ሕማማት ማክሰኞ #የጥያቄ_ቀን_ይባላል፦ ሰኞ ባደረገው አንጽሖተ ቤተመቅደስ ምክንያት፣ ሹመትን ወይም ሥልጣንን ለሰው ልጅ የሰጠ ጌታችን፣ ስለ ሥልጣኑ በጸሐፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋልና፤ የጥያቄ ቀን ይባላል፡፡ ጥያቄውም ከምድራውያን ነገሥታት፣ ከሌዋውያን ካህናት ያይደለህ ትምህርት ማስተማር፣ ተዓምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታትን፣ በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? ይህንንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ? የሚል ነበር፡፡ /ማቴ. 21፥23-27፣ ማር. 11፥ 7-35፣ ሉቃ.21፥23-27፣ ማር.11፥27-33፣ ሉቃ. 20፥1-8/፤ እርሱም ሲመልስ፤ «እኔም አንድ ነገር እጠይቃችኋለሁ፣ እናንተም ብትነግሩኝ በማን ሥልጣን እነዚህን እዳደርግ እነግራችኋለሁ፡፡ የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረ፣ ከሰማይ ነውን? ወይስ ከሰዉ? በእግዚአብሔር ፈቃድ፣ ወይስ በሰው ፈቃድ?» አላቸው፡፡ እነርሱም ከሰማይ ብንል ለምን አልተቀበላችሁትም ይለናል፤ ከሰው ብንል ሕዝቡ ሁሉ ዮሐንስን እንደ አባት ያከብሩታል፣ እንደ መምህርነቱ ይፈሩታልና ሕዝቡን እንፈራለን፤ ተባብለው ከወዴት እንደሆነ አናውቅም ብለው መለሱለት፡፡ እርሱም እኔም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ አልነግራችሁም አላቸው» ይህንንም መጠየቃቸው እርሱ የሚያደርጋቸውን ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንዲያደርግ አጥተዉት አልነበረም፣ ልቡናቸው በክፋትና በጥርጥር ስለተሞላ እንጂ፡፡ #የትምህርት_ቀንም_ይባላል፡- በማቴ. 21፥28፣ ማቴ. 25፥46፣ ማር.12፥2፣ ማር.13፥37፣ ሉቃ. 20፥9፣ ሉቃ. 21፥38 የሚገኙት ትምህርቶች ሁሉም የማክሰኞ ትምህርት ይባላሉ፡፡ በዚህ ዕለት በቤተ መቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረ፣ የትምህርት ቀን ይባላል፡፡ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ከሥጋዊ ነገር ርቆ በዚህ ሰሞን የሃይማኖት ትምህርት ሲማር ሲጠይቅ መሰንበቱም መጽሐፋዊ ሥርዓት ነው፡፡ አቤቱ ማረን ይቅር በለን   #ሼር_ሼር_ሼር 🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒 https://youtube.com/channel/UCbuXpsXU7hDaFWELjzHlxdg     👆🏾𝙎𝙐𝘽𝙎𝘾𝙍𝙄𝘽𝙀 𝙉𝙊𝙒👆🏾 ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻  @Orthodox_Addis_mezmur @orthodox_spiritual_poems @Eotc_Books_By_Pdf @Lesangeez128    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺
إظهار الكل...
👍 3
💠ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ💠
🎧የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር🎶
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ግጥም📜
🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒
📚⛪️ድርሳነ ማኅየዊ📚⛪️ አቅራቢ ፦ ✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት📚   #ሼር_ሼር_ሼር 🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒 https://youtube.com/channel/UCbuXpsXU7hDaFWELjzHlxdg     👆🏾𝙎𝙐𝘽𝙎𝘾𝙍𝙄𝘽𝙀 𝙉𝙊𝙒👆🏾 ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻  @Orthodox_Addis_mezmur @orthodox_spiritual_poems @Eotc_Books_By_Pdf @Lesangeez128    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺
إظهار الكل...
💠ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ💠
🎧የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር🎶
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ግጥም📜
🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒
📚⛪️መዝሙረ ዳዊት📚⛪️ አቅራቢ ፦ ✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት📚 📚 በሕማማት የሚፀለየውን የእያንዳንዱን ተከፍሎ ከታች ተቀምጧል። ❖ የዳዊት መዝሙራት በጠቅላላው መቶ ሃምሳ እና የነቢያት ጸሎት በቤተክርስትያን በሰባቱ ዕለታት ተከፋፍለው ይጸለያሉ ፤ እነርሱም ✍የሰኞ ከመዝሙር 1 – 30 (ፍካሬ ፥ አድኅነኒ ፥ አምላኪየ) ✍የማክሰኞ ከመዝሙር 31 – 60 (ብፁዓን ፥ ከመያፈቅር ፥ ለምንት ይዜኃር) ✍የረቡዕ ከመዝሙር 61 – 80 (አኮኑ ፥ እግዚኦ ኩነኔከ)፤ ✍የሀሙስ ከመዝሙር 81 -110 (እግዚአብሔር ቆመ ፥ ይኄይስ ፥ ስምዐኒ) ✍የአርብ ከመዝሙር 111 – 130 ( ብፁዕ ብእሲ ፥ ተፈሣሕኩ) ✍የቀዳሚት ከመዝሙር 131 – 150 (ተዘከሮ ፥ ቃልየ) እና ✍የእሑድ የነቢያት ጸሎት እና መኃልየ መኃልየ ዘሰሎሞን ናቸው።   #ሼር_ሼር_ሼር 🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒 https://youtube.com/channel/UCbuXpsXU7hDaFWELjzHlxdg     👆🏾𝙎𝙐𝘽𝙎𝘾𝙍𝙄𝘽𝙀 𝙉𝙊𝙒👆🏾 ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻  @Orthodox_Addis_mezmur @orthodox_spiritual_poems @Eotc_Books_By_Pdf @Lesangeez128    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺
إظهار الكل...
👍 1
💠ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ💠
🎧የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር🎶
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ግጥም📜
🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒
➦ 🧎‍♂ስንሰግድ ምን እያልን እንሰግዳለን ⁉️ ​​ሥርዓተ ጸሎት ሰሙነ ሕማማት ከሰኞ እስከ ዕሮብ  ካህናት እያዜሙ እየሰገዱ እኛም እየተቀበልን እያዜምን የምንሰግድበትን   ሥርዓት ለማውቅ እና ለመፈፀም ከስር ያንብቡ ❖ የጸሎተ ሐሙስና የዕለተ ዓርብ ሥርዓተ ጸሎት ! 👉 ከሰኞ ጀምሮ እስከ ዓርብ ድረስ ባሉት ቀናት ውስጥ  በመጀመሪያ ዲያቆኑ ቤተ ክርስቲያኑን ሦስት ጊዜ ዞሮ ደወል ካሰማ በኋላ መቶ አምሳው ዳዊት ይታደልና ይደገማል፡፡ የሰባት ቀናት ውዳሴ ማርያምና አንቀጸ ብርሃን  እስከ ይዌድስዋ  ድረስ ታድሎ ይደገማል፡፡ ከዚያም “እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ዓመ ከመ ዮም ያብጽሐኒ ያብጽሕክሙ አግዚአብሔር በፍሥሓ ወበሰላም” ተብሎ አቡነ ይደገምና  በዐራቱም ወንጌላት መሠረት ለእያንዳቸው በእየዕለቱና  ሰዓቱ የተመደበውን አቡነ ካህናቱ በቀኝና በግራ እየተፈራረቁ  ይመራሉ፡፡ ካህናቱና ሕዝቡም ይቀበላሉ፡፡ በመቀጠል፡- (ትእዛዝ፡ ሕዝቡ በጸሎት በተሰበሰቡ ጊዜ ጠዋት ወይም በ3፣ በ6፣በ9፣ በ11ሰዓተ መዓልት መጀመሪያ ሕዝቡ እየሰገዱና እየተከተሉ እንዲህ ይበሉ፡፡ ) ✥ "ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም ፡፡" ✥ "አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም፡፡" ✥ " ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም፡፡ " ✥ " ኃይልየ ወጸወንየ ውእቱ እግዚእየ፤ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኰቴት ፡፡" ትእዛዝ፡ በዚህ ጊዜ ካህኑ እየተከተሉ አቡነዘበሰማያት ይድገሙ ። ይህን የላይኛውን ጸሎት እያመላለሱ ከአቡነ ዘበሰማያት ጋር 12 ጊዜ ይበሉ ❖ " ለአምላክ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም፡፡ ❖ "ለሥሉስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለማሕየዊ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለዕበዩ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖"ለእዘዙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለመንግሥቱ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ስለልጣኑ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለኢየሱስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"፡፡ "ለክርስቶስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለሕማሙ  ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"፡፡ ❖ "ለመስቀሉ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም፡፡ " ትእዛዝ፡- ይህ ሦስት ጊዜ እየተመላለሰ ይባላል፡፡በመጨረሻም የሚከተለውን ሦስት ጊዜ እያመላለሱ ይበሉ፡፡ ❖ "ለከ ይደሉ ኃይል፣ ወለከ ይደሉ ስብሐት ወለከ ይደሉ አኰቴት ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም" ትእዛዝ፡- ካህኑ ‹ጸልዩ በእንተ ጽንዓ ዛቲ . . .› ብሎ በሚያነብ ጊዜ በየምዕራፉ "እግዚኦ ተሳሃለነ" እየተባለ ይሰገዳል፡፡ ትእዛዝ፡- ከዚህ ሁሉ በኋላ ሕዝቡ የሚከተሉትን ጸሎት በግራና በቀኝ ይበሉ፤ "ክርስቶስ አምላክነ፤ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ በሕማማቲሁ ቤዝወነ፤  ንሰብሖ ወናልዕል ስሞ ኅቡረ፤ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በዕበየ ሣህሉ" (በዐርብ) ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ ይባላል፡፡ ትእዛዝ፡- ቀጥሎም ሕዝቡ በሁለት ክፍል ሆነው የሚከተለውን ጸሎት ሁለት ጊዜ በመከታተል አንድጊዜ በማስተዛዘል ይበሉት፡፡ ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤#ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ #አብኖዲ  ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን #ናይን፣ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን ፤ #ታዖስ ናይን፣ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ #ማስያስ ናይን፣ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ #ኢየሱስ ናይን፣ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ #ክርስቶስ ናይን፣ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ #አማኑኤል ናይን፣ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ #ትስቡጣ ናይን፣ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን ትእዛዝ፡- ከዚህ በኋላ ኪርያላይሶን አርባ አንድ ጊዜ ይባላል፡፡ ይኸውም  በአንድ ወገን 20 ጊዜ በሌላው ወገን 21 ጊዜ በጠቅላላው 41 ጊዜ ኪርያላይሶን  ኪርያላይሶን  ኪርያላይሶን  እየተባለ ይሰገዳል፡፡ በመጨረሻ ጊዜ፡- ✥ ስብሐት ለእግዚአብሔር ኪያነ ዘፈጠረ ከመ ናምልኮ (እናመልከው ዘንድ ለፈጠረን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል)፡፡ ✥ ስብሐት ለማርያም እመ አምላክ እግእዝትነ ወመድኃኒትነ (እመቤታችንና መድኃኒታችን ለሆነች ለአምላክ እናት ለማርያም ምስጋና ይገባል)፡፡ ✥ ስብሐት ለመስቀለ ክርስቶስ ዕፀ መድኃኒት ኃይልነ ወፀወንነ(ኃይላችን መጠጊያችን ለሆነ ድኅነት ለተገኘበት ለክርስቶስ ምስጋና ይገባል)፤፤ ጸሎተ ሃይማኖትን ሐመ  እስከ ሚለው ድረስ መድገም ነው፡፡  /ከሰኞ እስከ ረቡዕ ይባላል/   #ሼር_ሼር_ሼር 🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒 https://youtube.com/channel/UCbuXpsXU7hDaFWELjzHlxdg     👆🏾𝙎𝙐𝘽𝙎𝘾𝙍𝙄𝘽𝙀 𝙉𝙊𝙒👆🏾 ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻  @Orthodox_Addis_mezmur @orthodox_spiritual_poems @Eotc_Books_By_Pdf @Lesangeez128    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺
إظهار الكل...
👍 2
💠ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ💠
🎧የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር🎶
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ግጥም📜
🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒
📚⛪️ሰይፈ ሥላሴ ወ ሰይፈ መለኮት📚⛪️ አቅራቢ ፦ ✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት📚 #ሼር_ሼር_ሼር 🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒 https://youtube.com/channel/UCbuXpsXU7hDaFWELjzHlxdg     👆🏾𝙎𝙐𝘽𝙎𝘾𝙍𝙄𝘽𝙀 𝙉𝙊𝙒👆🏾 ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻  @Orthodox_Addis_mezmur @orthodox_spiritual_poems @Eotc_Books_By_Pdf @Lesangeez128    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺
إظهار الكل...
👍 1
💠ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ💠
🎧የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር🎶
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ግጥም📜
🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒
​​#በሰሙነ_ሕማማት_የሚፈጸሙ_ሥርዓቶች 1, #ስግደት :- በሰሙነ ሕማማት 41 ጊዜ ኪርያላይሶን 12 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት እየተዜመ እጅግ አብዝቶ ይሰገዳል። 2, #ጸሎት :- በሰሙነ ሕማማት ከ24 ሰዓት ውስጥ 10 የጸሎትና የንባብ ሰዓታት ይገኛሉ እነዚህም ከጠዋቱ 1 ሰዓት; 3ሰዓት; 6ሰዓት; 9ሰዓት; 11ሰዓት እንዲሁም ከምሽቱ 1 ሰዓት; 3ሰዓት; 6ሰዓት; 9ሰዓት; 11ሰዓት ናቸው። በእነዚህም ሰዓታት የጌታን ስቃይ ለማዘከር መዝሙረ ዳዊትና ግብረ ሕማማት ድርሳነ ማኅያዊ አብዝተው ይጸለያሉ። 3, #ጾም :- በሰሙነ ሕማማት ብዙ አዝማደ መባልዕት / አዘውትረን የምንመገባቸው ምግቦች አይበሉም። በዚህም ሳምንት እስከ ምሽቱ #አንድ_ሰዓት እንድንጾም; ይኸውም ቆሎ;ዳቦ;ወኃና ጨው ብቻ እንደታዘዙ በግብረ ሕማማት ላይ ተጽፎ ይገኛል። 4, #አለመሳሳም :- አይሁድ ጌታችንን ለመስቀል እየተንሾካሾኩ ስለተመካከሩና ይሁዳ ጌታችንን በመሳም አሳልፎ ስለሰጠው መሳሳም አይፈቀድም። መስቀልም በዘመነ ኦሪት የወንጀለኛ መቅጫ የእርግማን ምልክት ስለ ነበር ጌታችን በክቡር ደሙ ቀድሶ የድል አርማ እስኪያደርግልን ድረስ አንሳለመውም ገላ.3:13 ማቴ.10:38 ማቴ. 26:29 5. #አክፍሎት :- እመቤታችን; ያዕቆብና ዮሐንስ የጌታችን ትንሳኤ ሳናይ እህልና ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሳኤው መቆየታቸውን በማሰብ የሚጾም ነው። 6, #ጉልባን :- ከባቄላ ከስንዴ ከገብስ የሚዘጋጅ በጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ሲሆን ትውፊቱም የስቅለቱ ሐዘን መግለጫ ነው። 7, #ጥብጠባ :- ይህ ምዕመናን በሰሙነ ሕማማት የፈጸሟቸውን ኃጢአቶች ለካህን እየተናዘዙ በወይራ ቅጠል ቸብቸብ እየተደረጉ ስግደት የሚቀበሉበት ነው። ይህም የጌታ ምሳሌ ነው። 8, #ቄጠማ :- ጌታችን ብርሃነ ትንሳኤዉን እንደገለጠልን የምናስብበት ሲሆን የእሾህ አክሊል በመድፋቱ ምሳሌም በራሳችን ላይ እናስረዋለን። እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻም ወድካም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም።   #ሼር_ሼር_ሼር 🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒 https://youtube.com/channel/UCbuXpsXU7hDaFWELjzHlxdg     👆🏾𝙎𝙐𝘽𝙎𝘾𝙍𝙄𝘽𝙀 𝙉𝙊𝙒👆🏾 ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻  @Orthodox_Addis_mezmur @orthodox_spiritual_poems @Eotc_Books_By_Pdf @Lesangeez128    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺
إظهار الكل...
💠ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ💠
🎧የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር🎶
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ግጥም📜
🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒
👉🏾ሰሙነ ህማማት 👉🏾የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ወዳጆች ወገኖች ከኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍ ቻናል የሚተላለፈውን ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት በያላችሁበት የምትከታተሉ በእግዚአብሔር ሰላምታ ሰላም እንላችኋለን፤ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን እያልን፤ ዛሬ በርዕሱ እንደተጠቀሰው " ሰሙነ ህማማት " በሚል ርዕስ ነው የምንነጋገረው፣ አንብባችሁ ትማሩበት ዘንድ አደራ እንላለን፦የሰሙነ ሕማማት ሰኞ" መርገመ በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው"ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሆሣዕና ዕለት "ቢታኒያ አድሮ በማግሥቱ ከቢታኒያ ሲመጡ ተራበ" ማርቆስ ምዕራፍ 11ቁጥር 11-12፣ ቅጠል ያላት በለስ ከሩቅ አይቶ ወደ በለሲቱ ቀረበ፣ ነገር ግን ከቅጠል በቀር ፍሬ አላገኛባትም "ከአሁን ጀምሮ  ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ ብሎ ረገማት" በለስ የተባለች ቤተ "እስራኤል" ናት፣ ፍሬ የተባለች "ሃይማኖትና ምግባር" ናት፣ ከእስራኤል ፍቅርን ሃይማኖት ምግባርን ፈለጋ አላገኘም፣ እስራኤልም "ሕዝብ እግዚአብሔር መባል እንጂደግ ሰው አይገኝብሽ ብሎ ረገማት በመረገሙ ምክንያት እርሱ ከለያቸው በስተቀር ደግ ሰው ጠፋብት፡፡ በለስ "ኦሪት ናት" ኦሪት በዚህ ዓለም ስፋነ ቢያገኛት ኦሪትና ነቢያት ልሽር አልመጣሁም፣ ልፈፅም እንጂ በማለት ፈፀማት፣ ሕገ ኦሪትን ከመፈጸም በቀር በእርሱ ድህነት አላደረገባትምና፤ ፍሬ በአንቺ አይሁን አላት፣ ድህነት በአንቺ አይደረግብሽ ብሏታልና እንደ መድርቅ ፍጥና አለፋት በለስ ኃጢአት ናት የበለስ ቅጠል ሰፊ እንድሆነች ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፋና አገኛትበለስ ሲበሉት ይጠፍጣል ቆይቶ ግን ይመራል፣ ኃጢአትም ሲሠሩት ደስ ደስ ያሰኛል፣ ኋላ ግን ያሳዝናል፣ ወደ እርሷም ሄዶ ማለትም ከኃጢአት ጋር ዋለ፣ ኃጥእ ከመባል በቀር በአንደበቱ ሐሰት በሰውነቱ ክፋት እንዳልተገኘበት ለማመልከት ፍሬ አላገኘባትም አለ፡፡ በአንቺ ፍሬ አይገኝ የሚለውም በኃጢአት ፍዳ ተይዞ የሚቀር ዓይኑን ለማለት ነው፣ ስትረገም ፈጥና መድረቋም በአዳም ምክንያት ያገኛትን ዕዳ በደል በእርሱ ካሣነት እንደጠፋችልን ለመግለፅ ነው አንጸሆተ ቤተ መቅደስ የተፈጸመበት ዕለት ነው፣ ጌታችን በለስን ከረገማት በኋላ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ፣ ቤተ መቅደስ፣ ቤተ ጸሎት፣ ቤተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ "ቤተ ምስያጥ (የንግድ ቤት) ሆነ ቢያገኘው "ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች፣ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አድርጋችኋት" ብሎ የሚሸጡትን ሁሉ ገለበጠባቸው፣ገርፎም አስወጣቸው፣ ይህም የሚያሳየው ማደሪያው ቤቱ የነበርን የአዳም ልጆች ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታችን ሁሉ እንዳራቀልን የሚገልፅ ነው፡፡ አቤቱ ማረን ይቅር በለን   #ሼር_ሼር_ሼር 🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒 https://youtube.com/channel/UCbuXpsXU7hDaFWELjzHlxdg     👆🏾𝙎𝙐𝘽𝙎𝘾𝙍𝙄𝘽𝙀 𝙉𝙊𝙒👆🏾 ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻  @Orthodox_Addis_mezmur @orthodox_spiritual_poems @Eotc_Books_By_Pdf @Lesangeez128    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺
إظهار الكل...
1
💠ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ💠
🎧የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር🎶
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ግጥም📜
🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒
📚⛪️ግብረ ሕማማት📚⛪️ 📕ይህን ግብረ ሕማማት የሚለው መጽሐፍ 261Mb የነበረ ሲሆን እኛ ሁሉም የኦርቶዶክስ አማኝ ሊያነበው ይገባል ብለን በ150Mb አቅርበነዋል። አቅራቢ ፦ ✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት📚   #ሼር_ሼር_ሼር 🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒 https://youtube.com/channel/UCbuXpsXU7hDaFWELjzHlxdg     👆🏾𝙎𝙐𝘽𝙎𝘾𝙍𝙄𝘽𝙀 𝙉𝙊𝙒👆🏾 ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻  @Orthodox_Addis_mezmur @orthodox_spiritual_poems @Eotc_Books_By_Pdf @Lesangeez128    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺
إظهار الكل...
💠ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ💠
🎧የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር🎶
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ግጥም📜
🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒
የዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት ገብርኄር ​​​​​​የዐብይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት ገብርኄር ይባላል፡፡ ገብርኄር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ስለ ታማኝ አገልጋይ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ስንኖር ለፈጣሪያችን ያለንን ታማኝነትና የምናገኘውን ዋጋ በመዋዕለ ሥጋዌው አስተምሯል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ለዜማ መክፈያነት የዐብይ ጾምን ሳምንታትን ሲከፍል ገብርኄርን ተጠቅሟልና እኛም ስለ ገብር ሄር ጥቂት እንበል፡፡ ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን በነቢዩ አንደበት አድሮ፤ “እከሥት በምሳሌ አፉየ፤ ወእነግር አምሳለ ዘእምትካት፤ አንደበቴን /ነገሬን/ በምሳሌ እገልጣለሁ፤ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ ታሪክና ምሳሌ እናገራለሁ” አለ፡፡ ይህም ማለት ወንጌልን በምሳሌ አስተምራለሁ፤ በመልከ ጼዴቅ ዘመን አስቀድማ የተሠራችና ታይታ የጠፋችውን ወንጌልን እናገራለሁ፡፡ ይህን ታላቅ ምሥጢር ሐዋርያው ሲያብራራ “ከመ በአሚን ያጸድቆሙ እግዚአብሔር ለአሕዛብ አቅደመ አሰፍዎቶ ለአብርሃም ከመ ቦቱ ይትባረኩ ኲሎሙ አሕዛብ ፤  በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ” ብሏል፡፡ /ገላ. ፫፥፰፣ መዝ. ፸፯፥፪ በዚሁ መሠረት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ለልዩ ልዩ ወገኖች በልዩ ልዩ ምሳሌ አስተምሯል፤ ከላይ በተገለጠው ኃይለ ቃል መነሻነት ሁለት ምሳሌያትና አንድ ቃለ ትንቢት ቀርበዋል፡፡ ከምሳሌያቱ የመጀመሪያው በዐሥሩ ደናግል አንጻር የቀረበው ምሥጢር ሲሆን፤ ሌላኛው ደግሞ ወጥተው ወርደው ነግደው ያተርፉበት ዘንድ ገንዘቡን ስለሰጠ አንድ ነጋዴ የሚናገረው ነው፡፡ የትንቢቱ ምሥጢራዊ ይዘት የሚያስረዳውም ስለ ኅልቀተ ዓለም አይቀሬነት ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ ዕትማችን ወጥተው ወርደው ነግደው እንዲያተርፉበት ከጌታቸው የተሰጣቸውን መክሊት ስለተቀበሉት አገልጋዮች ሕይወት እንመለከታለን፡፡ ፈጣሪያችን አእምሮውን ለብዎውን /ማስተዋሉን/ ያድለን፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማራቸው ምሳሌያዊ ትምህርቶች በቅዱስ መጽሐፋችን በሰፊው ተጽፈው እናገኛለን፡፡ የእነዚህ ትምህርታዊ ምሳሌዎች መሠረታዊ ሀሳብና ዓላማም የእግዚአብሔርን መንግሥት የምናገኝበትን የታማኝነትን ሥራ እንዴት መሥራት እንደሚገባንና መሥራትም እንደምንችል ማስተማር ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለመንግሥተ ሰማያት ምሥጢር ያስተማራቸው ብዙ ምሳሌዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህ ብዙ ምሳሌያዊ ትምህርቶች መካከልም እንዲያተርፉበት መክሊት ስለተሰጣቸውና ስለተመሰገኑት መልካም አገልጋዮች፣ እንዲሁም መክሊቱን በመቅበሩ ምክንያት በጌታው ስለተወቀሰውና ፍርድን ስለተቀበለው ሰነፍ ሰው ታሪክ፣ የታሪኩም ምሥጢር ምን እንደሚመስል የተጻፈው ትምህርት ነው። ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን ምሳሌ የተናገረው /ያስተማረው/ በሚከተለው መልኩ ነበር፤ ‹‹ወደ ሌላ ሀገር የሚሔድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ ሀገር ወዲያውኑ ሔደ፡፡ አምስት መክሊትም የተቀበለው ሔዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፣ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ፣ አንድ የተቀበለው ግን ሔዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ፡- ጌታ ሆይ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡ ጌታውም፡- መልካም አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡ ሁለት መክሊት የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፡፡ እነሆ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡ ጌታውም፡- መልካም አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሔጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት ፤ እነሆ መክሊትህ አለልህ አለው፡፡ ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፡- አንተ ክፉና ሐሰተኛ ባሪያ ካልዘራሁበት እንዳጭድ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር። እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር፡፡ ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት ዐሥር መክሊትም ላለው ስጡት። ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል። ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል፡፡ የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል የሚል ነው፡፡ መክሊት ጥንት የክብደት መለኪያ ነበር:: አንድ መክሊት 30 ኪሎ ግራም ያህል ነው፡፡ በዚህ ምሳሌ ላይ እንደተገለጸውም መክሊት የሚለው ቃል ገንዘብን ያመለክታል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምሳሌ ውስጥ እርሱን የምናገለግል ሁላችን እንደየዓቅማችን ማድረግ የሚገባንን መንፈሳዊ የአገልግሎት ሥራንና በአገልግሎታችን ውጤታማ በመሆናችንም ከእርሱ የምናገኘውን ዘለዓለማዊ ክብርና ዋጋን እንዲሁም መሥራት የሚገባንን ባለማድረጋችንም ምክንያት የሚገጥመንን መለኮታዊ ቅጣትን አመልክቶናል፡፡ በዚህ ምሳሌ ውስጥ ባለ አምስት የተባለው በቂና ፍጹም ትምህርት ተምሮ ሌላውን መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ የተካ ያወጣ ነው፡፡ በተመሳሳይም ባለ ሁለት የተባለው እንደ መጀመሪያው ሁሉ ተምሮ ሌላውን መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ ያወጣ ሲሆን ባለ አንድ የተባለው ደግሞ ተምሮ ሳያስተምር የቀረ በስንፍና በቸልተኝነት በማን አለብኝነት ሕይወት ተገድቦ የቀረ ሰው ነው፡፡ ሙሉውን ለማንበብ ከታች INSTANT VIEW የሚለውን በመጫን ያንብቡ                  👇👇👇 https://telegra.ph/የየዐቢይ-ጾም-ስድስተኛው-ሳምንት-ገብርኄር-ታማኝ-አገልጋይ-04-13 አቅራቢ ፦ ✞ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍት📚 👇🏾📽የግእዝ ትምህርት በyoutube🖥👇🏾 https://youtube.com/channel/UCbuXpsXU7hDaFWELjzHlxdg ➮ከወደዱት ያጋሩ share & join    🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻  @Orthodox_Addis_mezmur @orthodox_spiritual_poems @Eotc_Books_By_Pdf @Lesangeez128    🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺
إظهار الكل...
የየዐቢይ ጾም ስድስተኛው ሳምንት (ገብርኄር ታማኝ አገልጋይ)

ገብርኄር (6ኛ ሳምንት) ገብርኄር ታላቁን የጌታችንን ጾም ከጀመርን ስድስተኛ ሳምንት ላይ ደርሰናል፡፡ ይህን ሳምንት ቅድስት ቤተክርስቲያን «ገብርኄር» የሚል ስያሜ ሰጥታዋለች፡፡ ገብርኄር በጎ አገልጋይ ማለት ሲሆን የስያሜውን መነሻ የምናገኘው በዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴ ከሚነበበው የወንጌል ክፍል ማቴ.25-14-30 ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምሳሌ መስሎ ካስተማራቸው ትምህርቶች መካከል አንዱ የሆነው ይህ የዛሬው ወንጌል አስተማሪ የሆኑ መሠረታዊ ጉዳዮችን በውስጡ ይዟል፡፡ በተለይ ምንም እንኳን የቤተክርስቲያን ሓላፊነት የእገሌና የእገሊት ተበሎ ባይወሰንም ቤተ ክርስቲያን ባላት የአገልግሎት መዋቅር መሠረት የሓላፊነትን ቦታ ይዘው ለሚያገለግሉ ሰዎች አትኩሮት ሊሰጡባቸው የሚገባቸውን ነጥቦች ይጠቁማል፡፡ ይህን ለማየት ያመቸን ዘንድ ከታሪኩ የመጀመያ ክፍል በመነሣት ዋና ዋና የሆኑ ዐሳቦችን በአትኩሮት…

👍 6👏 1
💠ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ💠
🎧የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር🎶
⛪️ኦርቶዶክሳዊ ግጥም📜
🔔አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ሚድያ💒