ar
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

قناة بسيطة

إظهار المزيد
1 149
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

photo content
+2

photo content

photo content
+2

በተፈሪ መኮኮንን ፖ /ቴ /ኮ የሲቪል ማህበራት እና ህዝባዊ አደረጃጀቶች የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ። 🇪🇹ታህሳስ 08 /2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ/ም የኮሌጁ መሪ እቅድ ላይ ከአጋር የሲቪል ማህበረሰብ ማህበራት ጋር በጋራ ለመስራት ኮሌጁ ባቀዳቸው የጋራ ተግባራት ላይ ለመወያየት እና የትስስር ሰነድ ለመፈራረም የተዘጋጀ የሲቪል ማህበራት እና ህዝባዊ አደረጃጀቶች የውይይት መድረክ ።በመድረኩ ጥሪ የተደረገላቸው የመምህራን መህበር ፣ የአይነስውራን ማህበር ፣ የሙዚቀኞች ማህበር ፣ መስማት የተሳናቸው ማህበር ፣ የቀራጺያን ማህበር እና ሌሎች የሚመለከታቸው የሲቪል ማህበራት እና የኮሌጁ አመራሮችና ዳሬክቶሬቶች በተገኙበት ውይይት ተካሂዷል ። በመድረኩም የተፈሪ መኮኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 ዓ/ም መሪ እቅድ በዝርዝር ቀርቧል ። የኮሌጁን አላማ ለማሳካት የሲቪል ማህበረሰብ ማህበራት ድልዱይ በመሆን የስልጠና ፍላጎትን ከአቅርቦት መር ወደ ፍላጎት መር ለመቀየር ፣ትክክለኛ ፍላጎትን ለመለየት እና ተደራሽነትን ለማስፈት ጉልህ ሚና እንዳላቸው የገለፁት የኮሌጁ እቅድና በጀት ዳሬክቶሬት ወ/ሮ ንግስቲ ገ/ህይወት ኮሌጁ ለአካል ጉዳተኞች ሙሉ በሙሉ የትምህርት እድል በመስጠትና ምቹ በማድረግ ፣ የማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ልዩ ድጋፍ በመስጠት፣ ወቅቱን የዋጀ ስልጠና በጥራት እየሰጠ መሆኑን አስረድተዋል ።አክለውም ከሲቪል ማህበረሰብ ማህበራት የሰልጣኞች ቅስቀሳና ምልመላ በመስራት የስልጠና እድሎችን ማስተዋወቅ ፣የስነ ልቦና ስልጠናዎችን መስጠት እንዳለባቸው ገልፀው ኮሌጁ እያቀረበ የለውን አገልግሎት እና ተደራሽነት በምልክት ቋንቋ የትምህርት አገልግሎት ፣ በብሬል ድጋፍ ፣ የሴቶችን ኢኮኖሚ የሚያጎለብቱ የአጫጭር ስልጠና በተለያዩ ዘርፎች ስልጠና በመስጠት ፣ የስራ ፈጠራ ስልጠና ለወጣቶች በማሰልጠን በተጨማሪም በቴክኒክና ሙያ ሳምንት ላይበቴክኖሎጂና ክህሎት ውድድር ላይ ከሲቪል ማህበረሰብ ማህበራት አብሮ ለመስራት እና በፈጠራ እና ክህሎት ውድድር ላይ ስራዎችን ይዞ በመቅረብ መሀበራት መሳተፍ የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ ኮሌጁ አመቻችቷል ። በቀረበው የመወያያ መሪ እቅድም ላይ ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገ ሲሆን የተለያዩ ሀሳቦች ከመምህራን መህበር ፣ ከአይነስውራን ማህበር ፣ ከሙዚቀኞች ማህበር ፣ ከመስማት የተሳናቸው ማህበር ፣ ከቀራጺያን ማህበር እና የተፈሪ መኮንን ት/ቤት የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር ቀርበው ውይይት ተደርጎል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን ቡድን

photo content
+9

photo content

photo content

Long Image 12-17-2025 10.54
Long Image 12-17-2025 10.54

ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሙሉ የስነ ምግባር ዳይሬክቶሬት ባዘጋጀው የአንደኛ ዙር ስልጠና ላይ ያልገባችሁ ነገ ታህሳስ 9 ቀን 2018ዓ.ም ስለ ሚካሄድ ከጠዋቱ 2:30 ላይ በቴክኖሎጂአዳራሽ ISO ጎን ባለው አዳራሽ እንድትገኝ እናሳስባለን፡፡

photo content

የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ። 🇪🇹 ታህሳስ 6 /2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለአስራ ስምንተኛ ሳምንት ተካሄደ ። በእለቱ ሞያዊ የሆነ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት በሆቴልና ቱሪዝም የስልጠና ዘርፍ አሰልጣኝ የሆኑት አቶ ዘላለም ሲሳይ የተመጣጠነ ምግብ አመጋገብ ዙሪያ ጠለቅ ያለ ግንዛቤ ለኮሌጅ ማህበረሰብ የሰጡ ሲሆን የተመጣጠነ ምግብ መመገብ ለጤና ያለዉን ጠቀሜታ በጥልቀት በመረዳት ተጠቃሚ መሆን እንዳለብን አብራርተዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን ቡድን

photo content
+5

ባሳለፍነው ሳምንት

photo content
+7

አውደ ጥናቱ በዘልማድ  የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎችን በማስቀረት  የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎችን ለማቅረብ እንደሚያስችል ተገለፀ። 🇪🇹ታህሳስ 3/2018 ዓ.ም🇪🇹 የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ   የእሴት ሰንሰለት አዋጭነት ግምገማ አውደ ጥናት ማካሄድ ጀመረ። በዛሬው ዕለት በተከፈተውና ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚቆየው  አውደ ጥናት ዘጠኝ የእሴት ሰንሰለት ጥናቶች የሚቀርቡ ሲሆን በዚህም አልሙኒየም ስራ፣በአግሮ ፕሮሰሲንግ ወተት ምርት፣በከተማ ግብርና ዶሮ እርባታና እንስሳት መኖ፣ሚስማር ምርት፣ሸሚዝና ቲሸርት ምርት እንዲሁም በአውቶሞቲቭ አውቶ ቦዲ ትኩረታቸውን ያደረጉ ጥናቶች ቀርበው ይገመገማሉ። በአውደ ጥናቱ መክፈቻ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ ከሁሉም በላይ ባደረጉት ንግግር አውደ ጥናቱ ከዚህ ቀደም በዘልማድ  የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎችን በማስቀረት በዞኒንግ በተቀመጡ ስታንዳርዶች መነሻነት የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎችን ለማውጣት ያስችላል ብለዋል። በእሴት ሰንሰለት ላይ ሳይመሰረቱ በፍላጎት ዳሰሳ የሚካሄዱ ጥናቶች  ከአሁን በኃላ ተቀባይነት እንደማይኖራቸው የተገለፀ ሲሆን  ተግባር ላይ እንዲውሉ በማድረግ ሂደትም በትኩረት ይሰራል። ኃላፊዋ አክለውም የተለዩት ቴክኖሎጂዎች የሀገሪቱን የልማት ኮሪደር እና የመንግስት አቅጣጫ  መሰረት በማድረግ ከተማ አስተዳደሩን ተወዳዳሪ በማድረግ ኤክስፓርት ስታንዳርድ ምርት ለማቅረብ እንደሚረዳ አስረድተዋል። በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኖሎጂ ምርምር ኢኖቬሽንና ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ ቶልቻ በበኩላቸው በአውደ ጥናቱ ዘጠኝ የእሴት ሰንሰለት ጥናቶች ቀርበው እንደሚገመገሙ ገልፀዋል። በግምገማ ሂደቱ አልፈው  ችግር ፈቺነታቸው የተረጋገጡ  ቴክኖሎጂዎች የአዋጭነት ትንተና ሰነድ ተዘጋጅቶላቸው ወደ ምርት እንደሚገባ ጨምረው ገልፀዋል። አውደ ጥናቱ ቴክኖሎጂዎችን በብዛት በማምረት በተለይም እንደ ሀገር ተኪ ምርት  ለማምረት የሚያስችል  አቅም በመፍጠር ሂደት ጉልህ ሚና እንዳለው ተጠቁሟል። በአውደ ጥናቱ  የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ምክትል ዲኖችና ባለሙያዎች እንዲሁም አንቀሳቃሾች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። መረጃው የአአ ሥራና ክህሎት ቢሮ ነው

አውደ ጥናቱ በዘልማድ  የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎችን በማስቀረት  የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎችን ለማቅረብ እንደሚያስችል ተገለፀ። 🇪🇹ታህሳስ 3/2018 ዓ.ም🇪🇹 የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ   የእሴት ሰንሰለት አዋጭነት ግምገማ አውደ ጥናት ማካሄድ ጀመረ። በዛሬው ዕለት በተከፈተውና ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚቆየው  አውደ ጥናት ዘጠኝ የእሴት ሰንሰለት ጥናቶች የሚቀርቡ ሲሆን በዚህም አልሙኒየም ስራ፣በአግሮ ፕሮሰሲንግ ወተት ምርት፣በከተማ ግብርና ዶሮ እርባታና እንስሳት መኖ፣ሚስማር ምርት፣ሸሚዝና ቲሸርት ምርት እንዲሁም በአውቶሞቲቭ አውቶ ቦዲ ትኩረታቸውን ያደረጉ ጥናቶች ቀርበው ይገመገማሉ። በአውደ ጥናቱ መክፈቻ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ ከሁሉም በላይ ባደረጉት ንግግር አውደ ጥናቱ ከዚህ ቀደም በዘልማድ  የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎችን በማስቀረት በዞኒንግ በተቀመጡ ስታንዳርዶች መነሻነት የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎችን ለማውጣት ያስችላል ብለዋል። በእሴት ሰንሰለት ላይ ሳይመሰረቱ በፍላጎት ዳሰሳ የሚካሄዱ ጥናቶች  ከአሁን በኃላ ተቀባይነት እንደማይኖራቸው የተገለፀ ሲሆን  ተግባር ላይ እንዲውሉ በማድረግ ሂደትም በትኩረት ይሰራል። ኃላፊዋ አክለውም የተለዩት ቴክኖሎጂዎች የሀገሪቱን የልማት ኮሪደር እና የመንግስት አቅጣጫ  መሰረት በማድረግ ከተማ አስተዳደሩን ተወዳዳሪ በማድረግ ኤክስፓርት ስታንዳርድ ምርት ለማቅረብ እንደሚረዳ አስረድተዋል። በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኖሎጂ ምርምር ኢኖቬሽንና ሽግግር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ ቶልቻ በበኩላቸው በአውደ ጥናቱ ዘጠኝ የእሴት ሰንሰለት ጥናቶች ቀርበው እንደሚገመገሙ ገልፀዋል። በግምገማ ሂደቱ አልፈው  ችግር ፈቺነታቸው የተረጋገጡ  ቴክኖሎጂዎች የአዋጭነት ትንተና ሰነድ ተዘጋጅቶላቸው ወደ ምርት እንደሚገባ ጨምረው ገልፀዋል። አውደ ጥናቱ ቴክኖሎጂዎችን በብዛት በማምረት በተለይም እንደ ሀገር ተኪ ምርት  ለማምረት የሚያስችል  አቅም በመፍጠር ሂደት ጉልህ ሚና እንዳለው ተጠቁሟል። በአውደ ጥናቱ  የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ምክትል ዲኖችና ባለሙያዎች እንዲሁም አንቀሳቃሾች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። መረጃው የአአ ሥራና ክህሎት ቢሮ ነው

ፕሬስ ሪሊዝ
ፕሬስ ሪሊዝ

በተፈሪ መኮንን ፖ/ ቴ/ ኮ የሂወት ክህሎት እና የስራ ማፈላለግ ክህሎት ስልጠና ለ180 ሰልጣኞች ተሰጠ ። 🇪🇹ህዳር 29/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በጉ/ክ/ከ ስራና ክህሎት የተዘጋጀው በመንግስት የበጀት ድጋፍ የሚተገበረውን ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ስራና ክህሎት በኩል የመጡ 180 ሰልጣኞች ከህዳር 16/03/2018 ዓ/ም እስከ 30/03/2018 ዓ/ም ለአስራ ሁለት ቀናት በኮሌጅ የሂወት ክህሎት እና ስራ ማፈላለግ ክህሎት የሰለጠኑ አጫጭር ሰልጣኞች ተመርቀዋል ።በእለቱም የኮሌጁ አካዳሚክ ጉ/ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ለስልጠናው መሳካት ላበረከቱት አስተዋጽኦ የኮሌጅ ማህበረሰብን አመስግነው ሰልጣኞች በስልጠና ያገኙትን የስራ ላይ ክህሎት በማጎልበት ለታለመላቸው አላማ መሳካት የበኩላቸውን እንዲወጡ መልክት አሰተላልፈዋል ።በቀጣይም የስራ ላይ ክህሎት ለሰድስት ወር ሰልጣኞች በመረጡት ሙያ በኢንዱስትሪ የሚወስድ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን ለዚህም እራሳቸውን እንዲያዘጋጅ መልክት ተላልፏል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን ቡድን

TMPC 1917 - إحصائيات وتحليلات قناة تيليجرام