1 146
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
1 146
ውይይት ::
ዛሬ : ሐምሌ : ፳, ፳፻፲፮ ዓ.ም. ከሠዓሊ : ለይኩን : ግርማ : ጋር : በሥነ - ጥበብ : ትምህርት : ክፍል : ግሩም : ውይይት : አደረግን ፤ ከሕይወት : ልምዱና : በሥራዎቹም : ዙሪያ : ብዙ : ቁምነገሮችን : ተጨዋወትን ።
ሠዓሊ : ለይኩን : ግርማ : ከመጀመሪያዎቹ : የእንጦጦ : ፖሊ : ቴክኒክ : ኮሌጅ : ሥነ - ጥበብ : ትምህርት : ክፍል : ተመራቂዎች : አንዱ : ሲሆን ( በ፳፻፩ ዓ. ም. ) ፤ በብዙ : ወጣት : ሠዓሊያንና : ተማሪዎች : እጅግ : ተወዳጅ ፣ ከፍ : ያለ : ተጽዕኖ : የፈጠረ ፣ ምሳሌ : የሆነና : የራሱን : የሥነ- ጥበብ : መስመር : እያሰመረ : ያለ : ሠዓሊ : ነው ::
ለዚህም : ሠዓሊ : ለይኩን : ግርማን : በትምህርት : ክፍሉና : በተማሪዎቹ : ስም : ክብረት : ይስጥልን : እንላለን ::
ለዚህ : ዝግጅት : መሳካትም : ለተባበራችሁ: ተማሪዎችም : እንዲሁ :: 🙏🏿
ሐምሌ : ፳. ፳፻፲፮ ዓ.ም.
1 146
ሰላም ወንድሞች።
1) ICT
2) Constraction
3) Business
4) Automotive
5) Survey & Drafting
6) Hotel & Tourism
7) Garment & Textile
8) Electrical / Electronics
9) Manufacturing Technology
==========================
👉 ከላይ የተጠቀሳችሁ የስልጠና ዘርፎች በተጠየቀው መሰረት አሰልጣኞችን ለዳሰሳ ጥናት በመመደባችሁ እያመሰገንን የተላኩትን አሰልጣኞች ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በቡድን አዋቅረን ወደተግባር ስራ ለመግባት ዝግጁ እንሁን።
🙏መልካም ቀን🙏
1 146
ድጋፉን ለመስጠት ፍላጎት ያላችሁ ልበ ቀና ወዳጆች ለአቶ ስመኝ ሚደቅሳ በቴክኖሎጂ ህንጻ ስር ባለው ክፍል ውስጥ ማሰባሰብና መስጠት ትችላላችሁ!
1 146
#አሳዛኝ_ዜና
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ አመራሮች ፣ አሰልጣኞች ፣ ሰራተኞችና
ሰልጣኞቾ በጎፋ ዞን ፣ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለወዳጆቻቸዉና ቤተሰቦቻቸዉ መፅናናትን እንመኛለን!
ነፍስ ሄር!!!
ዉድ ኢትዮጵያዉያን !!
ድጋፋችንና ርብርባችን ያስፈልጋል!
በምንችለዉ ነገር ሁሉ እናስባቸዉ።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ
1 146
ለኮሌጁ ማህበረሰብ በሙሉ
የቲያትር ትምህርት ክፍል 1ኛ አመት የቀንና የማታ ሰልጣኞች በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን ትምህርት በተግባር የሚያሳዩበት እንዱሁም የሚመዘኑበት ልዪ የቲያትር ዝግጅት አጠናቅሯል።
'' #መሳ-ለመሳ '' - ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም (ረቡዕ) ከቀኑ 08:ዐዐ ጀምሮ፤
'' #ባለዳስ_እዳዎች '' አስቂኝ ኮሚዲ - ሐምሌ 18 ቀን 2016 ዓ.ም (ሀሙስ) ከቀኑ 08:ዐዐ ጀምሮ፤
''#አራቱ_ደባሎች ''- ሐምሌ 19 ቀን 2016 ዓ.ም (አርብ ) ከቀኑ 08:ዐዐ ጀምሮ፤
ማንኛውም የግቢዉ ማሕበረሰብ ይህን ደማቅ የኪነጥበብ ዝግጅት እንዲታደም የት/ክፍሉ ይጋብዛል ።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የቢዝነስ ትምህርት ስልጠና ዘርፍ ለማታ ሰልጣኞች
የተቋም ዉሰጥ ምዘና አካሄደ።
ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም
የቢዝነስ ትምህርት ስልጠና ዘርፍ በ2016 ዓ.ም በማታው የስልጠና መርሃግብር በ Marketing and Sales Management ዲፓርትመንት ለተቀበላቸዉ ሰልጣኞች በደረጃ 2 የተቋም ዉስጥ ምዘና (Institutional Assessment) አካሂዷል ። በምዘናዉ 33 ሰልጣኞች (ወንድ 6 ፣ ሴት 27 ) ወደሚቀጥለዉ ደረጃ ለመሸጋገር የተመዘኑ ሲሆን ምዘናዉም በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
ተመዛኞች በተሰጣቸዉ የጽሑፍና የተግባር መመዘኛ በጥቅሉ 84% ማምጣት የሚገባቸው ሲሆን ከተቀመጠው ነጥብ በታች ያመጡ ሰልጣኞች ከ10 ቀናት በኋላ የድጋሜ ምዘና ይወስዳሉ።
የምዘናዉን ሂደት ለመመልከት የተገኙት የትምህርት ክፍሉ ኃላፊ ለሰልጣኞች ስለምዘናዉ ማብራሪያ እና የማበረታች ንግግር ያደረጉ ሲሆን ምዘናው ለተከናወነበት የሆቴልና ቱሪዝም የስልጠና ዘርፍና ተባባሪ አሰልጣኞች በተቋማችን ውስጥ ለምናከናውነው የአንድነት ጉዞና ለተቀመጠው ግብ መሳካት ወሳኝነት ያለው በመሆኑ ምስጋናቸውን ገልጸዋል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዉድ የቻናላችን ቤተሰቦች በእንጦጦ ፖ/ቴ /ኮሌጅ በ2016 ዓ.ም የስራ ዘመን የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ እና የተሸለሙ የሥራ ክፍሎችና ሠራተኞች ዝርዝር ከታች ያለዉን ዶክመንት በመክፈት ይመልከቱ።
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
