1 149
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
1 149
+4
የካይዘን ልህቀት ማዕከል በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ያካሄደውን የዳሰሳ ጥናት ቀረበ ።
🇪🇹27/06/2018 ዓ.ም🇪🇹
የካይዘን ልህቀት ማዕከል በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ውስጥ ያለውን የሥራ ሂደት፣ የአመራር ሥርዓትና የአገልግሎት አሰጣጥ ነባራዊ ሁኔታ አስመልክቶ ያካሄደውን ጥልቅ የዳሰሳ ጥናት ውጤት አቀረበ።
አንጋፋው ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ያገኘውን ዓለም አቀፍ የጥራት እውቅና በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚያስችል የካይዘን የነባራዊ ሁኔታ ዳሰሳ ጥናት ውጤት ለኮሌጁ አመራሮች፣ ለዳይሬክቶሬቶች ፣አካዳሚክ ኮሚሽን አባላትና ለካይዘን አስተባባሪዎች ባቀረቡት በዚህ ጥናት ተቋሙ ቀደም ሲል የተቀዳጃቸውን የጥራት ስታንዳርዶች ይበልጥ ለማሳደግና ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር የካይዘን ፍልስፍና ያለውን ሚና ጉልህ እንደሆነ ገልፀዋል ።
ጥናቱ በተለይ በአካዳሚክ ዘርፍ፣ በቴክኒክ ስልጠና ክፍሎችና በአስተዳደራዊ ስራዎች ላይ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማጠናከር፣ ክፍተቶችን ደግሞ በካይዘን ቴክኖሎጂዎች ለመሙላት የሚያስችሉ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አካቷል።
የካይዘን ልህቀት ማዕከል ባለሙያዎች እንደገለጹት ይህ ጥናት አመራሩ የለውጥ ሂደቱን በባለቤትነት እንዲመራና ለታችኛው ሰራተኛ አርአያ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወንጀል መከላከል እና የጥበቃ ሰራተኛ ስነምግባር ስልጠና ።
🇪🇹26/06/2018 ዓ.ም🇪🇹
የወንጀል መከላከል ሲባል ቅድመ መከላከል ሲሆን የፍተሻ ስርአት ፣ የጥበቃ ስምሪት ፣የመኪና አፈታተሽ ፣ የሰው አፈታተሽ ፣የቀንና የማታ ስምሪት በዝርዝር ያካትታል ።
በተጨማሪም የጥበቃ ስነ ምግባር ምን መሆን እንዳለበት እና ቅንጅታዊ ስራዎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋራ ተቀናጅቶ መስራት ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የህንፃ አስተዳደር ዳሬክቶሬት አቶ አላዩ ጉትዬ እንደገለፁት ስልጠናው በመነን ፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ በኩል እየተሰጠ ሲሆን ስልጠናው የንድፈ ሀሳብና የተግባር ስልጠናዎችን ያካተተ መሆኑ ለማወቅ ተችሏል ።
ስልጠናው ከዚህ በፊት የተሰጠ መሆኑን አስታውሰው የጥበቃ ሰራተኛ በየጊዜው እራሱን በመፈተሽ እንዲበቃ ታስቦ የተዘጋጀ የማጠናከሪያ ግንዛቤ ማስጨበጫና የማነቃቂያ ስልጠና እንደሆነ አብራርተዋል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
አቶ ተሾመ ፈይሳ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአ/ጉ/ም ዲ እና ዋና ዲን ጊዜያዊ ተወካይ ከነበሩት አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ጋር የስራ ርክክብ አደረጉ ።
🇪🇹26/06/2018 ዓ.ም🇪🇹
በቅርቡ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን ሆነው የተሾሙት አቶ ተሾመ ፈይሳ ከቀድሞ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አ/ጉ/ም ዲ እና ዋና ዲን ጊዜያዊ ተወካይ ከነበሩት አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ጋር የስራ ርክክብ አደረጉ ።
አቶ ተሾመ ፈይሳ ከዚህ ቀደም ኮሌጁን በመሪነት ያስተዳደሩና በዘርፉ ሰፊ ልምድ ያላቸው ሲሆን፣ ከኮሌጁ የማኔጅመንት ቡድን ጋርም በቅርበት የመሥራት ልምድ እንዳላቸው ታውቋል።
አቶ ተሾመ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በቀጣይ ከኮሌጁ አመራሮች ጋር በቅንጅትና በተናቦ በመሥራት ኮሌጁን ወደ ተሻለ የአፈፃፀም ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን አስረድተዋል።
የኮሌጁ የማኔጅመንት ቡድን ለአዲሱ ዋና ዲን የእንኳን ደህና መጡ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን፣ ተቋሙ ለበለጠ ውጤት እንዲበቃ ከአዲሱ አመራር ጋር በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
ባለፉት ጊዜያት የዲኑን የሥራ ኃላፊነት ደርበው በመሥራት ኮሌጁን ሲያገለግሉ የቆዩትን የሥልጠና እና አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬን የማኔጅመንት ቡድኑ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋናና አክብሮቱን አቅርቧል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እየተከናወነ የሚገኘውን የማሽነሪዎች ጥገና ተጀመረ።
🇹25/06/2018 ዓ.ም🇪🇹
የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ የጥገና ቡድን በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውስጥ አቅምን በመጠቀም እየተከናወነ የሚገኘውን መጠነ-ሰፊ የማሽነሪዎች ጥገና በቦታው ተገኝቶ አስጀመረ።
የጥገናዉ ዋና ዓላማ ከየኮሌጁ በመጡ ባለሙያዎች አማካኝነት ለረጅም ጊዜ አገልግሎት ሳይሰጡ የቆዩና ብልሽት የገጠማቸውን ማሽነሪዎች ወደ ስራ ለማስገባት እየተከናወነ ያለውን ስራ ለማስጀመር እና ለመከታተ እንደሆነ ተገልጿል።
የኮሌጁ እና ከየኮሌጁ በመጡ ባለሙያዎች የራሳቸውን እውቀትና ክህሎት በመጠቀም የጥገና ስራውን እያከናወኑ መሆኑ ከፍተኛ ወጪን እንደሚያድን ተመልክቷል።
ለተለያዩ የሙያ ስልጠናዎችና ለማምረቻ ስራዎች የሚያገለግሉ ማሽነሪዎች ጥገና ተደርጎላቸው ወደ ስራ ለመመለስ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ ተረጋግጧል።
የክህሎት ሽግግር፦ ይህ የጥገና ሂደት ለባለሙያዎቹ ልምድ ከመሆኑ ባለፈ፣ ሰልጣኞችም በተግባር የተደገፈ ስልጠና ለመስጠት እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ተጠቁሟል።
የቢሮው የጥገና ቡድን አባላት በምልከታቸው ወቅት ባስተላለፉት መልእክት፣ ኮሌጁ የቆዩ ማሽኖችን በመጠገን ዳግም ለአገልግሎት እንዲውሉ እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታና ለሌሎች ተቋማትም አርአያ የሚሆን ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ የጥገና ዘመቻ በተቋሙ የሚገኙ የማስተማሪያ ግብዓቶችን ጥራት ከማሻሻሉም ባለፈ፣ ለከተማዋ የኢንዱስትሪ እድገትና ለስራ እድል ፈጠራ የሚሰጠው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑ ተመልክቷል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ አዲሱ የቴክኒክና ሙያ ፖሊስና ስትራቴጂ ለውጦች ላይ ለአስተዳደር ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ ።
🇪🇹25/06/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና (ቲቬት) ፖሊስ እና ስትራቴጂካዊ የለውጥ ነጥቦች ላይ ከለኮሌጁ የአስተዳደር ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ አካሄደ።
በኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ አማካይነት በዋናነት ትኩረቱን ያደረገው በ2000 ዓ.ም ተቀርጾ በነበረው ስርአት እና አሁን ተግባራዊ በሚደረገው የ2017 ዓ.ም አዲስ ስትራቴጂ መካከል ባሉ መሰረታዊ ልዩነቶችና መሻሻሎች ላይ ግንዛቤ ተሰቷል ። አዲሱ ስትራቴጂ ተቋሙን ከወቅታዊው የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ፍላጎት ጋር ለማጣጣም ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል።
ኮሌጁ በ2027 ዓ/ም የኢትዮጵያ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ሥርዓት የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ዋና ሞተር እንዲሆን የመሪነት ሚናውን ለመወጣት ማቀድንና ይህም አረንጓዴና ዲጂታል ኢኮኖሚ፣በክህሎት የበለፀገ፣ ሀገር ወዳድና ስራ ፈጣሪ፣ ከፍተኛ የፈጠራ ችሎታ ያለው የሰው ኃይል ማፍራትን እንደ ራዕይ ሰንቋል።
ይህንን ራዕይ ከግብ ለማድረስም ጥራት ያለውና በገበያ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ስልጠና በመስጠት፣ የኢንዱስትሪ እድገትንና ዘላቂ ልማትን የሚያረጋግጥ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂ ማፍራት የኮሌጁ ዋነኛ ተልዕኮ መሆኑ ተመላክቷል።
በመድረኩ ላይ በዝርዝር ከቀረቡት ነጥቦች መካከል በ11ዱ የቲቬት ዘረመሎች ላይ የተደረጉ ስር ነቀል ለውጦች ተጠቃሽ ናቸው። ከነዚህም መካከል የፋብሪኬሽን ቴክኖሎጂ እና የክህሎትና ቴክኖሎጂ ባንክ ግንባታ ፣ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን ፣ የመንግስትና የግል ባለሀብት ትስስር ፣ ሰልጣኞች በተግባር የተደገፈ ስልጠና እንዲያገኙና የስራ እድል እንዲመቻችላቸው ማጠናከር ፣ ኢንኩቤሽንና ቲቬት ኢንተርፕራይዜሽን ፣ የፈጠራ ስራዎችን ወደ ቢዝነስ መቀየርና የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን ፣ ሀገር ወዳድነትና ሰው ተኮር አሰራር ፣ በስነ-ምግባር የታነጸና ለሀገሩ የሚቆረቆር ባለሙያ መቅረጽ ላይ በትኩረት መሰራት እዳለበት ከስልጠናውና ውይይቱ ለማወቅ ተችሏል ።
በስልጠና ውይይቱ ላይ የተሳተፉ የአስተዳደር ሰራተኞች አዲሱ ስትራቴጂ ተቋማዊ አሰራርን ለማዘመንና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት ያለውን ፋይዳ እንደተገነዘቡ ገልፀዋል። ሰራተኞቹም ስትራቴጂው በተግባር ላይ እንዲውልና ዜጎች በየደረጃው ተመጣጣኝ እውቀትና ክህሎት እንዲያገኙ ለማድረግ የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለቴክስታይልና ጋርመንት አሰልጣኞች የአዶቤ ኢሉስትሬተር ስልጠና በፌደራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ተጀመረ።
🇪🇹25/06/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቴክስታይልና ጋርመንት ስልጠና ዘርፍ ለሚገኙ አሰልጣኞች የክህሎት ክፍተትን ለመሙላት የታለመ የ10 ቀናት የአዶቤ ኢሉስትሬተር ስልጠና ተጀምሯል።
ይህ ስልጠና በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አማካኝነት የሚሰጥ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም በዘርፉ ያለውን የዲጂታል ዲዛይን የክህሎት ክፍተት በመሙላት የሥልጠና ጥራቱን ማሳደግ ነው።
ለአሥር ተከታታይ ቀናት የሚቆየው የዚህ ስልጠና ሙሉ ወጪ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት የተሸፈነ ነው።
ፕሮጀክቱ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሚታዩ የክህሎት ክፍተቶችን በመለየትና ተግባራዊ ስልጠናዎችን በመደገፍ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
ስልጠናውን በመከታተል ላይ የሚገኙ ሰልጣኞች እንደገለጹት የቴክኖሎጂ ሽግግር አዶቤ ኢሉስትሬተር በዘመናዊው የጋርመንት ኢንዱስትሪ ውስጥ ለፋሽን ዲዛይንና ለፓተርን ዝግጅት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ ስልጠናው በዘርፉ የነበረባቸውን የረጅም ጊዜ የክህሎት ክፍተት እንደሚቀርፍላቸው ገልጸዋል።
ስልጠናዉ በእጅ ይሠሩ የነበሩ ውስብስብ ዲዛይኖችን በኮምፒውተር የታገዘና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ለማድረግ እንደሚያግዛቸው ያላቸውን እምነት ተናግረዋል።
ይህ የክህሎት ማሻሻያ ስልጠና ኮሌጁ ከኢንዱስትሪው ፍላጎት ጋር የተጣጣመ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ለሚያደርገው ጥረት ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ይጠበቃል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በክላስተር ደረጃ የአሰልጣኞች ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዉድድር ተካሄድ።
🇪🇹የካቲት 20/2018 ዓ.ም🇪🇹
16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አስመልክቶ በክላስተር ደረጃ በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በአራዳ ማኒፋክቸሪንግ ኮሌጅ አሰልጣኞች የተሰሩ ሁለት ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ለዉድድር የቀረቡ ሲሆን ሁለቱም ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በየተቋማቸዉ አንደኛ በመዉጣት ለዛሬዉ የክላስተር ደረጃ ዉድድር የበቁት። የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዓላማ እንደ ተቋም የራስን ችግር በራስ አቅም ለመፍታት ያቀደ ሲሆን ሁለቱም ተግባራዊ ጥናቶች በየተቋሞቻቸዉ ክፍተቶቸን የፈቱ እና ለዉጥ ያመጡ ናቸዉ።
በዉድድሩ ላይም የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች (ኮር ማኔጅመንት) ፣ የስራና ክህሎት ታዛቢዎች ፣ ተጋባዥ እንግጆች እንዲሁም ዳኞች የተገኙ ሲሆን የኢንዱስትሪና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ዲን አቶ ወንድም ሲያምረኝ ለተወዳዳሪዎች የማበረታቻ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ውድድሩም ከስራና ክህሎት በመጣ የማወዳደሪያ መስፈርት መሰረት የተከናወነ ሲሆን በዉድድሩም በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በከተማ ግብርና ስልጠና ዘርፍ የተሰራዉ '' enhancing milk yield through hydroponic fodder supplementation in TMPTC dairy farm '' ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ከፍተኛ ዉጤት በማምጣት አሸናፊ መሆን ችሎዋል። በቀጣይም ተግባራዊ ጥናትና ምርምሩም ክላስተሩን በመወከል ለከተማ ደረጃ በሚካሄደዉ ዉድድር ላይ ተወዳዳሪ ይሆናል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
