ar
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

قناة بسيطة

إظهار المزيد
1 149
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-37 أيام
-1830 أيام
أرشيف المشاركات
ተሰጥኦ፣መዝናኛና እውቀት የሚገናኙበት፣ስሜት በፈጠራ የሚቀልምበት፣በአዳዲስ ባለተሰጥኦዎች የተሞላው መናኝ የኪነጥበብ ምሽት ሊደገም ነው። በበርካቶች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈው የኪነጥበብ ምሽታችን አሁ
ተሰጥኦ፣መዝናኛና እውቀት የሚገናኙበት፣ስሜት በፈጠራ የሚቀልምበት፣በአዳዲስ ባለተሰጥኦዎች የተሞላው መናኝ የኪነጥበብ ምሽት ሊደገም ነው። በበርካቶች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈው የኪነጥበብ ምሽታችን አሁንም በወርሃ መጋቢት ዳግም ወደእናንተ ለመድረስ ዝግጅቱን አጠናቆ ይጠብቃችኋል። በእለቱም   #ግጥሞች   #ወግ   #ሙዚቃ   #ሞኖሎግና   #ተውኔት ተሰናድተዋል። የጥበብ አድናቂ ጓደኞችዎን ይዘው ይምጡ፤ አዳራሻችን በሳቅ፣ በጭብጨባና በኪነ-ጥበብ ፍቅር ይሞላል! 📍 አድራሻ፡ ተፈሪ መኮንን ኮሌጅ (ተፈሪ መኮንን ቴአትር አዳራሽ) 🕑 ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ አይቅሩ—ጥበብ ትጠራዎታለች!

የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከየቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተ /ማ ጋር በመሆን የረመዳን "የማዕድ ማጋራት" እና የአብሮነት መርሃ-ግብር አካሄደ ። 🇪🇹መጋቢት09/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮ
+7
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከየቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተ /ማ ጋር በመሆን የረመዳን "የማዕድ ማጋራት" እና የአብሮነት መርሃ-ግብር አካሄደ ። 🇪🇹መጋቢት09/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቤተሰቦች የዒድ አል-ፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ፣ በተቋሙ ውስጥ ያለውን የእርስ በርስ መተሳሰብና የአብሮነት እሴት የሚያጎላ የጋራ "የማዕድ ማጋራት" መርሃ-ግብር ተካሄደ ። በመርሃ-ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ የተቋም ልማትና አቅም ግንባታ ምክትል ዲን ዶ/ር ከበደ በይቻ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ የኮሌጁ ሰራተኞችና ሰልጣኞች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። አክለውም ይህ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ኮሌጁ ከየቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማህበር ጋር በጋራ ያዘጋጀ መሆኑን ገልጸው ማህበሩን አመስግነዋል ። "የማዕድ ማጋራት" እና የአብሮነት መርሃ-ግብር በመካከላችን ያለውን አብሮነትና ወንድማማችነት የሚያጠናክር እንደሆነ ገልፀው በኮሌጁ ውስጥ እያሳዩ ያሉት የስራ ትጋትና ቁርጠኝነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በዕለቱ በኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች አማካኝነት ለሰራተኞቹ የበዓል ስጦታ የተበረከተ ሲሆን፣ ይህም ሰራተኛው በተቋሙ ውስጥ ያለው ሚና ትልቅ ግምት የሚሰጠው መሆኑን ያሳየበት አጋጣሚ ሆኗል። የመርሃ-ግብሩ ተሳታፊዎችም ኮሌጁ እንዲህ አይነት ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶችን በማክበር ለሰራተኞች እውቅናና ክብር መስጠቱ ለቀጣይ ስራቸው ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥርላቸው ገልጸዋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድንቡ

የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአይሲቲ አሰልጣኞች የግራፊክስ ዲዛይንና ኤዲቲንግ የክህሎት ክፈተት የመሙላት ስልጠና ተጀመረ ። 🇪🇹መጋቢት09/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአይሲቲ (ICT) አሰልጣኞች እና የክላስተር ኮሌጅ አሰልጣኞችን ያካተተ የክህሎት ክፍተታቸውን የሚሞላ የግራፊክስ ዲዛይኒንግ እና ኤዲቲንግ ስልጠና በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ኮሌጅ መሰጠት ተጀመረ። ይህ ስልጠና በአሰልጣኞች ዘንድ ለረጅም ጊዜ ሲታይ የነበረውን የክህሎት ክፍተት ለመሙላት ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በተቋሙ የመማር ማስተማር ሂደትና በስልጠና ጥራት ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል። ለዚህ ስልጠና የሚያስፈልገውን ሙሉ ወጪ በመመደብ ረገድ  እና ስልጠናዉ እንዲዘጋጅ የEASE ፕሮጀክት ከፍተኛ ድርሻ አበርክቷል። የ EASE ፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች እንደገለጹት፣ ስልጠናው የአሰልጣኞችን አቅም በመገንባት መሰረታዊ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ ነው። ፕሮጀክቱ በቀጣይም መሰል ስልጠናዎችን ለማመቻቸትና ዘላቂ መፍትሄዎችን ለማምጣት በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታውቀዋል። ስልጠናው ውጤታማ እንዲሆን የEASE ፕሮጀክት  ከተፈሪ መኮንን ከአቅም ግንባታ  የስራ ሂደት ጋር በቅርበትና በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱ ተገልጿል። የአቅም ግንባታ የስራ ሂደት አስተባባሪዎች እንደገለጹት ስልጠናው የአሰልጣኞችን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል እንዲሁም ተግባራዊ ስልጠናው በገበያው የሚፈለጉ ክህሎቶች ላይ ትኩረት ያደርጋል። በተጨማሪም በኮሌጆች መካከል ያለውን የልምድ ልውውጥና የክላስተር ትስስር ያጠናክራል። ይህ ስልጠና የአሰልጣኞችን ብቃት በማሳደግ፣ ሰልጣኞች በዘመናዊ የግራፊክስ ጥበብና በኤዲቲንግ ስራዎች የሰለጠነ የሰው ኃይል ሆነው እንዲወጡ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ታምኖበታል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+5

መፍትሄ አመላካች "የ2017 የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ስትራቴጂካዊ ግቦች የመነጩ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ስራዎች ለማህበረሰቡና ለተቋማት ። 🇪🇹መጋቢት 09/2018 ዓ.ም🇪🇹 የአዲስ አበባ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች "አቅርቦት-መር" ከነበረው የቆየ አሰራር ወጥተው፣ ለማህበረሰቡና ለተቋማት ተጨባጭ ችግሮች ቴክኖሎጂ-መር መፍትሄዎችን የሚያመነጩ የምርምር ማዕከላት እየሆኑ መምጣታቸውን አስመሰከሩ። የ2017 የቴክኒክና ሙያ ስልጠና (ቴሙሥ) ስትራቴጂን መሠረት በማድረግ የቀረቡ ተግባራዊ ጥናቶች፣ ተቋማቱ የሀገር በቀል ኢኮኖሚው የፈጠራ ሞተር ለመሆን ያላቸውን ዝግጅት አሳይተዋል። በዘርፉ ከተከናወኑት ተግባራዊ ጥናቶች መካከል ተስፋ ሰጪና አርአያ ይሆናሉ ተብለው የተለዩት ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው ። በለሚ ኩራ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ በቤተልሔም አበበ የቀረበው የኦንላይን ማኔጅመንት ሲስተም ጥናት፤ የኮሌጆችን የአገልግሎት አሰጣጥ በማዘመን ማህበረሰቡ ፈጣንና ግልጽ አገልግሎት እንዲያገኝ የሚያስችል ነው። ይህም የስትራቴጂውን "ቴክኖሎጂ-መር" አሰራር በተግባር የሚያረጋግጥ ነው። በጄነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደራርቱ ኡርጋሃ የቀረበው የዶሮ እርባታ ምርታማነትን የማሳደግ ጥናት፤ ተቋማት በራሳቸው ገቢ እንዲመሩና ለማህበረሰቡ የእውቀት ሽግግር ማዕከል እንዲሆኑ የሚያስችለውን "ራስ-ገዝነት" ራዕይ የሚደግፍ ሆኖ ተገኝቷል። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በባንቺአየሁ ጌታሁንና ቡድናቸው የቀረበው የሃይድሮፖኒክ መኖ አጠቃቀም ጥናት፤ በአነስተኛ ቦታ ከፍተኛ የወተት ምርት ለማግኘት ለሚፈልጉ የከተማ ነዋሪዎች ሳይንሳዊና ተግባራዊ መፍትሄን አመላክቷል ።"የእነዚህ ተግባራዊ ጥናቶችና የክህሎት ውድድሮች ዋነኛ ፋይዳ ተቋማቱ በራሳቸው የፈጠራ አቅም የቴክኖሎጂ ባለቤት እንዲሆኑና የማህበረሰቡን ችግር እንዲፈቱ ማስቻል ነው ። እነዚህ አዳዲስና ተስፋ ሰጪ የጥናት ውጤቶች በቅርቡ በሚከበረው 16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ላይ ለህዝብ እይታ የሚቀርቡ ይሆናል። ይህም ኮሌጆቹ ለሀገራዊ ብልጽግና ያላቸውን የቴክኖሎጂና የፈጠራ አቅም በተግባር የሚያሳዩበት ትልቅ መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+5

ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የኮንስትራክሽን ዘርፍ ስልጠና መስጠት ጀመረ ። 🇪🇹መጋቢት 09/2018 ዓ.ም🇪🇹 ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር፣ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን በኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፍ የክህሎት ስልጠና እንዲያገኙ ስምምነት ላይ ደርሶ ስራ ጀምሯል። ይህ ስልጠና ተማሪዎች 12ኛ ክፍልን አጠናቅቀው ሲወጡ በደረጃ አንድ (Level I) እና በደረጃ ሁለት (Level II) የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) ምዘናን አልፈው በቀጥታ ወደ ስራ ዓለም እንዲገቡ ወይም የራሳቸውን የፈጠራ ስራ እንዲጀምሩ ለማስቻል ያለመ ነው። ተማሪዎች በመደበኛ ትምህርት ቤት የሚያገኙትን የንድፈ-ሀሳብ እውቀት በኮሌጁ ዘመናዊ ወርክሾፖች ውስጥ በተግባር እንዲለማመዱ ማድረግ።ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ባያመጡ እንኳ፣ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ባላቸው ሙያ ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ እና፨ ተማሪዎች ከጥገኝነት ወጥተው "የራሴን ስራ እፈጥራለሁ" የሚል ስነ-ልቦና እንዲገነቡ ማገዝ። የኮሌጁ አመራሮች እንደገለጹት፣ ይህ የትስስር ስራ የቴክኒክና ሙያ 11ዱን የልህቀት ምሰሶዎች መሰረት ያደረገ ሲሆን፣ በተለይም የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን ከወጣት ተማሪዎች ጋር ለማስተሳሰር ትልቅ ፋይዳ አለው። ስልጠናው በኮንስትራክሽን ዘርፍ ውስጥ ባሉ ንዑሳን ክፍሎች ማለትም በህንፃ ግንባታ፣ በቧንቧ ስራ እና በሌሎችም ተያያዥ ሙያዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+6

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከGIZ ጋር በመተባበር በICT የስልጠና ዘርፍ በHNS ዘርፍ በካንፓኒዎች ሲሰጥ የነበረው የተግባር ላይ ስልጠና ተጠናቀቀ። 🇪🇹መጋቢት08/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጀርመን ዓለም አቀፍ ትብብር (GIZ) ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የፓይለት ፕሮግራም፣ በHardware and Network Service (ደረጃ 4) የሰለጠኑ 14 ሰልጣኞች በታዋቂ የግልና የመንግስት ተቋማት ውስጥ ሲያካሂዱ የነበረውን የሁለት ወር ከአስራ አምስት ቀን የተግባር ስራ ላይ ልምምድ (Cooperative Training) በስኬት አጠናቀቁ። የዘንድሮው የልምምድ ፕሮግራም ልዩ የሚያደርገው የግል ስራ ዘርፉ (Private Sector) ለTVET ስልጠና ጥራትና ተገቢነት ያለውን ሚና በተግባር ያሳየበት መሆኑ ነው። ስልጠናው በተለይም የነገውን ዓለም ክህሎቶች (Future Skills) ማለትም ዲጂታል ክህሎት (Digital Skills) በICT ዘርፍ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፣አረንጓዴ ክህሎት (Green Skills): ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆኑ አሰራሮች፣ኢንተርፕረነርሺፕ (Entrepreneurship): የራስን ስራ የመፍጠር አቅምን ማሳደግ ላይ ትኩረት አድርጓል። በዕለቱ በተካሄደው ደማቅ የእውቅና መርሃ-ግብር ላይ በልምምድ ሂደቱ በንቃት የተሳተፉት ሮያል ቢዝነስ፣ አፍሪኮም፣ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት፣ ኢአይዲ (EID) እና ሜድሮክ ካምፓኒዎች የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል። ካምፓኒዎቹ በሰጡት ምስክርነት "የሰልጣኞች ብቃት፣ ከፍተኛ የስራ ተነሳሽነትና ከዘመኑ የስራ ዓለም ጋር አብሮ የሚሄድ ስነ-ምግባር ኃላፊነታችንን በስኬት እንድንወጣ አድርጎናል" ብለዋል። ሰልጣኞቹ በበኩላቸው በቆይታቸው የስራ ስነ-ምግባርን፣ የጊዜ አጠቃቀምንና ኃላፊነትን የመወጣት ክህሎት ማዳበራቸውን ገልጸዋል። የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ እንደገለጹት፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና GIZ ለኮፕሬቲቭ ትሬኒንግ ስልጠና እያደረጉት ያለው ድጋፍ ለICT ዘርፉ ትልቅ አቅም ፈጥሯል። "ይህ መድረክ ኮሌጁ ከኢንዱስትሪው ጋር ይበልጥ ተናቦ ለመስራት የሚያስችለውን መነቃቃት የፈጠረና ለተመራቂዎቻችን ቀጥተኛ የስራ ዕድል በመፍጠሩ ምስጋና አቅርበዋል ። በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከGIZ እና ከኮሌጁ የተገኙ ከፍተኛ አመራሮች እንደገለጹት፣ በቀጣይም የግል ካምፓኒዎች ወደ ስልጠናው በስፋት እንዲመጡ በማድረግ የክህሎት ክፍተቶችን በጋራ ለመፍታትና የኢንዱስትሪ መር ስልጠናን (Industry-led Training) ለማጠናከር ስምምነት ላይ ተደርሷል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+3

photo content
+9

ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለ150 ተመራቂ ሰልጣኞች በስራ ፈጠራና ኢንኩቤሽን ላይ ያተኮረ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል ። 🇪🇹መጋቢት07/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የኢን
+7
ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለ150 ተመራቂ ሰልጣኞች በስራ ፈጠራና ኢንኩቤሽን ላይ ያተኮረ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል ። 🇪🇹መጋቢት07/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር የስራ ክፍል፣ ከተለያዩ የሙያ ዘርፎች ለተውጣጡ ከ150 በላይ ተመራቂ ሰልጣኞች በስራ ፈጠራና በኢንኩቤሽን (Incubation) ዙሪያ ያተኮረ ስልጠና መስጠት ጀመረ። ይህ ስልጠና በዋነኝነት ያተኮረው በአይሲቲ (ICT) ፣በጋርመንት (Garment) እና በኤሌክትሪካልና ኤሌክትሮኒክስ የሥልጠና ዘርፍ ትምህርታቸውን አጠናቀው የሚመረቁ ሰልጣኞች ሲሆን የስልጠናው ዋና ዓላማ ተመራቂዎች ከመደበኛው የስራ ቅጥር ባለፈ፣ የራሳቸውን የፈጠራ ስራ ወደ ቢዝነስ በመቀየር ራሳቸውን እንዲችሉና ለሌሎችም የስራ ዕድል እንዲፈጥሩ ማስቻል ነው። ሰልጣኞቹ በቆይታቸው በኮሌጁ ውስጥ በተዘጋጀው የኢንኩቤሽን ማዕከል ተጠቃሚ የሚሆኑበትን መንገድ ጨምሮ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የቢዝነስ ሞዴል አቀራረጽ ላይ ሰፊ ግንዛቤ ያገኛሉ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን ታሪካዊ ዝና የሚያድስ የ500 ካሬ ሜትር ህንፃ ግንባታ ውል ተፈረመ ። 🇪🇹መጋቢት07/2018 ዓ.ም🇪🇹 የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማህበር (Alumni) ለተቋሙ እድገት እያበረከተ ያለውን ታላቅ አስተዋጽኦ በማጠናከር፣ በዛሬው ዕለት የጂ+3 (G+3) ህንፃ እና የአንፊ ቲያትር ግንባታ ውል ስምምነት ከሚሼል ኮንስትራክሽን ጋር በይፋ ተፈራረመ። በ500 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈውና ከጀርባው ለብቻው የሚቆም ዘመናዊ አንፊ ቲያትር (Amphi-theater) የሚያካትተው ይህ ፕሮጀክት፣ የኮሌጁን ጥንታዊና ታሪካዊ ይዘት በጠበቀ መልኩ እንደሚገነባ ተገልጿል። ግንባታው በ18 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከስምምነት ላይ ተደርሷል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት በአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ የውጤት ተኮር ተቋማት ልማት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማ፣ ማህበሩ እያከናወነ ያለው ስራ ለሌሎች ቴክኒክና ሙያ ተቋማት አርአያ የሚሆን መሆኑን ገልጸዋል። "ማህበሩ ከዚህ በላይ ሰፊ አቅም ያለው በመሆኑ በቀጣይም ብዙ ይጠበቅበታል" ሲሉም አክለዋል። የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በመክፈቻ ንግግራቸው የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማህበር ለኮሌጁ እያደረገ ያለውን የላቀ ድጋፍ አድንቀዋል። ማህበሩ ለተቋሙ እድገት የቆመ ትልቅ አጋር መሆኑን በመጥቀስ በኮሌጁ ስም ጥልቅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የግንባታ ውሉን የቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማህበር የካንትሪ ዳይሬክተርና የቦርድ ሴክሬተሪ ወ/ሮ ቆንጂት ተድላ እና የሚሼል ኮንስትራክሽን ባለቤት አቶ ነጋዳር አበሞ በጋራ ፈርመዋል። ማህበሩ በስራና ክህሎት ቢሮ በኩል ለሚደረግለት ድጋፍ ምስጋና አቅርቦ፣ በቀጣይም የተለያዩ የአልሙናይ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን እቅድ እንዳለው ጠቁሟል። ከህንፃ ግንባታው ጎን ለጎን የኮሌጁን የመቶ ዓመት ታሪክ ለትውልድ ለማቆየት የታሪክ መጽሐፍ የማጻፍ ስራ በይፋ ተጀምሯል። ጨረታውን ያሸነፉት የታሪክ መምህሩ ዶክተር አጉቾ አማረ ጥናቱን እንዲያካሂዱ የተለዩ ሲሆን፣ ለስራው መሳካት ኮሌጁ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ በማህበሩ ቀርቧል። በመጨረሻም በኮሌጁ እና በቀድሞ ተማሪዎች ማህበር መካከል ያለውን አጋርነት ይበልጥ የሚያጠናክር የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ተፈርሞ ፕሮጀክቱ በይፋ ተጀምሯል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+1

photo content
+9

የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለቴክስታይልና ጋርመንት አሰልጣኞች  የአዶቤ ኢሉስትሬተር ሲሰጥ የነበረዉ የክህሎት ክፍተት ስልጠና ተጠናቀቀ። 🇪🇹መጋቢት07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቴክስታይልና ጋርመንት ስልጠና ዘርፍ ለሚገኙ አሰልጣኞች የክህሎት ክፍተትን ለመሙላት የታለመ የ10 ቀናት የአዶቤ ኢሉስትሬተር (Adobe Illustrator) ሰደረግ የነበረዉ ስልጠና  ተጠናቋል። ይህ ስልጠና በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አማካኝነት የተደረገ ስልጠና ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም በዘርፉ ያለውን የዲጂታል ዲዛይን የክህሎት ክፍተት በመሙላት የሥልጠና ጥራቱን ማሳደግ ነው።ስልጠናዉ ለአሥር ተከታታይ ቀናት የቆየ ሲሆን የዚህ ስልጠና ሙሉ ወጪ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት የተሸፈነ ነው። EASE ፕሮጀክት በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሚታዩ የክህሎት ክፍተቶችን በመለየትና ተግባራዊ ስልጠናዎችን በመደገፍ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ስልጠናውን ሲከታተሉ የነበረ ሰልጣኞች እንደገለጹት የቴክኖሎጂ ሽግግር አዶቤ ኢሉስትሬተር በዘመናዊው የጋርመንት ኢንዱስትሪ ውስጥ ለፋሽን ዲዛይንና ለፓተርን ዝግጅት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ ስልጠናው በዘርፉ የነበረባቸውን የረጅም ጊዜ የክህሎት ክፍተት እንደሚቀርፍላቸው ሰልጣኞች ገልጸዋል። በተጨማሪም ስልጠናዉ በእጅ ይሠሩ የነበሩ ውስብስብ ዲዛይኖችን በኮምፒውተር የታገዘና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ለማድረግ እንደሚያግዛቸው ያላቸውን እምነት ተናግረዋል። ይህ የክህሎት ማሻሻያ ስልጠና ኮሌጁ ከኢንዱስትሪው ፍላጎት ጋር የተጣጣመ ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት ለሚያደርገው ጥረት ትልቅ እገዛ እንደሚኖረው ስልጠናዉን ሲከታተሉ የነበሩ ሰልጣኞች ገልጸዋል። በስተመጨረሻም በስልጠናዉ ላይ ለተሳተፉት ሰልጣኞች ሰርተፍኬት የመስጠት ፕሮግራም በማድረግ የስልጠናዉ መርሃግብር ተጠናቋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+3

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ “የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለጤናማና ውጤታማ የሥራ ማህበረሰብ” በሚል ርዕስ የልምድ ልውውጥ ተካሄደ። 🇪🇹መጋቢት07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በየሳምንቱ የሚካሄደው "የወርቃማው ሰኞ" የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለ28ኛ ሳምንት በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል።የኮሌጁ የኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ የስፖርት ትምህርት ክፍል፣ ለኮሌጁ ማህበረሰብ “የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ጤና”በሚል መሪ ቃል ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተደረገ ። በዕለቱ ገለጻውን የሰጡት የስፖርት ትምህርት ክፍል አሰልጣኝ አቶ ዮሐንስ ዋለ የአካል ብቃት እንቅስቃሴና ጤና ያላቸውን ጥብቅ ቁርኝት ለተሳታፊዎች በዝርዝር አስረድተዋል። አሰልጣኙ በገለጻቸው ወቅት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማለት አንድ ሰው የዕለት ተዕለት ተግባራቱን ያለ ከፍተኛ ድካም እንዲያከናውን የሚያስችለው የአካል ብቃትና ዝግጁነት መሆኑን ገልጸው፣ ይህንንም ከጤና ጋር በማስተሳሰር ግንዛቤ ሰጥተዋል። አሰልጣኝ ዮሐንስ በዋነኝነት ካብራሯቸው ነጥቦች መካከል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አስፈላጊነት ፣ ስፖርት የሰውነትን በሽታ የመከላከል አቅም እንደሚጨምር፣ ከውጥረትና ከአእምሮ ድካም ነጻ እንደሚያደርግ እንዲሁም ለሥራ ምርታማነት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ዓይነቶች እንደ ልብና የደም ዝውውርን የሚያጠናክሩ ፣ የጡንቻ ጥንካሬን የሚጨምሩና የሰውነት መለዋወጥን የሚያሳድጉ እንቅስቃሴዎችን በተግባር ጭምር በማስረዳት ግንዛቤ ሰጥተዋል። የኮሌጁ ማህበረሰብ ለስፖርት ያለውን ግንዛቤ በመቀየር፣ ስፖርትን እንደ ፋሽን ሳይሆን እንደ ጤና መጠበቂያ ስልት እንዲያዘወትሩ አሳስበዋል። መደበኛ እንቅስቃሴ ማድረግ ከስኳር፣ ከደም ግፊትና ከልክ ያለፈ ውፍረት እንደሚከላከልም በገለጻቸው ወቅት በስፋት ተዳስሷል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን