1 146
المشتركون
-224 ساعات
-47 أيام
-1930 أيام
أرشيف المشاركات
1 146
የስራ ባልደረባችን አቶ ፍሬዓለም ጥሩነህ በማረፋቸው የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቹ ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለስራ ባልደረቦቹ መጽናናትን እንመኛለን።
የቀብር ስነ-ስርዓታቸው በዛሬው ዕለት
ጥር 7/2017ዓ.ም ከቀኑ 9:00 በቀጨኔ
መድሀኒዓለም ይፈፀማል
ፈጣሪ ነብስህን በአፀደ ገነት ያሳርፍልን።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+6
ጥር 2017ዓ.ም
ስልጠናን በተግባር
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የGMF ስልጠና ዘርፍ ስልጠናውን ከተግባር ጋር በማቀናጀት ይበል የሚያስብል ተግባር አከናውኗል።
የኮሌጅ የGMF ስልጠና ዘርፍ ከማሰልጠን ባሻገር የከተማ አስተዳደሩ በሚያከናውናቸው የተለያዩ ተግባራት ላይ የበኩሉን በመወጣት ፋና ወጊ ስልጠና ዘርፍ ነው ።
ይህ ተግባሩን ከስልጠናው ጋር በማስተሳሰር በብረታ ብረትና እንጨት ስራ ትምህርት ክፍል ለረጅም ዓመታት የማይሰሩ በመሆናቸው ይወገዱ ተብለው የተለዩ ማሽኖችን አሠልጣኝ ራውል ደርቤ በፕሮጀክት ቤዝድ ስልጠና ውስጥ በማካተት የመካኒክስ እና የማሽን ደረጃ 2 ሠልጣኞችን የተግባር ስልጠና በመስጠት
1. ስምንት የመበየጃ ማሽኖች
2. አንድ የመላጊያ ማሽን
3. አንድ ሳንደር ማሽን በመጠገን በአንድ ወንጭፍ ሁለት ወፍ እንዳሉት ሠልጣኞች የተግባር ስልጠናን እንዲሰለጥኑ የማሽን ጥገናውን በተሳካ ሁኔታ በማከናወን ለአገልግሎት እንዲበቃ ማስቻላቸውን ከትምህርት ክፍሉ የተገኘ መረጃ ያመላክታል ።
በመሆኑም ከስልጠናው ባሻገር ማሽኖቹን ለማስጠገን ይወጣ የነበረውን 29,800 (ሃያ ዘጠኝ ሽህ ስምንት መቶ ብር) ማዳን እንደተቻለ የስልጠና ዘርፍ አስተባባሪው አቶ ታሪኩ ሁሉቃ መረጃውን አስተላልፈዋል። በዚህ ተግባር ላይ ለተሳተፉ አሠልጣኝ ራውል ደርቤ እና ሠልጣኞች በስልጠና ዘርፉ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
በመጨረሻም ይህን ተሞክሮ ሌሎች የስልጠና ዘርፎች ቢጋሩት እና ቢጠቀሙበት በየስልጠና ዘርፉ ያሉ የማሰልጠኛ ማሽኖች እጥረትን ለመቅረፍ የሚያግዝ መሆኑን እየገለጽን በርቱ ተበራቱ እንላለን ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+3
ዕለተ ሐሙስ ጥር 1/2017 ዓ.ም
የተቋማት ልማትና አስተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ የ2017በጀት ዓመት የ2ኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ተገመገመ ።
ሪፖርቱ የቁልፍ ተግባር አፈጻጸም ፣ ዓበይት ተግባራትን እንዲሁም ጠንካራ ጎኖች ያጋጠሙ ችግሮች እና የተወሰዱ መፍትሄዎችን በግልጽ አመላክቷል።
ዶ/ር ከበደ ለአቅራቢው ምስጋናቸውን ችረው ቤቱ በቀረበው የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ቀረ ወይም የተጋነነ ነው የሚሉት ካላቸው ሃሳብ አስተያየት እንዲሰጡበት ተጠቁሟል። ከተሳታፊዎች በቀረበው ሪፖርት በሚገባ አልተካተተም ያሏቸውን ሃሳቦች በተለይ የሴቶች ተሳትፎ እና ለሠራተኞች በተሰጠ ስልጠና ላይ፣ የጥገና ኮሚቴ ፣የበጎ አድራጎት ስራዎች እንዲሁም ለኮሌጁ የውስጥ ገቢ ማስገኛ የተሰሩ ስራዎች ያልተካተቱ መሆናቸውን በማመላከት ውይይት ተደርጎባቸው ተስተካክለው እንዲቀርቡ ከጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+3
ዕለተ ሐሙስ ጥር 1/2017ዓ.ም
ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ስልጠና ማስጀመሪያ ኦረንቴሽን ተሠጠ።
ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ለተውጣጡ 412 ሴትች እና 458 ወንድ ስራ ፈላጊ ወጣቶች በንግድ ስራ ክህሎት የሚሰለጥኑ ሲሆን ስልጠናው ለአንድ ሳምንት የሚቆይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው ስልጠናውን በአግባቡ እንዲከታተሉና በመጨረሻም ምዘና ተመዝነው ብቃታቸውን አረጋግጠው የሚወጡ መሆናቸውም ተገልጿል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+4
ዕለተ ሐሙስ ታህሳስ 24/2017ዓ.ም
የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ክፍል በ4ቱ የድጋፍ ማእቀፍ ላይ ስልጠና ተሰጠ።
የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ስራው የተሳለጠና በሚፈለገው ደረጃና ጥራት እንዲከናወን ስራው ለሚመለከታቸው አካላት የአቅም ግንባታ ስራዎችን ማከናወን አሌ የማይባል ተግባር ነው። በመሆኑም
በዚህ ስልጠና የጉለሌ ክፍለ ከተማ የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ባለሙያዎች ፣ ከወረዳ 1 እስከ ወረዳ 8 ስራና ክህሎት ጽ/ቤት የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አስተባባሪ ባለሙያዎች ፣ በኮሌጃችን ለኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ የተመደቡ አሰልጣኞች ፣ የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አስተባባሪ ባለሙያዎች እና የቴክኖሎጂ ዲዛይን አዋጭነት ማረጋገጥ ባለሙያዎች ተሳታፊ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።
የስልጠናው በ4ቱም የድጋፍ ማዕቀፎች ካይዘን፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንተርፕሩነር ሺፕ እና ቴክኒካል ክህሎት ላይ ያተኮረ ሲሆን
- በካይዘን ድጋፍ የፈራ ሃብት ጥመራ ፣ ኢንተርፕሩነር ሺፕ/ቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታና - በቴክኖሎጂ ሽግግር በድጋፍ የሚፈሩ ሃብቶች ጥመራ እንዲሁም ንብረት አመዘጋገብን አስመልክቶ የተሰጠ መሆኑን የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ዘገየ መረጃውን አጋርተውናል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+5
ዕለተ ሐሙስ ታህሳስ 24/2017 ዓ.ም
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በንግድ ምልክት፣ በፓተንት እና ኮፒ ራይት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ።
በኮሌጃችን ከተለያዩ ስልጠና ዘርፎች ለተውጣጡ የኮሌጃችን ሠልጣኞች
- አእምሯዊ ንብረት ምንድ ነው?
- የአእምሯዊ ንብረት ምዝገባ
- የፓተንት ምንነት
- የፓተንት ማመልከቻ አይነቶች
- ፓተንት ለባለ ፓተንቱ የሚሰጣቸው መብቶች
- የባለ ፓተንቱ ግዴታዎች
- የንግድ ምልክት
- የንግድ ምልክት አይነቶች
- የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ምዝገባ እንዲሁም ኮፒራይትን አስመልክቶ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
በተመሳሳይ የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ባለስልጣን የአእምሯዊ ንብረት ጥበቃ ባለቤትነትን በማረጋገጥ የፈጠራ ስራዎችን በማበረታታት ፍትሃዊ ውድድርን የሚያሰፍን መሆኑ የገለጹት የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ከፍተኛ ባለሙያ ወ/ሮ ሂሩት ቢራራ ገልፀዋል።
በአጠቃላይ የአእምሯዊ ንብረት ባለቤትነት ጥበቃ መረጋገጥ ማህበረሰቡ ጥራት ያለውን አገልግሎት እንዲያገኝ የሚያስችለው ሲሆን በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ ተጠቁሟል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+6
ታህሳስ / 2017ዓ.ም
በGMF ስልጠና ዘርፍ በእንጨት ስራ፣በማሽንና መካኒክስ ትምህርት ክፍል በአዲሱ የስልጠና ፖሊሲ የሠለጠኑ ሠልጣኞች የተቋም ምዘና ተመዘኑ ።
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የGMF ስልጠና ዘርፍ በከተማ ደረጃ የሚከናወኑ የተለያዩ የኮሪደር ልማት ስራዎችም ሆነ በሌሎች ስራዎች ላይ ደከመን ሰለቸን ሳይሉ ስራዎችን በማከናወን ላይ ሰፊ ድርሻ ያለው መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ትምህርት ክፍሉ ተቀብሎ የሚያሰለጥናቸውን ሰልጣኞች በእንጨት ስራ የደረጃ 1ና የደረጃ 2 ሰልጣኞችን እንዲሁም በማሽን እና በመካኒክስ የደረጃ 1 ሰልጣኞችን በትምህርት ክፍሉ ተዘጋጅቶ በተዋረድ በስልጠና ዘርፉ እንዲሁም በስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ጸድቆ የቀረበውን የተግባርና የንድፈ ሃሳብ ምዘና ተመዝነዋል ።
ለምዘናው የተቀመጡት በእንጨት ስራ 16 እና በብረታ ብረት 26 ተመዛኞች መሆናቸው ታውቋል። ምዘናውን ከወሰዱት መካከል ከእንጨት ስራ 100% እና ከብረታ ብረት 69% ብቃታቸው የተረጋገጠ በመሆኑ ወደ ቀጣይ ደረጃ ይሸጋገራሉ ፤ በምዘናው ብቁ ያልሆኑት በቀጣይ ክፍተታቸውን በመለየትና ክፍተቱን በስልጠና በመሙላት ዳግም ይመዘናሉ በማለት መረጃውን ያጋሩን የስልጠና ዘርፍ ተጠሪው አቶ ታሪኩ ሁሉቃ ።
አቶ ታሪኩ አክለውም ይህ ምዘና በቀጣይ ሰልጣኞች የተመዘገቡበትን ደረጃ ስልጠና ሲያጠናቅቁ በከተማ ደረጃ ለሚዘጋጀው ሁሉን አቀፍ ምዘና የዝግጅት ምዕራፍ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
አለምአቀፍ የሙዚቀኞች ቡድን የተሳተፉበት የሙዚቃ ወርክሾፕ በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ተካሄደ።
ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም
~~~~
በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ለሚካሄደው ታላቅ ''የኦፔራ ምሽት'' ወደ ኢትዮጵያ የመጡ አለም አቀፍ ሙዚቀኞች በኮሌጃችን ለሚገኙ የሙዚቃ ት/ክፍል ሰልጣኞች ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት ወርክሾፕ
ተዘጋጀ።
በወርክሾፑ የቴምፕል ዩኒቨርስቲ የሙዚቃ ምሩቅ የሆነችዉ ኢትዮጵያዊቷ ምኞት ቶጃ ፣ ታይላንዳዊ አሜሪካዊዋ ፒያኒስት ሲራፓት ጅቲፒሮም እና ሌሎች ከአሜሪካ የመጡ የሙዚቃ ባለሙያዎች ለኮሌጃችን የሙዚቃ ት/ክፍል ሰልጣኞች በድምጽ ቴክኒክ እና የሙዚቃ መሳሪያ ዙሪያ ልምዳቸዉን አካፍለዋል። ከእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ሰልጣኞች በተጨማሪ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎችም በወርክሾፑ ተካፍለዋል።
የፈረንጆች ገና እና አዲስ አመት አስመልክቶ በተለያዩ አገራት መሰል የሙዚቃ ዝግጅቶች የሚከናወን ሲሆን ኢትዮጵያዊቷ የኦፔራ ንግስት ምኞት ቶጃ በአዲስ አበባ ለሚገኙ የዲፕሎማቲክ ሚሽን አባላት እና የኦፔራ ሙዚቃ አድናቂዎች በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ዝግጅቷን ታቀርባለች ተብሎ ይጠበቃል።
ወርክሾፑን ያዘጋጀዉ የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የኤስቴቲክስ ት/ክፍል የሙዚቃ ዲፓርትመንት ሲሆን አለም አቀፍ ሙዚቀኞች ልምዳቸዉን ሲያካፍሉ በኮሌጁ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ማወቅ ተችሏል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
አለምአቀፍ የሙዚቀኞች ቡድን የተሳተፉበት የሙዚቃ ወርክሾፕ በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ተካሄደ።
ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም
~~~~
በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ለሚካሄደው ታላቅ ''የኦፔራ ምሽት'' ወደ ኢትዮጵያ የመጡ አለም አቀፍ ሙዚቀኞች በኮሌጃችን ለሚገኙ የሙዚቃ ት/ክፍል ሰልጣኞች ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት ወርክሾፕ
ተዘጋጀ።
በወርክሾፑ የቴምፕል ዩኒቨርስቲ የሙዚቃ ምሩቅ የሆነችዉ ኢትዮጵያዊቷ ምኞት ቶጃ ፣ ታይላንዳዊ አሜሪካዊዋ ፒያኒስት ሲራፓት ጅቲፒሮም እና ሌሎች ከአሜሪካ የመጡ የሙዚቃ ባለሙያዎች ለኮሌጃችን የሙዚቃ ት/ክፍል ሰልጣኞች በድምጽ ቴክኒክ እና የሙዚቃ መሳሪያ ዙሪያ ልምዳቸዉን አካፍለዋል። ከእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ሰልጣኞች በተጨማሪ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎችም በወርክሾፑ ተካፍለዋል።
የፈረንጆች ገና እና አዲስ አመት አስመልክቶ በተለያዩ አገራት መሰል የሙዚቃ ዝግጅቶች የሚከናወን ሲሆን ኢትዮጵያዊቷ የኦፔራ ንግስት ምኞት ቶጃ በአዲስ አበባ ለሚገኙ የዲፕሎማቲክ ሚሽን አባላት እና የኦፔራ ሙዚቃ አድናቂዎች በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ ዝግጅቷን ታቀርባለች ተብሎ ይጠበቃል።
ወርክሾፑን ያዘጋጀዉ የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የኤስቴቲክስ ት/ክፍል የሙዚቃ ዲፓርትመንት ሲሆን አለም አቀፍ ሙዚቀኞች ልምዳቸዉን ሲያካፍሉ በኮሌጁ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሆነ ማወቅ ተችሏል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የተማሪዎች ካወንስል አባላት ምርጫ ተካሄደ።
ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም
የተማሪዎች ካወንስል አደረጃጀት በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የተማሪዎች መብትና ግዴታ፣ የክበባት ተሳትፎ፣ ጥናትና ምርምር ፣ ቴክኖሎጂ ፈጠራ እና ቅጅ እንዲሁም ተማሪዎች በኮሌጁ የሚኖራቸዉን አጠቃላይ ተሳትፎ ከኮሌጁ ማኔጀመንት ጋር በመሆን የሚሰራ አደረጃጀት ነዉ።
የኮሌጁ የተማሪዎች ካዉንስል ሰባት መዋቅሮች ያሉት ሲሆን ከዚህ በፊት ሲያገለግሉ የነበሩ የካዉንስሉ አባላት በአዳዲስ አባላት ተተክተዋል። በዚህም መሰረት
1.ተማሪ ናሆም ግርማ (ከአዉቶሞቲቭ ት/ክፍል) - ፕሬዚዳንት
2. ተማሪ የሸጥላ ዳኛቸዉ (ከኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ት/ክፍል)- ጸሀፊ
3.ተማሪ ፍቅረማርያም ጥላሁን (ከሆቴልና ቱሪዝም ት/ክፍል)- የአካዳሚክ ጉዳዮች ተወካይ
4. ተማሪ ቤተልሔም ሰለሞን (ከጋርመንት ት/ክፍል)- የክበባት ጉዳዮች ተጠሪ
5.ተማሪ ጽዮን አካለወልድ (ከጋርመንት ት/ክፍል)- የሴቶች ጉዳይ
6. ተማሪ ብሩክ ይመኑ (ከአዉቶሞቲቭ ት/ክፍል)- የአካል ጉዳተኞች ተጠሪ
7.ተማሪ ሀና ደረጀ (ከሆቴልና ቱሪዝም ት/ክፍል)- አባል
በመሆን ተመርጠዋል ።
በምርጫው ስነስርአት ላይ የተገኙት የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ስልጠና ጉዳዮች እና አካዳሚክ ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ አዲስ የተመረጡ የካዉንስል አባላት ከቀድሞዎቹ የካዉንስል አባላት ልምድ በመዉሰድ እና ከኮሌጁ ማኔጅመንት አካላት ጋር በቅርበት በመስራት የተጣለባቸዉን ሃላፊነት እንዲወጡ አሳስብዋል ።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የእ
ስራ ፈላጊዎች የሴቶችና የወጣቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና መስጠት ጀመረ።
(ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 17 -04 -2017 ዓ.ም)
የክፍለ ከተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት በ3 ወራት ዕቅድ ለያዘው ከ10ሩም ወረዳ የተወጣጡ የስራ ዕድል የሚፈጠርላቸው ሴቶችና ወጣቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠና መስጠት ጀመረ።
በስልጠና ማስጀመሪያው ላይ ተገኝተው ለሰልጣኞች መልዕክት ያስተላለፉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰሎሞን ታደሰ እንደተናገሩት አስተዳደሩ በ3 ወራት ፍትሃዊ የሴቶችና የወጣቶችን ስራ ዕድል ፈጠራ ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ ይገኛል ያሉ ሲሆን በዛሬው ዕለት ለሚሰጠው የሕይወት ክህሎት ስልጠና ወጣቶች ግንዛቤያቸውን በማስፋት በተሰማሩበት የስራ መስክ ላይ በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት በመተግበር ውጤታማነታችሁን ማረጋገጥ ይገባችኋል ብለዋል።
የክፍለ ከተማው ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መሠረት በለጠ በበኩላቸው ክህሎት መር የሆነ የስራ ዕድል ፈጠራን ለማረጋገጥ ስራ ፈላጊዎች ወጣቶችን በስልጠና እንዲያልፉ በማድረግ በተሰማሩበት የስራ ዘርፍ ምርትና ምርታማነታቸው ማረጋገጥ በመሆኑ የዛሬው የሕይወት ክህሎት ስልጠና ማስጀመሪያ የዚሁ አካል ነው ብለዋል።
1 146
ለኮሌጁ ሰራተኞች በሙሉ
በነገው እለት 17/04/2017 ዓ.ም በኮልጁ ውስጥ "ሰብአዊ መብት ያከበረ የኤች.አይ.ቪ አገልግሎት ለሁሉም" በሚል መሪ ቃል የጸረ ኤድስ ቀን የሚከበር በመሆኑ ሁሉም የኮሌጁ ሰራተኛ ጠዋት 3:00 በቴክኖሎጂ አዳራሽ እንዲገኝ ጥሪ እናስተላልፋለን።
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
